በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ -  ማኅበረ ቅዱሳን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ማኅበሩ
    • ማእከላት
      • ሰሜን አሜሪካ
      • አውሮፓ
      • ሩቅ ምሥራቅ
      • ደቡባዊ አፍሪካ
      • የካናዳ ማእከል
      • አዲስ አበባ ማእከል
        • የወርሃዊ አስተዋጽኦ መሰብሰቢያ
    • ኅትመት እና ሚዲያ
      • ሐመር እና ስምዐ ጽድቅ
      • ማኅበረ ቅዱሳን ቲቪ
      • የማኅበረ ቅዱሳን ዩቲዉብ
      • መጽሔተ ተልዕኮ
      • ማእከለ ሥዕላት
        • ካሜራው ምን ይላል
        • የቅዱሳት ሥዕላት ማኅደር
  • ትምህርቶች
    • የርቀት ትምህርት
    • ስብከት
    • መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች
  • ግቢ ጉባኤ
  • ሌሎች ድረ ገጾች
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ ልዩ ጽ/ቤት ድረ ገጽ
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ድረ ገጽ
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ድረ ገጽ
  • ቋንቋ
    • አማርኛ
    • ትግርኛ
    • ወላይትኛ
    • ሲዳምኛ
    • Affan Oromo
    • English
  • ያግኙን
  • Click to open the search input field Click to open the search input field Search
  • Menu Menu

ጥምቀት

You are here: Home1 / ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን2 / ጥምቀት

ጥምቀት

ጥር ፱ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም

የሰው ልጅ ሕገ እግዚአብሔርን በመተላለፉና ለኃጢአት ተገዢ በመሆኑ ንጽሕት ነፍሱ አደፈች፤ ረከሰችም፤ በኃጢአቱም ምክንያት ከአምላኩ ተጣላ፤ ወደ ምድርም ተጣለ፤ ምድርም በእርሱ የተነሣ ተረገመች፤ እሾህና አሜከላንም አበቀለች፡፡ እርሱም ለብዙ ዘመን አዝኖና በሥቃይ ኖረ፡፡

ቸርነቱ የማይልቅ መሐሪና ይቅር ባይ አምላካችን እግዚአብሔር በኅዘኑ አዝኖና ሥቃዩን ተመልክቶ ለእርሱ፤ ስለ እርሱ መከራና ሥቃይ ይቀበልለት ዘንድ ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ሊያድነው በገባለት ቃል መሠረት ተፈጸመ፡፡ ከዚያም በኋላ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዮርዳኖስን ብርህት ማኅፀን እንድትሆን፣ ምእመናንም ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ፣ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ዳግም ተወልደው መንግሥተ ሰማያት እንዲገቡ  እንደዚሁም ሥርዓተ ጥምቀትን ለማስተማርና አብነት ለመሆን በጥር ዐሥራ አንድ ቀን ተጠምቋልና ይህችን የተከበረች ቀን ሕዝበ ክርስቲያን ያከብር ዘንድ ይገባል፡፡

በመጽሐፍ ቅዱስም ‹‹ጥሩ ውኃንም እረጭባችኋለሁ፤ እናንተም ከርኵሰታችሁ ሁሉ ትጠራላችሁ›› ተብሎ አስቀድሞ በተነገረው መሠረት ጌታችን በውኃ ተጠመቀ፡፡ የዚህም ምክንያት ሊቀውንተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚያስረዱት ውኃ ለሁሉ አስፈላጊ በመሆኑና ያለ ውኃ መኖር የሚችል ባለመሆኑ ያለ ጥምቅት ደግሞ ያለ ጥምቀት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አይቻልምና ጥምቀትም ለሁሉም የሚገባ ሥርዓት ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር ውኃ መልክ ያሳያል፤ መልክ ያለመልማል (ያጠራል)፡፡ ጥምቀትም መልክዐ ነፍስን ያሳያል፤ መልክዐ ነፍስን ያለመልማልና (ያጠራልና)፡፡ (ሕዝ.፴፮፥፳፭)

