ቅዱስ ፓትርያርኩ ምእመናን ለመዋቅራዊ ለውጡ ድጋፍ እንዲሰጡ ጠየቁ
ጥር 9/2006 ዓ.ም.
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጥር 7 ቀን 2006 ዓ.ም. የቅድስት ሥላሴን ዓመታዊ የንግሥ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በከበረበት ወቅት ቤተ ክርስቲያኗ በለውጥ ላይ በመሆኗ ምእመናንና አገልጋይ ካህናት ለውጡን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲተባበሩ ጥሪ አስተላለፉ፡፡