በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/በሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ -  ማኅበረ ቅዱሳን
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ማኅበሩ
    • ማእከላት
      • ሰሜን አሜሪካ
      • አውሮፓ
      • ሩቅ ምሥራቅ
      • ደቡባዊ አፍሪካ
      • የካናዳ ማእከል
      • አዲስ አበባ ማእከል
        • የወርሃዊ አስተዋጽኦ መሰብሰቢያ
    • ኅትመት እና ሚዲያ
      • ሐመር እና ስምዐ ጽድቅ
      • ማኅበረ ቅዱሳን ቲቪ
      • የማኅበረ ቅዱሳን ዩቲዉብ
      • መጽሔተ ተልዕኮ
      • ማእከለ ሥዕላት
        • ካሜራው ምን ይላል
        • የቅዱሳት ሥዕላት ማኅደር
  • ትምህርቶች
    • የርቀት ትምህርት
    • ስብከት
    • መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርቶች
  • ግቢ ጉባኤ
  • ሌሎች ድረ ገጾች
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ የብፁዕ ወቅዱስ ልዩ ጽ/ቤት ድረ ገጽ
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ድረ ገጽ
    • በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ድረ ገጽ
  • ቋንቋ
    • አማርኛ
    • ትግርኛ
    • ወላይትኛ
    • ሲዳምኛ
    • Affan Oromo
    • English
  • ያግኙን
  • Click to open the search input field Click to open the search input field Search
  • Menu Menu

ሦስቱ ነገሥታት

You are here: Home1 / ክርስቲያናዊ ሕይወትና ሥነ ምግባር2 / ሦስቱ ነገሥታት

ሦስቱ ነገሥታት

ዲያቆን ተስፋዬ ቻይ

ታኅሣሥ ፳፰ ቀን ፳፻፲፬ ዓ.ም

ኢየሩሳሌም ከተማ ከወትሮው በተለየ መልኩ የፍርሃት ድባብ ተንጸባርቆባታል፤ በንጉሥ ሄሮድስ ቤተ መንግሥት ዙሪያ በሠራዊቱና በቤተ መንግሥቱ የቅርብ ሰዎች የሰሞኑ ወሬ የሦስቱ ነገሥታት ጉዳይ ነው፡፡ ከሩቅ ምሥራቅ ሠራዊቶቻቸውን አስከትለው የመጡት  ማንቱሲማር፣ በዲዳስፋ፣ እና ሜልኩ የተባሉ ነገሥታት በእስራኤል ምድር መምጣታቸው ብቻ ሳይሆን ተወልዷል ለተባለው ንጉሥ እጅ መንሻ ለመስጠት እንደመጡ መናገራቸው ንጉሥ ሄሮድስን ቅር አሰኝቶታል፤ ፍርሃት በልቡ እንዲነግሥም አድርጎታል፡፡ (ማቴዎስ ወንጌል አንድምታ ትርጓሜ ፪፥፫)

ንጉሥ ሄሮድስ ይህንን ዜና ከሰማ በኋላ ለዓይኖቹ ሽፋሽፍት በቂ እንቅልፍን፣ ለጀርባው በቂ ዕረፍትን ከሰጠ ቀናቶች ተቆጥረዋል፡፡ ነገሥታቱ ከሩቅ ምሥራቅ ኮከብ እየመራቸው ከንጉሥ ሄሮድስ ቤተ መንግሥት ከገቡ ጊዜ አንሥቶ የተወለደውን ንጉሥ አግኝተው ከአባቶቻቸው በአደራ የተረከቡትን ሥጦታ ለመስጠት ንጉሡንም ለማየት እጅግ ጓጉተዋል፡፡ ከማረፊያ ቤት እንዲቀመጡ ከተደረገ በኋላ ንጉሥ ሄሮድስ መምህራራን አስጠርቶ በእስራኤል ሀገር ይወለዳል ስለተባለው ንጉሥ የተነገሩ ትንቢቶች ካሉና የትውልድ ቦታውን እንዲነግሩት ጠየቃቸው፤ ሊቃውንቱ፣ ከአስፈሪውና ከጨካኙ ንጉሥ ሄሮድስ ዘንድ ቀርበው የተጠየቁትን ጥያቄ ለመመለስ በመጻሕፍት የተጻፉትን ማስታወስ ጀመሩ፤ ከዚያም ስለሚወለደው ንጉሥ በነቢዩ ሚክያስ ‹‹አንቺ ቤተ ልሔም የይሁዳ ምድር ከይሁዳ ምድር፣ ከይሁዳ ገዢዎች ከቶ አታንሺም፤ ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ  መስፍን ከአንቺ ይወጣልና ተብሎ በነቢይ እንዲህ ተጽፎአልና በይሁዳ ቤተ ልሔም ነው›› አሉት፡፡  (ማቴዎስ ወንጌል አንድምታ ትርጓሜ ፪፥፮)