በዘመነ ሥጋዌ ‹‹ጌታችን  መድኃኒታችን  ኢየሱስ  ክርስቶስ  በዮሐንስ  እጅ  ይጠመቅ  ዘንድ  ከገሊላ  ወደ ዮርዳኖስ መጣ›› (ማቴ.፫፥፲፫፣ማር.፩፥፱፣ሉቃ.፫፥፳፩፣ዮሐ.፩፥፴፪)፡፡ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ግን አገልጋይ በጌታው እጅ ይጠመቃል እንጂ ጌታ በአገልጋዩ አይጠመቅም፤ ‹‹እኔ በእንተ ልጠመቅ እሻለሁ፤ አንተ ወደ እኔ ትመጣለህን?›› ብሎ አይሆንም አለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም መልሶ ‹‹አሁንስ ተው፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ ልንፈጽም ይገባናልና›› አለው፡፡ ከዚህም በኋላ ተወው፡ ጌታችን ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆ ሰማይም ተከፈተለት፤ የእግዚአብሔርም መንፈስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ሲቀመጥ አየ፤ እነሆም ‹‹በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው››የሚል ድምጽ ተሰማ፡፡(ማቴ.፫፥፲፫-፲፯)

መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል መውረዱም ምሥጢር አለው፡፡ ርግብ ኃዳጊተ በቀል ናት፤ መንፈስ ቅዱስም ኃዳጌ በቀል ነውና፡፡ ርግብ በኖኅ ጊዜ ‹‹ሐጸ ማየ አይኅ ነትገ ማየ አይኅ፤ የጥፋት ውኀ ጎደለ›› ስትል ቆጽለ ዕፀ ዘይት ይዛ ተገኝታለች፡፡ መንፈስ ቅዱስም ተስፋ መስቀልን ያበሥራልና፡፡

እኛም የሐዲስ ኪዳን ሕዝቦች ይህን ምሥጢር በመረዳት፣ መከራ መስቀሉን በመሸከምና እምነት በመጽናት እንድኖንር አስፈላጊ በመሆኑ ነገረ ድኅነቱን በመረዳት በልደቱ እንደዘከርነው ሁሉ በጥምቀቱም እንዲሁ እናደረግ ዘንድ ይገባል፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተጠመቀውም በሠላሳ ዓመቱ ነው (ሉቃ. ፫፥፳፫)፡፡ በሠላሳ ዓመቱ የተጠመቀበት ምሥጢርም አዳም የሠላሳ ዓመት፤ ሔዋን የዐሥራ አምስት ዓመት ሰው ሆነው ተፈጥረው አዳም በዐርባ ቀን፣ ሔዋን በሰማንያ ቀን ከሥላሴ የተቀበሉትን ልጅነት በምክረ ከይሲ ዕፀ በለስን በልተው አስወስደው ነበረና በሠላሳ ዓመቱ ተጠምቆ መልሶላቸዋል፡፡ በሠላሳ ዓመት የመጠመቁ ምሥጢር ይህ ሲሆን እኛ ዛሬ ወንዶች በዐርባ ቀን፣ ሴቶች በሰማንያ ቀን በዕለተ ዓርብ ከቀኝ ጎኑ በፈሰሰው ማየ ገቦ ተጠምቀን ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ሁለተኛ የምንወለድበት ምክንያትም አዳም በዐርባ ቀኑ፣ ሔዋን በሰማንያ ቀኗ ከሥላሴ ያገኙትን ልጅነት መሠረት በማድረግ ነው /ኩፋ. ፬፥፱/፡፡ የምንጠመቀውም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ነው፡፡  ‹‹ወእንዘ ታጠምቅመው በሉ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ፤ ስታጠምቋቸውም በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው፤›› እንዲል(ማቴ. ፳፰፥፲፱)፡፡

