ጥንተ ስቅለት
/in ምንባባት, ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanለዓለም ሁሉ ድኅነት መድኃኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ መጋቢት በባተ በ፳፯ኛው ቀን በመስቀል ላይ ተሰቀለ፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ልጆቹም ይህን እናዘክር ዘንድ ዓይን ልቡናችንን ወደ ቀራንዮ እናንሣ!
ገብር ኄር
/in አጽዋማት, ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanበጎ አገልጋይ ለጌታው ታምኝ እንደመሆኑ ‹‹ገብር ኄር›› ይባላል፡፡ ይህም ስያሜ ለዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት እንደተሰጠ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ይገልጻል፡፡ የስያሜው መነሻ የሚገኘው ደግሞ በዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከሚነበበው በማቴዎስ ወንጌል ክፍል ነው፡፡ (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)
ጥንተ ሆሣዕና
/in ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanየዓለም መድኃኒት አምላካችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንባባና ልብስ ተነጥፎለት በአህያ ውርንጭላዋ ተጭኖ ቤተ መቅደስ የገባበት ዕለት ‹‹ጥንተ ሆሣዕና›› በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ይዘከራል፡፡ ሆሣዕና ማለት ‹‹አሁን አድን›› ማለት ነው፤ (ማሕቶተ ዘመን ገጽ ፻፷)
ደብረ ዘይት
/in አጽዋማት, ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanከኢየሩሳሌም በስተምሥራቅ የሚገኝ ቦታ የሚገኘው ተራራ ደብረ ዘይት የጸሎተ ሐሙስ ማታ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተያዘበት ነው፡፡ ቤተ ፋጌ እና ቢታንያ በኮረብታው ጫፍ እና በምሥራቅ ዳገት ላይ ይገኛሉ። ጌታችን ኢየሱስ ስለ ቤተ መቅደሱ መፍረስ፣ ስለ ዓለም ፍጻሜና ስለ ዳግም ምጽአት በዚህ ተራራ ላይ ተናገሯል።
ዝርዝር ርባታ-ክፍል ሁለት
/in ግእዝ ይማሩ /by Mahibere Kidusanውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? የእግዚአብሔር አምላካችን ስም የተመሰገነ ይሁን! ባለፈው የትምህርታችን ክፍለ ጊዜ የግሥ ርባታ የመጀመሪያውን ክፍል አቅርበንላችኋል፤ እንደተረዳችሁት ተስፋ እንዳርጋለን፤ ለዛሬ ደግሞ ሁለተኛውን ክፍል እንደሚከተለው አቅርበንላችኋል፤ በጥሞና ተከታተሉን!
የዐቢይ ጾምና ሳምንታቱ
/in ለሕፃናት /by Mahibere Kidusanውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ?! የጾምን ወቅት እንዴት እያሳለፋችሁት ነው? አባቶቻችን ሊቃውንት ስለ ጾም እንዲህ ይላሉ፤ ጾም ማለት ከምግብና ከውኃ መከልከል ብቻ ሳይሆን ከክፉ ሥራም መታቀብ (መከልከል) ነው፤ ጾም የጽድቅ በር ናት፤ ጾም ለመልካም ነገር የምታነሣሣን ናት፡፡
ውድ እግዚአብሔር ልጆች! ከጸሎትና ከስግደት ጋር እንዲሁም ትምህርት በማይኖረን በዕረፍት ጊዜያችን ደግሞ ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ፣ ታዛዦች በመሆን የጾሙን ጊዜ ልናሳልፍ ይገባል፡፡ መልካም!
ባለፈው የትምህርት ክፍለ ጊዜ ስለ ዐቢይ ጾምና በጾሙ ወቅት ስላሉት ሳምንታት እስከ እኩለ ጾም ድረስ ተመልክተናል፤ ለዛሬ ደግሞ ቀጥሎ ያለውን እንመለከታለን፤ መልካም ንባብ!!!
‹‹አልጋህን ተሸክመህ ሂድ›› (ዮሐ.፭፥፩-፱)
/in አጽዋማት, ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanለሠላሳ ስምንት ዓመታት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ የነበረው አንድ በሽተኛ ሰው በጌታችን ቃል ተፈውሶና አልጋውን ተሸክሞ ወደ ቤቱ መሄዱ በቅዱስ መጽሐፍ ተመዝግቧል፡፡
ዝክረ ግማደ መስቀሉ
/in ምንባባት /by Mahibere Kidusanየክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የተገለጠበትና የተገኘበት መጋቢት ፲ ግማደ መስቀሉን የምንዘክርበት ዕለት ነው። የዚህም የከበረ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል። መጀመሪያ የጻድቁ ንጉሥ የቈስጠንጢኖስ እናት በሆነች በንግሥት ዕሌኒ እጅ ነው።
ቤተ መቅደስ
/in ወቅታዊ ትምህርት /by Mahibere Kidusanቤተ መቅደስ ከሁለት ጥምር ቃላት የተገኘ ትርጓሜው ‹የተቀደሰ ቤት› የሚል ሲሆን ይህም የእግዚአብሔር አምላካችን ማደሪያ ወይም ቤት ነው፤ ቤተ መቅደስን የሚወክሉ አካላትም ሦስት ናቸው፡፡
ዜና ዕረፍት
/in ዘገባዎች /by Mahibere Kidusanብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በቀድሞው አጠራር ጎንደር ክፍለ ሀገር በአሁኑ በደቡብ ጎንደር ዞን በአንዳቤት ወረዳ ልዩ ስሙ አረጊት ኪዳነ ምሕረት ገዳም አካባቢ ከአባታቸው ከብላታ ፈንታ ተሰማና ከእናታቸው ከወ/ሮ ለምለም ገሠሠ በ ፲፱፻፴ ዓ.ም ተወለዱ፡፡