ማኅበሩ በሬድዮ ማሰራጫው ላይ የአየር ሞገድ ለውጥ አደረገ፡፡

ጥቅምት 8 ቀን 2005 ዓ.ም.

በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ

በማኅበረ ቅዱሳን ኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ የሬድዮና ቴሌቪዥን ዝግጅት ክፍል ዘወትር አርብ ከምሽቱ 3፡30 እስከ 4፡30 ያሰራጭ የነበረውን ትምህርታዊ የሬድዮ ዝግጅት የአየር ሞገድ ለውጥ በማድረግ በ19 ሜትር ባንድ 15335 ኪሎ ኸርዝ አጭር ሞገድ አማካኝነት በተሻለ ጥራት ከጥቅምት 9/2005 ዓ.ም. ጀምሮ ማስደመጥ እንደሚጀምር በማኅበረ ቅዱሳን የሬድዮና ቴሌቭዥን ፕሮግራም አስተባባሪ ዲ/ን ሄኖክ ኀይሌ አስታወቁ፡፡ እንዲሁም ከዚህ ቀደም የተላለፉ መርሐ ግብሮችን www.dtradio.org ላይ መከታተል እንደሚቻል አያይዘው ገልጸዋል፡፡