ቅዱስ ፓትርያርኩ ምእመናን ለመዋቅራዊ ለውጡ ድጋፍ እንዲሰጡ ጠየቁ

 

 

ጥር 9/2006 ዓ.ም.

 

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጥር 7 ቀን 2006 ዓ.ም. የቅድስት ሥላሴን ዓመታዊ የንግሥ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በከበረበት ወቅት ቤተ ክርስቲያኗ በለውጥ ላይ በመሆኗ ምእመናንና አገልጋይ ካህናት ለውጡን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲተባበሩ ጥሪ አስተላለፉ፡፡

ቅዱስነታቸው የዕለቱን በዓል አስመልከተው ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርት ካስተማሩ በኋላ በትምህርታቸው ማጠቃለያም ቤተ ክርስቲያን የምእመናንንና የካህናት በመሆኗ የሁለቱ አንድነት አገልግሎቱን የተሟላና የሠመረ እንደሚያደርገው ገልጸው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተንሰራፍቶ ያለው ተገቢ ያልሆነ አሠራር መስተካከል እንደሚኖርበት አሳስበዋል፡፡

 

ቅዱስነታቸው በተደጋጋሚ ተገቢ ያልሆነ አሠራር መኖሩ እየተነገረ ዝም ብሎ ማለፍ ስለማይገባ የችግሩን አሳሳቢነት ግምት ውስጥ በማስገባት የቤተ ክርስቲያኗን አሠራርና መዋቅር በተመለከተ ለውጥ ላይ ስለምትገኝ ምእመናንም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል፡፡አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል፡፡