የጥናትና ምርምር ማእከል 4ኛ ዓመታዊ የጥናት ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡

ነሐሴ 18 ቀን 2004 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ


“በማኅበረ ቅዱሳን የጥናትና ምርምር ማእከል   ለነሐሴ 19 እና 20 ሊያካሂደው የነበረው የጥናት ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን በተከሰተው የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ ዜና እረፍት ምክንያት ጉባኤውን ማካሄድ ባለመቻላችን ይቅርታ እየጠየቅን መርሐ ግብሩ ወደ ጳጉሜ 3 እና 4 ቀን 2004 ዓ.ም. መተላለፉን እንገልጻለን” በማለት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሰይፈ አበበ ገለጹ፡፡

 

በጥናቱ ላይ ከተካተቱት ዋና ዋና ርዕሰ ጉዳዮች መካከል የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅርሶች ጥበቃና አያያዝ፣ የሕግ አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን፣ የአብነት ትምህርት ቤቶች ለሀገር ያበረከቱት አስተዋጽኦ፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ካህናት አባቶች ሚና  በምክክር አገልግሎት፣ The role of folklore in controlling sexual behavior in Christian context, አንዳንድ ነጥቦች ስለማኅበረ ቅዱሳን፣ ኅትመቶች አስተዳደራዊና ሀገር አቀፋዊ ጉዳዮች አዘጋገብ የተሰኙት ይገኙበታል፡፡

 

በእያንዳንዱ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ጥናቱን የሚያቀርቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ሲሆኑ ሰፊ ውይይት እንደሚካሄድባቸው የጥናትና ምርምር ማእከሉ ምክትል ዳይሬክተር  ገልጸዋል፡፡