ንጉሥ ሄሮድስ ሦስቱን ነገሥታት ከእንግዳ ማረፊያ ቤት አስጠርቶ ‹‹… ይወለዳል የተባለው ንጉሥ በቤተ ልሔም ነው፤ ስለዚህ ወደዚያ ሂድ! ነገር ግን ካገኛችሁት ለእኔም ንገሩኝ፤ እኔም እሰግድለታለው›› አለ… (ማቴ.፪፥፯-፰) ሦስቱ ነገሥታት አመስግነው በተነገራቸው መሠረት ጉዞ ወደ ቤተ ልሔም አደረጉ…፤ በጉዟቸው ወቅት ከሀገራቸው ሲመጡ በሰማይ እያበራ ይመራቸው የነበረው የሚያበራ ኮከብ ዳግመኛ ታያቸው፤ ከዚያም አቅጣጫውን እየመራ ወደ ቤተ ልሔም ወሰዳቸው …. ፤ ቤተ ልሔም ከተማ ትሕትና በአካል ገዝፎ የታየባት ድንቅ ሥፍራ ናት፡፡ ከኢየሩሳሌም ከተማ ስምንት ኪሎ ሜትር ርቃ በስተደቡብ የምትገኝ ከተማ ናት፤ ቤተ ልሔም የቀድሞ ስሟ ኤፍራታ ይባላል፤ ጸዋሪተ ፍሬ (ፍሬን የያዘች) ማለት ሲሆን ቤተ ልሔም ማለት ደግሞ የእንጀራ ቤት ማለት ነው፤ እውነትም የእንጀራ ቤት ‹‹.. የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ከቶ አይራብም…›› በማለት እንደተናገረው፤ ያውም በልተው የማይራቡት የሕይወት እንጀራ መድኅነ ዓለም ክርስቶስ የተወለደባት ቅዱስ ሥፍራ፡፡ በቤተ ልሔም ንጉሥ ዳዊት ተወልዶባታል፤ ያዕቆብ ሚስቱ ራሔልን ባረፈች ጊዜ የቀበራት በዚሁ ሥፍራ ነው፡፡ (ዮሐ.፮፥፴፭)

