መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




ለአንድ ወር ያክል ሲሰለጥኑ የቆዩ 28 ተተኪ አመራሮች መመረቃቸው ተገለጸ
ለአንድ ወር ያክል ሲሰለጥኑ የቆዩ 28 ተተኪ አመራሮች መመረቃቸው ተገለጸ ሚያዝያ 20/2018 ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል አባላትና ማስተባበሪያ አገልግሎት ዋና ክፍል ከየካቲት 14 እስከ መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለአንድ ወር ያክል ሲያሠለጥናቸው የቆዩ ተተኪ አመራር ሠልጣኞችን ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም አስመርቋል። በመርሐግብሩ የማእከሉ መዘምራን ያሬዳዊ መዝሙር ያቀረቡ ሲሆን ትምህርተ ወንጌል […]
አሜሪካ አቀፍ የአቡነ ጎርጎርዎስ ተማሪዎች ዓመታዊ ውድድር መካሄዱ ተገለጸ
ፖርትላንድ የአጠቃላይ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ ሚያዝያ ፳/፳፻፲፰ ዓ.ም በአሜርካ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሁለተኛው የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎች የጥያቄና መልስ ውድድር ቅዳሜ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም (April 25, 2026) በችካጎ ከተማ መደረጉን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤቶች አስተዳደር ቦርድ ገልጿል:: ውድድሩ በመጀመሪያ በእያንዳንዱ ትምህርት ቤትና ቀጥሎም በማስተባበሪያ ማእከል ደረጃ በአራት የዕድሜ ክልል ተከፍሎ የተደረገ ሲሆን በአንድ የዕድሜ […]
‹‹ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፤ የጻድቅ መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል›› (መዝሙረ ዳዊት ፻፲፩፥፮)
የምድራዊ ሕይወት ውጣ ውረድን አልፎ፣ የእሾህና አሜኬላዋን ሥቃይ ተቋቁሞ፣ ቀናውን የጽድቅ ጎዳና ተጉዞ፣ ሩጫውን በገድል ጨርሶ፣ በመልካም ፍሬ ዘለዓለማዊ ዕረፍትን የሚያገኝ ሰው ምስጉን ነው፡፡ ቅዱሱ መጽሐፍ ‹‹ዝክረ ጻድቅ ለዓለም ይሄሉ፤ የጻድቅ መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል›› ይለናል፡፡ (መዝሙረ ዳዊት ፻፲፩፥፮)
ጾመ ነነዌ
ምሕረቱ የበዛው አምላካችን የነነዌ ሰዎችን ይቅር እንዳላቸው ሁሉ እኛንም ጸሎታችንን ሰምቶ፣ ልመናችንን ተቀብሎና ጾማችንን አስቦ ምሕረትን ያደርግልን ዘንድ ከክፋት ርቀን፣ ከቂም በቀል ከጥላቻ ነጽተን፣ በበጎነትና በመልካም ምግባር ጾሙን እንጹም!
“እግዚአብሔር ብርሃኔ ነው” ቅዱስ ዑራኤል
በቅዱስ ፈቃዱ ዓለምን የፈጠረው ሁሉን ቻይ አምላካችን እግዚአብሔር መላእክትን ከእሳትና ከነፋስ በቀዳሚት እሑድ ሲፈጥራቸው በነገድና ከተሞች ከፋፍሎ እንደነበርና ለእያንዳንዱም ሊቃነ መላእክት እንደሾመላቸው የመጽሐፍተ ፍጥረታት ይጠቅሳሉ፡፡
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና
በዚያም ተጽናንታ በምድር ኖረችበት
የአምላክ እናት ለ፷፬ ዓመታት
አብዝታ በመመላለስ ሳታቋርጥ ጸሎት
በጌቴሴማኒ መቃብሩ ቤት
ጊዜው ደረሰና ከተወደደው ልጇ የምትሄድበት
ጊዜ ዕረፍታ ለሶልያና
ወረደ ወልድ እምዲበ ልዕልና
ሥዕለ አድኅኖ
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች እንዴት አላችሁልን? ዘመነ አስተርእዮ ተብሎ በሚጠራው ወርኃ ጥር በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ብዙ በዓላትን አክብረናል፤ የጥምቀት፣ የቃና ዘገሊላ እንዲሁም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍቷ መታሰቢያ ዓመታዊ ክብረ በዓልና የቅዱሳን መላእክት፣ የቅዱሳን አባቶቻችን፣ እናቶቻችንን በዓላት አክብረናል፡፡ እንዴት ነበር ልጆች! በጣም ልዩ ነበር አይደል? ታዲያ እነዚህ መንፈሳዊ በዓላት ወደፊትም እንዲከበሩ የእናንተ ጉልህ አስተዋጽኦ ያስፈልጋል፤ ምክንያቱም የነገዋን አገርና ቤተ ክርስቲያን የምትረከቡት እናንተ ስለሆናችሁ በዓሉን ከማክበራችሁ በተጓዳኝ ለምን እንደሚከበርና የአከባበበር ሥርዓቱን በመጠየቅ መረዳት አለባችሁ፡፡
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ታዲያ ይህን አደራ ለመረከብ በመንፈሳዊውም፣ በዘመናዊው ትምህርት ጎበዞች መሆን አለባችሁ! በነገራችን ላይ ዘመናዊ ትምህርታችሁ የመንፈቀ ዓመት ፈተናችሁን እየተፈተናችሁ ያላችሁ፣ ለመፈተንም በዝግጅት ላይ ያላችሁም በርትታችሁ ማጥናት እንዳለባችሁ መዘንጋት የለበትም፡፡ ልጆች! ባለፈው ትምህርታችን በሥዕለ አድኅኖ ከተደረጉ ተአምራት ለአብነት ያህል ተመልክተን ነበር፤ ለዛሬ ደግሞ ቅዱሳን ሥዕላትን እንዴት አክብረን መያዝ እንዳለብን እንመለከታለን፡፡
ሕፃኑ ሰማዕት
ግብዝና ደካማ የሆነው የሰውን ሥጋ አሸንፎ፣ መከራን ተቀብሎ፣ ችግርን ተቋቁሞ፣ ፈተናን አልፎ መንፈሳዊ ሕይወትን ለመኖርና ክርስቲያን ለመሆን የሚደረገው ትግል እራሱን የቻለ ተጋድሎ እንደሚያስፈልገው የታወቀ ነው፡፡ እውነተኛ ለሆነው የክርስትና እምነተና ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖት የሚከፈለው መሥዋዕትም የተለየ ስፍራ አለው፡፡
የቃና ዘገሊላ ሰርግ
በቃና ሰርግ ቤት የተደረገው ተአምር የአዳዲስ አማኞችንና የሐዋርያትን እምነት ለማጽናትም የተደረገ በመሆኑ፣ ወንጌላዊው ዮሐንስ “ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ” ይለናል። እመቤታችን ድንግል ማርያምም ጌታችን ማንነቱ የሚገለጥበት ጊዜ መድረሱን አውቃ “የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው። ጌታችንም “ጊዜዬ ገና አልደረሰም” ማለቱ፣ በወቅቱ ያልነበረው ይሁዳ መጥቶ ተአምሩን እንዲያይና ለወደፊት “እኔ በሌለሁበት ተአምር አድርጎ ለየኝ” የሚል ምክንያት እንዳይኖረው ለማድረግ እንደሆነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተርጒሞታል፡፡
በዓለ ጥምቀት
በጥር ዐሥራ ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአጥማቂው ቅዱስ ዮሐንስ ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ።