በምሕረትህ ጎብኘኝ

ለዘመናት ከአንተ ስሸሽ እንደኖርኩኝ፣
ለማትጠቅመኝ ዓለም ለፈራሽ ሥጋዬ እንደተጨነኩኝ፣
ነፍሴን እንዳስራብኳት እንደተጠማሁኝ፣
አለሁ እኔ ባሪያህ ለተፈጠርኩለት መኖር እንዳቃተኝ፡

ጊዜ እንደሰጠኸኝ እንደጨመርክልኝ ማለዳ አስባለሁ፣
ለሥጋዬ ድካም ቀኔን ስጀምረው ደግሞ እዘነጋለሁ፡፡
አምላክ ሆይ ለምስኪን ልጅህ ግለጥልኝ፣
ዕድሜዬ ሲጨምር የኖርኩ ሲመስለኝ፣
ከተቀመጠልኝ ከተጻፈው ቀኔ ቁጥር እንደቀነስኩኝ፡፡

  • ወይ እኔ መሔዴ ወይ አንተ መምጣትህ፣
    የማይቀር ነውና ልጅህን መጥራትህ፡፡
    ጌታ ሆይ ባሪያህን በምሕረትህ ጎብኘኝ፣
    ለልቤ ልብ ሆነህ ማስተዋሉን ስጠኝ፣
    በዘላለማዊው በማያልፈው ቤትህ ሕይወት እንዲኖረኝ፡፡

                  ሳምራዊት ሰለሞን
ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሐረር ጤናና ሕክምና ሳይንስ ግቢ ጉባኤ

0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *