ሰዋስወ ግእዝ (ክፍል ሁለት)

ሰኔ 19 ቀን 2005 ዓ.ም.

በመ/ት ኑኀሚን ዋቅጅራ

 ፩.፪. የግእዝ ፊደላት አካፋፈል

መጀመሪያ ጊዜ ለሄኖስ በጸፍጸፈ ሰማይ (በሰማይ ገበታነት) የተገለጹለት ፊደላት አሁን በፊደል ገበታ ላይ በቅደም ተከተል እንደምናያቸው ሳይሆን ከዚህ በተለየ መልኩ ተዘበራርቀውና የእብራይስጡን የቋንቋ ስልት ይዘው ነው እነሱም አሌፋት በመባል የራሳቸው ስያሜ ነበራቸው

አ – አሌፍ                           ሐ – ሔት                            ሠ – ሣምኬት

በ – ቤት                            ጠ – ጤት                            ጸ – ጻዴ

ገ – ጋሜል                          የ – ዮድ                              ፈ – ፌ

ደ – ዳሌጥ                          ከ – ካፍ                              ዐ – ዔ

ሀ – ሄ                               ለ – ላሜድ                           ቀ – ቆፍ

ወ – ዋው                           መ – ሜም                           ተ – ታው

ዘ – ዛይ                             ነ – ኖን                                ረ – ሬስ

በማለት በእብራይስጡ አጠራር ይጠሯቸው ነበር፤ ነገር ግን እነዚህን የግእዝ ፊደላት በኢትዮጵያ ቀዳማዊ ጳጳስ በአቡነ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን የግእዝ ፊደላትን አሻሽለው አሁን በፊደል ገበታ ላይ የምናያቸውን በቅደም ተከተል ከማስቀመጣቸው በፊት ያሉት ፊደላት፡-

 

ቀዳማዊ የግእዝ ፊደላት በሚል ስያሜ የሚጠሩ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ከሀ – ጀምሮ በዝርዝር በቀደም ተከተል የምናያቸው ፊደላት ደግሞ ደኀራዊ የግእዝ ፊደላት ብለን በሁለት እንመለከታቸዋለን፡፡

 

፩.፫. ቀዳማዊና ደኀራዊ የግእዝ ፊደላት፣-

፩. ቀዳማዊ የግእዝ ፊደላት የምንላቸው በአሁኑ ጊዜ በፊደል ገበታ ላይ አ፣ በ፣ ገ፣ ደ…./አቡጊዳ/ በማለት የምንጠራው የፊደል አቀማመጥ ነው እነዚህ ፊደላት በመነሻ ፊደል ብቻ ነበር የተጻፉት፡፡

 

                                      ቀዳማዊ የግእዝ ፊደላት

                                      

                                     

                                       

                                     

                                      

                                     

                                      

                                     

                   

በዚህ ዓይነት አቀማመጥ በነጠላ በግእዝ ፊደሉ ብቻ ነበር የተቀመጡት ከዚህ በኋላ ግን በእነዚህ ፊደላት ላይ የተወሰኑ ቅጥያዎችን በመጨመር በመጀመሪያ ደረጃ እነዚህን ፊደላት ወደ ሰባት የፊደላት አዘራዘር በመለወጥ ለእያንዳንዱ ፊደል የተለያዩ ቅርጽና ድምጽን በመፍጠር ፊደላቱ ወደ ሰባት ድምጽ /ሥልት/ ተለውጠው እንዲጻፉ በወቅቱ ከነበሩት ሊቃውንት አባቶች ጋር በመነጋገር የፊደላቱን ቅርጽ አዘጋጅተውልናል፡፡


 

 

ግእዝ

ካዕብ

ሣልስ

ራብዕ

ሐምስ

ሳድስ

ሳብዕ

፲፩

፲፪

፲፫

፲፬

፲፭

፲፮

፲፯

፲፰

 

 

ግእዝ

ካዕብ

ሣልስ

ራብዕ

ሐምስ

ሳድስ

ሳብዕ

፲፱

፳፩

፳፪

፳፫

፳፬

፳፭

፳፮

 

ደሐራዊ የግእዝ (የኢትዮጵያ) ፊደላት አጻጻፍ

 

ግእዝ

ካዕብ

ሣልስ

ራብዕ

ሐምስ

ሳድስ

ሳብዕ

፲፩

፲፪

፲፫

፲፬

፲፭

፲፮

፲፯

፲፰

፲፱

፳፩

፳፪

፳፫

፳፬

፳፭

፳፮

 

