መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ወርኃ ግንቦት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ዘጠነኛው ወር “ግንቦት” በመባል ይታወቃል፡፡ ግንቦት “ገነበ፣ ገነባ፣ ሠራ፣ ቆፈረ፣ ሰረሰረ” ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ሲሆን ትርጒሙም “ገቦ፣ ክረምት፣ የክረምት ጎን፣ ጎረ ክረምት (የክረምት ጉረቤት)” ይባላል። ይህንም ስም የሰጡት የክረምት መግቢያ ምድር ለእርሻ የምትዘጋጅበት ወቅት በመሆኑ ነው።
አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላት መጽሐፋቸው ውስጥ የዚህን ወር ቃል ሲተረጒሙ “ስመ ወርኅ፣ ታስዕ እመስከረም፣ ገቦ ክረምት፣ ጎረ ክረምት” ይልና በግንብ ዘይቤ ሲፈቱት ግን “ወርኀ ሡራሬ” ያሰኛል፡፡ የባቢሎን ግንብ ሳይቀር ሁለቱ መቅደሶች በግንቦት ወር ተመሥርተዋል፡፡ (፫ኛ ነገ.፮፥፩፣ ዕዝ.፫፥፰) ይሉታል። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፫፻፳፪)
‹‹ለሁሉም ጊዜ አለው›› (መክብብ ፫፥፩)
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የትንሣኤን በዓል ወቅት (በዓለ ኀምሳን) እንዴት እያሳለፋችሁ ነው? በሰንበት ቤተ ክርስቲያን በመሄድ እያስቀደሳችሁ እንደሆነ ተስፋችን እሙን ነው! የአካዳሚ (ዘመናዊ) ትምህርትስ ጠንክራችሁ እየተማራችሁ ነውን! የዓመቱ ትምህርት የሚያበቃበት ጊዜ እየደረሰ ነው! አንዳንዶች ፈተና የምትፈተኑበት ጊዜው በጣም ደርሷል፡፡ በርትታችሁ በመማር፣ በማጥናት ጥሩ ውጤት ማስመዝገብ አለባችሁ፡፡
ልጆች! ያላችሁበት ወቅት ዓለማችን ከብዙ ሥልጣኔ ደረጃ የደረሰችበት ነው። ታዲያ እናንተም ከዚህ እኩል እንድትራመዱ በርትታችሁ በመማር ችግር ፈቺ፣ መፍትሔ አምጪ መሆን አለባችሁና በርቱ! ባለፈው ትምህርታችን ስለ ሰላም ተምረን ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ ስለ “ጊዜ” እንማራለን! መልካም!
የሕይወት መዓዛ
መድኃኒዓለም ክርስቶስ ሕይወትን ያጣጣምንበትና ያሸተትንበት መልካም መዓዛ መሥዋዕት ነው!
ዘለዓለማዊ ሰላም
ፍጹም ጤና፣ ዕረፍት፣ ዕርቅ፣ ፍቅር፣ አንድነት፣ ደኅንነት፣ ተድላ፣ ደስታ፣ ሰላምታ፣ የቡራኬ የምርቃት ቃል ሰው ሲገናኝ የሚለዋወጠው የመልካም ምኞት መግለጪያ የሆነው ሰላም ለሁሉ ነገር መሠረት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መዝገበ ቃላት ገጽ ፰፻፷፮) ምንጩ ደግሞ እውነተኛ ዘለዓለማዊ ሰላምን የሚሰጥ የሰላም አምላክ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ እርሱ የሰላም አለቃ ነውና ‹‹…የዘለዓለም አባት የሰላም አለቃ…›› እንዲል፡፡ (ኢሳ.፱፥፮) እውነተኛ ሰላም የሚገኘው ከእርሱ ዘንድ መሆኑን እንዲህ በማለት ነግሮናል፤ ‹‹…ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም…፡፡›› (ዮሐ.፲፬፥፳፯)
ሰላም!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? በፈቃደ እግዚአብሔር የጀመርነው ዐቢይ ጾም (ጾመ ክርስቶስ) ጨርሰን በዓለ ትንሣኤን እያከበርን ነው፤ በዓሉን እንዴት እያከበራችሁ ነው? የትንሣኤ በዓል ነጻነታችንን አግኝተን ትንሣኤ እንዳለን የተበሠረበት በዓላችን ነውና ታላቅ በዓል ነው፡፡
ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶ ሞትን ድል አድርጎ በመነሣቱ ትንሣኤያችንን አበሠረን፤ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለን ዐወቅን፡፡ ታዲያ በጾሙ ወቅት እናደርገው እንደነበረው በጸሎት መበርታትና በመንፈሳዊ አገልግሎት መሳተፍ አለብን፤
በዘመናዊ ትምህርታችን መበርታት እንዳለብንም መዘንጋት አይገባም፡፡ አሁን ያለንበት ጊዜ ትምህርቱ መገባደጃ ወቅት ስለሆነ ከፈተና በፊት በርትተን በማጥናት ዕውቀትን አግኝተን ከክፍል ክፍል በጥሩ ውጤት መሸጋገር ይገባናል፤ መልካም! ለዛሬ ከበዓለ ትንሣኤ ጋር በተያያዘ ስለ ሰላም እንማራለን፡፡
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ አደረሳችሁ!
