ከሰባት ሺህ በላይ በሌላ እምነት የነበሩ ሰዎች ተጠመቁ

ጥቅምት 8 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ

 

በደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ባሳለፍነው የ2004 ዓ.ም. ቁጥራቸው ሰባት ሺህ አንድ መቶ አርባ አንድ ሰዎች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ሃይማኖት በመቀበል መጠመቃቸውን የሀገረ ስብከቱ ሪፓርት አመለከተ፡፡

 

የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ትጉሀን ወንድወሰን ገ/ሥላሌ ለ31ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ባቀረቡት ሪፓርት የሕግ ታሪሚዎች በተለያዩ ቤተ እምነቶች ውስጥ ከነበሩ ሰዎች መካከል ሰባት ሺህ አንድ መቶ አርባ አንድ ሰዎች ሊጠመቁ ችለዋል” ብለዋል፡፡