የግእዝ ቋንቋ እንደ ሌሎች ቋንቋዎች እራሱን የቻለ ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ የሚነገር ጥንታዊ ቋንቋ ነው፡፡ አንድን ቋንቋ እንደ ቋንቋ ከሚያስቆጥሩት መሠረታዊ ነገሮች አንዱ እና ዋንኛው የራሱ የሆኑ ፊደላት ሲኖሩት እና የራሱን የአነጋገር ሥርዓት ተከትሎ መሄድ ሲችል ነው፡፡ ይህም በመሆኑ በዛሬ አምዳችን ስለ ግእዝ ቋንቋ ፊደላት ብዛትና የፊደላቱንም ስያሜ ትርጒም እንመለከታለን፡፡

  1. የግእዝ ፊደላት አጠቃላይ ብዛት ፳፮ (26) ነው፡፡
  2. የግእዝ ፊደላት በሰባት የአዘራዘር ስልት ይዘረዘራሉ፡፡
  3. የግእዝ ፊደላት ብዛት ከነ አዘራዘራቸው ፻፹፪ (182) ናቸው፡፡
  4. ይህም ማለት እየአንዳንዱ ፊደል በሰባት ሥልት ስለሚዘረዘር ነው፡፡

ምሳሌ. ሀ. ግእዝ ሁ. ካዕብ ሂ. ሣልስ ሃ. ራብዕ ሄ.ሐምስ ህ.ሣድስ ሆ. ሣብእ ከፊደል ሀ እስከ ፐ ያሉት ፊደላት በዚህ ዓይነት መንገድ ይዘረዘራሉ፡፡

 

በፊደል ገበታ ላይ የምናገኛቸው የፊደላት ብዛት አጠቃላይ ፴፫ (33) ሲሆኑ ቀሪዎቹ ፯ (ሰባት) ፊደላት የአማርኛ ፊደላት በመባል ይጠራሉ፡፡ እነዚህን ፊደላት ከነ አዘራዘራቸው በሌላ ጊዜ እናያቸዋለን፡፡ ለዛሬ ፳፮ (26)ቱን የግእዝ ፊደላት በቅደም ተከተል ከነትርጒማቸው እንመለከታለን፡፡

 ፩.   ሀ- ብሂል ሀልዎቱ ለአብ እም ቅድመ ዓለም፡፡

   ሀ- ማለት የአብ አኗኗሩ ከዓለም በፊት ነው፡፡

  ፪.  ለ- ብሂል- ለብሰ ሥጋ እምድንግል፡፡

   ለ. ማለት- ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ሥጋን ለበሰ፡፡

  ፫. ሐ. ብሂል ሐመ ወሞተ ወተቀብረ፡፡

  ሐ.ማለት ክርስቶስ ታመመ፣ ሞተ፣ ተቀበረ፡፡

  ፬.  መ. ብሂል መንክር ግብሩ ለእግዚአብሔር፡፡

   መ-ማለት የእግዚአብሔር ሥራው ድንቅ ነው

  ፭. ሠ- ብሂል ሠረቀ በሥጋ፡፡

    ሠ- ማለት ጌታ በሥጋ ተወለደ (ተገለጠ)፡፡

  ፮.  ረ- ብሂል ረግዓት ምድር በቃሉ፡፡

   ረ- ማለት ምድር በቃሉ ረጋች (ጸናች)፡፡

  ፯.  ሰ- ብሂል ሰብአ ኮነ እግዚእነ፡፡

    ሰ- ማለት ጌታችን ሰው ሆነ፡፡

    ፰. ቀ- ብሂል ቀዳሚሁ ቃል፡፡

   ቀ- ማለት በመጀመሪያ ቃል ነበር፡፡

   ፱.…….    በ- ብሂል በትኅትናሁ ወረደ እግዚእነ፡፡

   በ- ማለት ጌታችን በትሕትናው ወደኛ ወረደ (ተወለደ)፡፡

        ፲.  ተ- ብሂል ተሰብአ ወተሰገወ፡፡

        ተ- ማለት ጌታችን ሰው ሆነ፡፡

        ፲፩ . ኀ- ብሂል ኀያል እግዚአብሔር፡፡

        ኀ- ማለት እግዚአብሔር ኀያል ነው፡፡

        ፲፪.  ነ- ብሂል ነሥአ ደዌነ ወፆረ ሕማመነ፡፡

 ነ- ማለት ጌታችን ደዌያችንን ያዘልን ሕመማችንን ተሸከመልን

        ፲፫.  አ- ብሂል አአኲቶ ወእሴብሖ ለእግዚአበሔር አቀድም (አእኲቶቶ ለእግዚአብሔር)

                    አ- ማለት እግዚአብሔርን በፍጹም ልቤ አመሰግነዋለሁ (እግዚአብሔርን ማመስገንን አስቀድማለሁ)፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

 

ይቆየን