• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

ደብረ ማርቆስ ማእከል 252 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን አስመረቀ።

በማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ማርቆስ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል ለ4 ዓመታት በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እንድማጣ ገነተ ኢየሱስ ዋናው ግቢ 150 እና ጤና ካምፓስ የመቃ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን 102 በድምሩ 252 ተማሪዎችን ካህናት አባቶች፣ የማእከሉ የሥራ አስፈጻሚ አባላትና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም አስመረቋል። በመርሐ ግብሩ ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን […]

በዘንድሮው ዓመት ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ካዘጋጃቸው 18 ሜዳሊያ ዋንጫውን ጨምሮ 14ቱ በግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የተወሰዱ መሆናቸው ተገለጸ

በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል በ7 የተለያዩ ግቢ ጉባኤያት ያስተማራቸውን 1,073 የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት በፔዳ ግቢ ጉባኤ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ አስመርቋል። አቶ ብርሃኑ አሳሳ በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል ምክትል ሰብሳቢ በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው የማእከሉን የእንኳን ደስ […]

የግቢ ጉባኤ አባል (CGPA) 4.00 ነጥብ በማምጣት የዓመቱ የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነ።

በማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል የጎባ ወረዳ ማእከል በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል ግቢ ጉባኤ 82 ተማሪዎች በጎባ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአባቶች ቡራኬ አሰመርቋል። ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል በግቢ ጉባኤው በሥራ አሰፈጻሚነት ሲያገለግል የነበረው ተማሪ ቶልቻ ከበደ በነርሲንግ የትምህርት መስክ ከ39 ኮርሶች 25ቱን ‘A+’ እና ቀሪውን ‘A’ […]

ማኅበረ ቅዱሳን እያስገነባ የሚገኘውን የልህቀት ማእከል የመጀመሪያ ዙር የፊኒሺንግ ሥራ ለማከናወን የገንዘብና የዐይነት ድጋፍ ማሰባሰብ መጀመሩን አስታወቀ

ማኅበረ ቅዱሳን ባለፉት 34 ዓመታት በርካታ መንፈሳዊ አገልግሎቶችን በስብከተ ወንጌል፣ በገዳማትና በአብነት ትምህርት ቤቶች፣ በጥናትና ምርምር፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (የዩንቨርስቲ/ኮሌጅ) ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችን በማስተማር፣ 24 ሰዓታት የሚዲያ አገልግሎት በመስጠት፣ በመዝሙርና በኪነ ጥበባት፣ በሙያ፣ በማኅበራዊና በኢኮኖሚያዊ ዘርፍ እንዲሁም ሌሎች  አገልግሎቶችን እያከናወነ ይገኛል። ይህን አገልግሎት በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የልህቀት ማእከል እያስገነባ እንደሚገኝ በማኅበረ ቅዱሳን የልህቀት ማእከሉ ግንባታ ዐቢይ […]

የእንጅባራ ማእከል ላለፉት 4 ዓመታት ሲያስተምራቸው የቆዩ 200 ተማሪዎችን  አስመረቀ

በማኅበረ ቅዱሳን የእንጅባራ ማእከል የግቢ ጉባኤ ማስተባበሪያ ዋና ክፍል  ለአራት ተከታታይ ዓመታት በሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነምሕረት ቤተ ክርስቲያን በመደበኛ እና በኤክስቴንሽን መርሐ ግብር ሲያስተምራቸው የነበሩ 200 የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አስመርቋል። ከተመራቂ ተመሪዎች መካከል አንድ የዋንጫ፣ 11 የሜዳልያ እና 12 የማዕረግ ሰርተፍኬት ተሸላሚዎች የሚገኙበት ሲሆን የዋንጫ እና የሁለት ሜዳልያ ተሸላሚው ዲ/ን አላምራው ዋጋው ከወሰደው 55 ኮርሶች […]

ማኅበረ ቅዱሳን በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ለሚገኙ ተፈናቃዮች  አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አደረገ

የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የሆነበት አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አድርጓል። ባለፉት ጊዜያት በመተከል ዞን ዳንጉር ወረዳ በሚገኙ አንዳንድ ቀበሌዎች ባጋጠማቸው ማኅበራዊ ቀውስ ምክንያት የተጎዱ ከ1500 የሚልቁ ወገኖች በማንቡክ ከተማ ውስጥ በተለያየ ሁኔታ ከማኅበረሰቡ ጋር ተጠልለው እንደሚገኙ መረጃዎች ያሳያሉ። ይህንንም ችግር የተረዳው ማኅበረ […]

የአዲስ አበባ ማእከል 500 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች መመረቃቸውን ገለጸ።

በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል ቅዱስ ገብርኤል ማስተባበሪያ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ሲያስተምራቸው የነበሩ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በደብረ ጽጌ ፋንታ ቅድስት አርሴማ ወቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያን ማስመረቁን የማስተባበሪያው ኃላፊ አቶ ተሾመ ሙሉጌታ ገለጸዋል። በዕለቱም ትምህርተ ወንጌል በመጋቤ ሐዲስ መምህር ጥላሁን ታዬ ፣መዝሙርና ወረብ በተመራቂ ተማሪዎች የቀረበ ሲሆን […]

የወላይታ ሶዶ ማእከል ለ8 ወራት ያስተማራቸውን 45 የበገና ዘማርያንን አስመረቀ።

በማኅበረ ቅዱሳን ወላይታ ሶዶ ማእከል በልማት ተቋም ሥር ለ8 ወራት ሲያስተምራቸው የቆዩ 45 የበገና ዘማርያንን በወላይታ ሶዶ በኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም አስመረቋል። በመርሐ ግብሩ የወላይታ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ቀሲስ ቦክቻ ኤንጋ፣ የኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ አርያም ዮሐንስ አያሌው […]

የቅዱስ ያሬድን ትሩፋት በዓለም የዕውቀት መድረክ ላይ ለማስተዋወቅ የምርምር ማእከላትን የማቋቋምና የዲጂታል ቅርስ አያያዝ ዘዴዎችን የመተግበር ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለጸ።

በማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማእከል ከባሕር ዳር ሀገረ ስብከት እና ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በቅዱስ ያሬድ አበርክቶ እና በቅዱስ ያሬድ ዜማ ላይ ያሉ ተግዳሮቶችን የሚዳስስ የዐውደ ጥናት ጉባኤ ተካሄዷል። በዐውደ ጥናት መርሐ ግብሩ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ኤፍሬም ሙሉዓለም፣ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ዋና ጸሐፊ መልአከ ብርሃን ፍሥሐ ጥላሁን፣ የባሕር […]

አውስትራሊያ ማእከል ዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር አካሄደ

በማኅበረ ቅዱሳን አውስትራሊያ ማእከል የተዘጋጀው “ዝክረ ቅዱስ ያሬድ” መርሐ ግብር ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም (May 24, 2026) ተካሄዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ ያሬዳዊ ወረብ፣ የቅዱስ ያሬድን የሕይወት ታሪክ ከትውልድ እስከ መሰወር እንዲሁም ቅዱስ ያሬድ ከነገረ መለኮት ባሻገር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያደረገው አስተዋፅኦ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን ስለ ሦስቱ የዜማ ስልቶችና ስለ አምስቱ የዜማ መጻሕፍት […]

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