IMG 0062

ዝግጅት ለጥምቀት በዓል

 

IMG 0062የጥምቀት በዓል በኢትጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ የጥምቀት በዓልን በአደባባይ በማክበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ብቸኛዋ ቤተክርስቲያን  ስትሆን ከተለያዩ ዓለማት የበዓሉ ታዳሚ ለመሆን የእምነቱ ተከታዮችና ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ወደ ጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታዎች ይሄዳሉ፡፡ ከበዓሉ ቀደም ብሎ ለታቦታቱ ማረፊያና ለበዓሉ ማክበሪያ የተለያዩ ዝግጅቶች ይከናወናሉ፡፡
 ካህናትና ምእመናን  ለበዓሉ የሚስማማ ልብስ በመልበስ ታቦታቱን በማጀብ  ከከተራ ጀምሮ በዝማሬና በእልልታ እስከ ቃና ዘገሊላ ድረስ በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡
ሰሞኑንም በሀገራችን የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታዎችና ታቦታቱ የሚጓዙበት መንገዶች ሲጸዱና ሲያሸበርቁ ሰንብተዋል፡፡ ጥቂት ቦታዎችን ለመጎብኘት ሞክረናል፡፡

አዲስ አበባ
በአዲስ አበባ ከተማ 46 የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታዎች አሉ፡፡ ወደነዚህ ቦታዎች የሚወስዱ መንገዶች ሁሉ እየጸዱ በኢትዮጵያ ባንዲራ፣ በዘንባባና በቄጤማ እያሸበረቁ ይገኛሉ፡፡
በአራዳና በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቶች ያገኘነው መረጃ እንደሚገልጸው፡-
1.    በጃንሜዳ የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ከአስራ አንድ ባላይ ታቦታት የሚያድሩ ሲሆን እነሱም መንበረ ፓትርያርክ ቅ/ቅ/ማርያም ገዳም፣ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም፣ መ/ፀ/ቅ/ሥላሴ፣ መ/መ/ቅ/ገብርኤል፣ ገነተ ጽጌ ቅ/ጊዮርጊስ፣ ቀጨኔ ደ/ሰ መድኃኔዓለም፣ መንበረ ልዑል ቅ/ማርቆስ፣ ወ/ነጎድጓድ ቅ/ዮሐንስ ፣ገነተ ኢየሱስ፣ መ/ህ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አንቀጸ ምሕረት ቅ/ሚካኤል ሲሆን የ2006 ዓ.ም በዓል መንፈሳዊ አገልግሎት አቅራቢ ተረኛ የወ/ነጎድጓድ ቅ/ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡

IMG 0034IMG 0045

2.    ወረዳ 13 ቀበሌ 16 ቀበና ሼል አካባቢ ቀበና መድኃኔዓለምና ቀበና ኪዳነምሕረት
3.    በጉለሌ እንጦጦ ተራራ  መ/ፀ ር/አድባራት ቅ/ማርያም እና እንጦጦ ደ/ኃ/ቅ/ራጉኤል
4.    ሽሮ ሜዳ አካባቢ
መንበረ ስብሐት ቅ/ሥላሴ፣ ሐመረ ኖህ ቅ/ኪዳነ ምሕረት
5.    ወረዳ 11 ቀ. 27 ቁስቋም አካባቢ መ/ንግሥት ቁስቋም ማርያም
6.    አዲሱ ገበያ በላይ ዘለቀ መንገድ አካባቢ ደ/ሲና እግዚአብሔር አብ፣ መንበረ ክብር ቅ/ሚካኤል እና አቡነ ተክለሃይማኖት
7.    ጉለሌ አምባ ቅ/ኪዳነ ምሕረትና ድልበር መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን
8.   ወረዳ 11 ቀበሌ 20 ፡-ገርጂ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን፤ የረር ቅዱስ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን፤ ቦሌ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን
9.   ወረዳ 17 ቀበለሌ 24 /ለምለም ሜዳ/፡-ደብረ ምጽላል እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን፤
10.  ወረዳ 17 ቀበሌ 2 ወንድራይድ ት/ቤት አካባቢ፡- 7 አብያተ ክርሰቲያናት
11.  ወረዳ 28፡- ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም፤ አቡነ አረጋዊ፤ ቅዱስ ኡራኤል
12.  ወረዳ 16/17 ቀበሌ 1፡- ደብረ እንቁ ልደታ ለማርያም፤
13.  ሎቄ ገበሬ ማኅበር፡- ሎቄ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
14.  ወረዳ 17 ገበሬ ማኅበር፡- ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ጊዮርጊስ
15.  ወረዳ 28 ገበሬ ማኅበር ቀበሌ 14/15 ሲኤም ሲ፡- ሰሚት ኪዳነ ምሕረት፤ ቀሬ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤  ወጂ መድኀኔዓለም
16.  ቦሌ 14 /15፡- መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ የረር ቅዱስ ገብርኤል፤ የረር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ
17.  ወረዳ 28 ገበሬ ማኅበር፡-  ደብረ ኢያሪኮ እግዚአብሔር አብ
18.  ራስ ኃይሉ ሜዳ/ መድኀኔዓለም ትምህርት ቤት አካባቢ፡- ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል፤ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል፤ ጽርሐ አርያም ሩፋኤል፤ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጼጥሮስ ወጳውሎስ፤ ጠሮ ሥላሴ
19.  ትንሹ አቃቂ ወንዝ/ ገዳመ ኢየሱስ/፡- ቀራንዮ መድኀኔዓለም፤ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል፤ ቅዱስ ጳውሎስ፤ ገዳመ ኢየሱስ፤ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ፤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም፤ ፊሊዶር አቡነ ተክለ ሃማኖት
20.  አስኮ ጫማ ፋብሪካ / ሳንሱሲ አካባቢ፡- አስኮ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል፤ ኩርፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ
21.  ወረዳ 25 ቀበሌ 25 አካባቢ፡- ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ገብረ ክርስቶስ፤ ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ አውጉስታ ቅድስት ማርያም፤ ዳግማዊት ጸድቃኔ ማርያም፤
22.  ወረዳ 24 ቀበሌ 15፡- አየር ጤና ኪዳነ ምሕረት፤ ጀሞ ሥላሴ፤ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል
23.  ቃሌ 15 ቀበሌ፡- ቃሉ ተራራ አቡነ ሃብተ ማርያም፤ ፍኖተ ሎዛ ቅድስት ማርያም
24.  አያት ቤተ ሥራዎች ድርጅት፡- መሪ አቡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡- መሪ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት፤ ቅዱስ ሩፋኤል፤ መሪ ቅድስት ሥላሴ
25.  ወረዳ 28 ገበሮ ማኅበር፡- ኢያሪኮ እግዚአብሔር አብ
26.  ቤተል ኳስ ሜዳ፡- ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል፤ አንፎ ቅዱስ ኡራኤል
27.  ወረዳ 18 ቀበሌ 26፡- ቅዱስ እስጢፋኖስ፤ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ
28.  ወረዳ 16 ቀበሌ 11 ኳስ ሜዳ፡- ደብረ ጽጌ ቅዱስ ኡራኤል፤ የካ ቅዱስ ሚካኤል
29.  አድዋ ፓርክ፡-ቦሌ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም

IMG 0056

ከአዲስ አበባ ወጪ የሚገኙ አኅጉረ ስብከት በከፊል
  የበዓለ ጥምቀት ዝግጅት በጎንደር – ፋሲለደስ፡-
ቀሃ ኢየሱስ፤ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አባ ጃሌ ተክለ ሃማኖት፤ እልፍኝ ቀዱስ ጊዮርጊስ፤ ፊት ሚካኤል፤ አጣጣሚ ሚካኤል፤ መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም
ፋሲለድስ መዋኛ ፡- 8 ታቦታት
ልደታ ለማርያም
በዓታ ለማርያም
   አቡነ ሐራ – ሩፋኤልን ዞሮ ይገባል
በጎንደር ዙሪያ በሚገኙ 13 ቀበሌዎች፤ 13 ክፍለ ከተማዎችና የገጠር ቀበሌዎች

በሐዋሳ  የበዓለ ጥምቀት ዝግጅት
ፒያሳ ሔቁ አካባቢ፡- ደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም
ቅዱስ ገብርኤል
ቅድስት ሥላሴ
ፋኑኤል
በዓለ ወልድ
ዳቶ ኪዳነ ምሕረት
ሐዋሳ መግቢ በይርጋለም ሞኖፖል አካባቢ፡- ደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም፤ አቡነ ተክለ ሃማኖት፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ

የበዓለ ጥምቀት ዝግጅት በሚዛን ተፈሪ
በሚዛን ተፈሪ ከተማ በሚዛንና አማን ክፍለ ከተማ ለሚከበረው  በዓል ከከተራው  ጀምሮ የከተማዋን ዋና መንገድ በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ  የማስዋብ ስራ በከተማው የእምነቱ ተከታይ ወጣቶች ተሰርቷል:: በከተማው የዘንድሮው የበዓሉን ዝግጅት ተረኛ የሆኑት የአቡነ ተክለሀይማኖት የእናቶች አንድነት ገዳምና የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስትያን ለታቦታት ማደርያና እንዲሁም ለስርኣተ ማኅሌቱና ቅዳሴው የሚከናወንበት ድንኳን በሰበካ ጉባኤያት አስተባባሪነት፣ በወጣት ሰንበት ተማሪዎች ፣ በሚዛን መዕከል አባላት፣ በሚዛን ግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችና በአካባቢው የሚገኙ የእምነቱ ተከታይ ወጣቶች ተባባሪነት የጥምቀተ ባህር ማክበርያ ቦታ ጽዳት ከተደረገ በኋላ ድንኳንና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን በማቅረብ በዓሉን ለማድመቅ ተዘጋጅተዋል::
በዓሉ የሚከበረው በሁለት የጥምቀተ ባህር ስፍራዎች ኮሶኮልና አማን ጥምቀተ ባህር ናቸው፡፡  በሚዛን ክፍለ ከተማ ከሾርሹ በዓለ ወልድ አንድ ታቦት፣ ከሚዛን ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ሁለት ታቦታት፣ ከሚዛን ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሁለት ታቦታት፣ ከሚዛን ማረሚያ ቤት ቅዱስ ሚካኤል  አንድ ታቦት በተለምዶ ኮሶኮል ወደሚባለው ጥምቀተ ባህር ጉዟቸውን የሚያደርጉ ሲሆን ፣ በአማን ክፍለ ከተማ ደግሞ ከደብረ መድኀኒት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ታቦታት፣ ከቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አንድ ታቦት፣ ከደብረ ሰላም ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ሁለት ታቦታት፣ ከዛሚቃ አባ ሳሙኤል ገዳም አንድ ታቦት፣ ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን አንድ ታቦት ፣ ከመንበረ ንግስት ቅድስት ቁስቋም ቤተ ክርስቲያን አንድ ታቦት ወደ አማን ጥምቀተ ባህር እንደሚዎጡና በአጠቃላይ ቁጥራቸው አስራ አራት የሚሆኑ ታቦታት ወደ ሁለቱ ጥምቀተ ባህር እንደሚያመሩ መረጃዎች ይጠቁማሉ::
ወጣቶች እንደተለመደው ዘንድሮም ሕዝቡ በግፍያ እንዳይጎዳና መጨናነቅ እንዳይፈጠር ታቦታት በሚያልፉበት መንገድ ላይ ምንጣፍ እየተሸከሙ በማንጠፍ ባለፉት ጊዜያት ያሳዩት የነበረው አገልግሎት ዘንድሮም ለቤተ ክርስቲያናቸውና ለእምነታቸው ያላቸውን ፍቅርና ክብር ለማሳየት ተዘጋጅተዋል፡፡ /ከሚዛን ማዕከል ሚድያ ክፍል/

የጥምቀት በዓል ዝግጅት በወልድያ
በወልድያ ከተማ የጥምቀት በዓል ከዋዜማው ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በድምቀት እንደሚከበር ተገለፀ፡፡
የሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ኃላፊና የወልድያ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል ስጦታው ሞላ የበዓሉን አከባበር አስመልክተው በሰጡት መረጃ በከተማው ውስጥ ያሉ አድባራትና በዙሪያው የገጠር አብያተ ክርስቲያናት የከተራ በዓሉን በወልድያ ታቦት ማደሪያ በአንድ ላይ ያከብራሉ፡፡
በከተማውና በዙሪያው ያሉ የ10 አብያተ ክርስቲያናት 15 ታቦታት ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ ወደ ታቦት ማደሪያው እንደሚንቀሳቀሱና ምዕመናንም በሰዓቱ ተገኝተው የሚከብሩ ሲሆን፤ ምዕመናን በዓሉን በሰላምና በፍቅር እንዲሁም ጧሪ የሌላችውን አረጋዊያንና አሳዳጊ የሌላቸው ህፃናትን በመርዳት እንድያከብሩ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
ከባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት ወዲህ በበዓላት አከባበር ወጣቱ እያሳየው ያለው ተሳትፎና ሥነ-ስርዓት እጅግ የሚያስደስት በመሆኑ በዚህ ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሚጠበቅ ሲሆን፤
ታቦታቱ ጉዞ የሚያደርጉበትን ጎዳናዎች በማፅዳት፣ ሠንደቅ ዓላማዎችን በመስቀል፣ ምንጣፍ በማንጠፍና ቄጤማ በመጎዝጎዝ ለእግዚአብሔር ያላቸውን ፍቅር እየገለፁ ይገኛሉ፡፡ በዓሉን ለማክበር ሰ/ት/ቤቶች፣ ማኅበራትና ወጣቶች ዝግጅት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በዕለቱ መዝሙር፣ ዕለቱን የተመለከተ ስብከተ ወንጌልና ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች ከተካሄዱ በኋላ 11፡30 ላይ ታቦታቱ ወደ ተዘጋጀላቸው ማረፊያ ይገባሉ፡፡ በዚሁ የዋዜማ በዓሉ ፍፃሜ ይሆናል፡፡ /ወልድያ ማዕከል  ሚድያ ክፍል/