በአሁኑ ጊዜም ታቦታቱን ወደ ጥምቀተ ባሕር በማውረድ በዓለ ጥምቀቱን ለሚያከብሩ ክርስቲያኖች በሙሉ ከታቦታቱ ሁለት ሺህ ክንድ ርቀው መከተል እንዲገባቸው በመጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ተብሎ ተገልጿል፤ ‹‹ሕዝቡን የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያን ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሠፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት፡፡ በእናንተና በታቦቱ መካከል ያለው ርቀት በስፍር ሁለት ሺህ ክንድ ይሁን፡፡ በዚህ መንገድ በፊት አልሄዳችሁበትና፤ የምትሄዱበትን መንገድ እንድታውቁ ወደ ታቦቱ አቅርቡ፡፡›› (ኢያ.፫፥፩-፲፯)

ታቦታቱ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርደው ለማደራቸው መነሻ ይህ ትምህርት ነው፡፡ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀትም ከተጠመቀበት ከ፴ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በየዓመቱ ጥር ፲፩ ቀን ሃይማኖታዊ ሥርዓቱን በጠበቀ መልኩ ሲከበር ይኖራል፡፡

ከበዓለ ጥምቀቱ ረድኤት፣ በረከት ይክፈለን፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

Search Search

አዳዲስ ጽሑፎች

  • በዓለ ደብረ ምጥማቅ
  • የቅዱስ ያሬድን ትሩፋት በዓለም የዕውቀት መድረክ ላይ ለማስተዋወቅ የምርምር ማእከላትን የማቋቋምና የዲጂታል ቅርስ አያያዝ ዘዴዎችን የመተግበር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ።
  • አውስትራሊያ ማእከል ዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር አካሄደ
  • የደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም የ፬ቱ ትርጓሜ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ።
  • ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ መሳካት ያላቸው ሚና
  •                  “እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።” (መዝ ፵፮ ፥፭)
  • “ሕያው ዜማከ ወሕያው ድርሳንከ” በሚል መሪ ቃል የዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር እንደሚከናወን የዜማና ኪነ ጥበባት ማእከል አስታወቀ
  • በማኅበረ ቅዱሳን ወሊሶ ማእከል ያስተማራቸውን ዲያቆናት ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ በማድረግ አስመረቀ
  • በቤተ ክርስቲያናችን ከላይ እስከ ታች ወጥ የሆነ የሰው ሀብት አስተዳደር መመሪያ ያስፈልጋል ” ከሐመር መጽሔት ” የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ዐምድ ግንቦት 2018 ዓ.ም
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • “ባለፉት 34 ዓመታት በአገልግሎት የራቁትን ማቅረብ፣ የቀረቡትን ደግሞ ለንስሐ ሕይወት ለእግዚአብሔር መንግስት ማብቃት ትልቅ ነገር ነው።” ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ጅግጅጋና የምሥራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
  • ማኅበረ ቅዱሳን 34ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አከበረ
  •  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
  • ፻፴፬ ኛው የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልአተ ጉባኤ ላይ በቅዱስነታቸው የተላለፈ አባታዊ መልእክት
  • በአሜሪካ ቦስተን ከተማ የበገና እና የመሰንቆ ተማሪዎች ተመረቁ

የጽሑፎች ማውጫ – በወራት

© Mahibere Kidusan - All Rights Reserved. Website by MK-IT
  • Link to Facebook
Link to: በዓለ ጥምቀት Link to: በዓለ ጥምቀት በዓለ ጥምቀት Link to: ‹‹በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር ሠርግ ሆነ፤ ውኃውንም ወደ ወይንነት ለወጠው›› (ዮሐ. ፪፥፩-፲፩) Link to: ‹‹በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር ሠርግ ሆነ፤ ውኃውንም ወደ ወይንነት ለወጠው›› (ዮሐ. ፪፥፩-፲፩) ‹‹በገሊላ አውራጃ በቃና መንደር ሠርግ ሆነ፤ ውኃውንም...
Scroll to top