ከተማዋ መግቢያ ሲደርሱ ከተማዋ በብርሃን ተሞልታለች፡፡ ልብን በሐሤት የሚሞላ ልዩ ድባብ ይንጸባረቅበታል፤ ኮከቡ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ከተወለደበት በኤፍራታ ዋሻ ከእንስሳቱ ማደሪያ አመለከታቸውና ተሠወረ፤ ሦስቱ ዕድለኞች ነገሥታት በጽናት ተጉዘው የተወለደውን ንጉሥ በማግኘታቸው እጅግ ተደሰቱ፤ ሕፃኑን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከእመቤታችን ከንጽሕተ ንጹሓን ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር አገኙት፤ ወላዲተ አምላክ ድንግል ማርያም ፍጥረታቱን በቸርነቱ የሚመግብን ፈጣሪያችንን ታቅፋው አገኙ፤ እንደገቡም ለነገሥታት ንጉሥ ለክርስቶስ ሰገዱለት፤ ከዚያም ይዘው የመጡትን እጅ መንሻ ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ ሌሎችንም ሥጦታዎች ሰጡት፤ የልባቸው መሻት በመፈጸሙ በጣም ተደሰቱ፤ የእግዚአብሔርም መልአክ በሌሊተ ተገልጾ በመጡበት ሳይሆን በሌላ መንገድ እንዲመለሱ ነገራቸው፤ ሦስቱ ነገሥታት ሲመጡ ረጅም ጊዜ የፈጀባቸውን መንገድ በአጭር ቀን ተመለሱ፤ ሲመጡ ‹‹የተወለደው ንጉሥ የታለ›› እያሉ ነበር፤ ሲመለሱ ‹‹አገኘነው›› እያሉ ተመለሱ፤ ሲመጡ ምድራዊ ንጉሥ መስሏቸው ነበር፤ የሰማይና የምድር ፈጣሪ ነገሥታትን የሚሾም ንጉሥ እንደሆነ አምነው ተመለሱ፡፡

ስብሐት ለእግዚአብሔር

ወለወላዲቱ ድንግል

ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!!!

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

Search Search

አዳዲስ ጽሑፎች

  • በዓለ ደብረ ምጥማቅ
  • የቅዱስ ያሬድን ትሩፋት በዓለም የዕውቀት መድረክ ላይ ለማስተዋወቅ የምርምር ማእከላትን የማቋቋምና የዲጂታል ቅርስ አያያዝ ዘዴዎችን የመተግበር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ።
  • አውስትራሊያ ማእከል ዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር አካሄደ
  • የደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም የ፬ቱ ትርጓሜ መጻሕፍት ምስክር ጉባኤ ቤት ያስተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ።
  • ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ መሳካት ያላቸው ሚና
  •                  “እግዚአብሔር በመለከት ድምፅ ዐረገ።” (መዝ ፵፮ ፥፭)
  • “ሕያው ዜማከ ወሕያው ድርሳንከ” በሚል መሪ ቃል የዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር እንደሚከናወን የዜማና ኪነ ጥበባት ማእከል አስታወቀ
  • በማኅበረ ቅዱሳን ወሊሶ ማእከል ያስተማራቸውን ዲያቆናት ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ በማድረግ አስመረቀ
  • በቤተ ክርስቲያናችን ከላይ እስከ ታች ወጥ የሆነ የሰው ሀብት አስተዳደር መመሪያ ያስፈልጋል ” ከሐመር መጽሔት ” የነገዋ ቤተ ክርስቲያን ዐምድ ግንቦት 2018 ዓ.ም
  • ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ
  • “ባለፉት 34 ዓመታት በአገልግሎት የራቁትን ማቅረብ፣ የቀረቡትን ደግሞ ለንስሐ ሕይወት ለእግዚአብሔር መንግስት ማብቃት ትልቅ ነገር ነው።” ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሶማሌ ጅግጅጋና የምሥራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል
  • ማኅበረ ቅዱሳን 34ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አከበረ
  •  በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
  • ፻፴፬ ኛው የቅዱስ ሲኖዶስ መደበኛ ምልአተ ጉባኤ ላይ በቅዱስነታቸው የተላለፈ አባታዊ መልእክት
  • በአሜሪካ ቦስተን ከተማ የበገና እና የመሰንቆ ተማሪዎች ተመረቁ

የጽሑፎች ማውጫ – በወራት

© Mahibere Kidusan - All Rights Reserved. Website by MK-IT
  • Link to Facebook
Link to: አብረን እንዘምር! Link to: አብረን እንዘምር! አብረን እንዘምር! Link to: ‹‹ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ›› (ኤፌ.፭፥፳፪) Link to: ‹‹ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ ተገዙ›› (ኤፌ.፭፥፳፪) ‹‹ሚስቶች ሆይ፥ በጌታ እንደሚገባ ለባሎቻችሁ...
Scroll to top