‹‹የማይመረመር ብርሃን!›› (ሥርዓተ ቅዳሴ)
የማይመረመረው ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳኑ ምሥጢር ከፍጥረት ረቂቅ (የማይመረመር) ነው፡፡ በመስቀል ላይ ሁኖ አምላክነቱን በገለጸ ጊዜ ጠላት ዲያብሎስ እንዲህ ብሏል፤ ‹‹… ያለኃጢአት የሞተ ይህ ማን ነው? በብርሃኑ ብዛት የጨለማውን አበጋዝ ዕውር ያደረገው ይህ ማን ነው?›› (ሃይማኖተ አበው ትምህርት ኅቡዓት ፬፥፲፮)
‹‹የወይን ግንድ ይቆረጣል›› (ተአምረ ማርያም)
እውነተኛው የወይን ግንድ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማዳን ሥራውን ይፈጽም፣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል መፀነሡን ያበስር ዘንድ ወደ እመቤታችን በተላከ ጊዜ የተነገረ ቃል ነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ብሥራትን ይናገር ዘንድ ወደ እመቤታችን በተላከ ጊዜ በግንባሩ ተደፍቶ ልዑል እግዚአብሔርን ‹‹ጌታ ሆይ! የምትነግረኝ ይደረግ ዘንድ እንደምን ይሆናል?›› አለው፡፡ ጌታም ‹‹የጀመርኩትን ቸርነት ፈጸምኩ፣ የወይን ግንድ ይቆረጣል፤ ወይራም ከበለስ ጋር ይተከላል፤ ቅጽሮችም ይቀጸራሉ (ምግባር ከሃይማኖት ጋር ይሠራል)፤ ገብርኤል ሆይ! ሄደህ ለዳዊት ልጅ ‹‹እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ›› ብለህ አብሥራት›› አለው፡፡ ‹‹ለዘለዓለም ነግሦ የሚኖረውን እነሆ ትፀንሳለሽ በላት›› አለው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ይህን ሰምቶ ሰገደ፡፡ ጌታችን ‹‹እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ›› በማለት እንደተናገረው የወይን ግንድ የተባለ እርሱ ነው፡፡ (ዮሐ.፲፭÷፩)
“ሆሣዕና በአርያም” (ማቴ.፳፩፥፱)
ከደቀ መዛሙርቱም ሁለቱን ልኮ ቤተ ፋጌ ከምትባል ቦታ አህያ እና ውርንጫ አስመጥቶ በእነርሱም ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገባ። በዚያን ሰዓት ከይሁዳ አውራጃዎች ሁሉ የፋሲካን በዓል ለማክበር የተሰበሰቡት ሁሉ የኢየሱስን ወደ ኢየሩሳሌም መምጣት ሰምተው በእልልታ እና በዝማሬ “ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም የሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር።” (ማቴ.፳፩፥፱)
ወርኃ ሚያዝያ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ስምንተኛው ወር “ወርኃ ሚያዝያ” በመባል ይታወቃል፡፡ ሚያዝያ ማለት “መሐዘ፣ ጎለመሰ” ከሚለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን “ጎለመሰ፣ ጎበዘ፣ አደገ፣ ሚስት ፈለገ፣ የሚዜዎችና የሙሽሮች ወር” የሚል ትርጒም ይይዛል። ይህን ስያሜም ያገኘው በሀገራችን በአብዛኛው ሰርግ የሚደረገው በዚህ ወር ስለሆነ ነው።