የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የከሰዓት በኋላ ውሎ

ጥቅምት 6 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ


31ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከዛሬው የከሰዓት በኋላ መርሐ ግብሩ ላይ የትግራይ ማእከላዊ ዞን፣ /የአክሱም/፣ የሲዳሞ፣ የሰሜን ጎንደር፣ የምሥራቅ ሐረርጌ፣ የጅማ ዞን፣ የመቀሌ ዞን፣ የኢሊባቡር፣ የድሬዳዋ፣ የጋሞ ጎፋ፣ የሰሜን ወሎ፣ የባሌ፣ የደቡብ ጎንደር የምሥራቅ ወለጋ፣ የአርሲ፣ የትግራይ ምሥራቅ ዞን /የአዲግራት/፣ አህጉረ ስብከቶች የበጀት ዓመቱን ሪፓርታቸውን በሥራ አስኪያጆቻቸው አማካኝነት ለጉባኤው አቅርበው መርሐ ግብሩ በጸሎት ተፈጽሟል፡፡ 31ኛው መደበኛ ጉባኤ ነገ ጧት 2፡30 ላይ ይቀጥላል፡፡