ማስተዋሉን ስጠኝ

                ማስተዋሉን ስጠኝ

ያ መልካም ገበሬ ለበጋው የሚሆን ምርቱ የናፈቀው፣

ሕይወት የሚያድል ዘር በክረምት ጊዜው፡፡

                ይዘራ ጀመረ ወንጌሉን በሙሉ በወደደው መሬት፣

                የሚሰበስበው ለእርሱ የሚያደርገው ፍሬ እንዲሆንለት፡፡

ከፊሉ በመንገድ እንዲሁ ወደቀ፣

የሰማይ አዕዋፍ እየተመገቡት ያለፍሬ አለቀ፡፡

                ሌላም መጠን ያህል ደገኛው ከዘራው፣

                በመሬት ሆነና ጥልቅ አፈር በሌለው፡፡

ቢቀበልም እጅግ በሐሴት ተሞልቶ፣

በችግሩ ካደ ጊዜዋን ያልፋት ዘንድ ማፍራቱን ሰውቶ፡፡

                ደግሞ ከተቀረው ከዚያ ከመልካም ዘር ፣

                በእሾህ የታነቀ እንዳያፈራበት የተያዘም ነበር፣

                የዓለምን ትካዜ መከራ ሐሳቧን ተሸክሞ ‘ሚኖር፡፡

ከመልካሙ መሬት የወደቀው ቃሉ፣

ሠናይ ፍሬ ኖረው ተወዳጅ በሁሉ፡፡

                የሰማያውያን  ቃል አዳምጦታልና፤

                በተግባር ቢኖረው የእርሱ አደረገ መልካሙን ጎዳና፡፡

አምላክ ሆይ ያ ዘርህ በእኔ ልብ የላከው፣

ከሚቆረጠው ተክል ፍሬን ካላፈራው፣

በዓለም ትካዜ በእሾህ ከታነቀው፡፡

                መካከል ነውና ባሪያህን አስበኝ፣

                ከመልካሙ መሬት ዘርህን እንዳሳርፍ ማስተዋሉን ስጠኝ፡፡

 

                                ሳምራዊት ሰለሞን

                ከሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሐረር ጤናና ሕክምና ሳይንስ ግቢ ጉባኤ

0 replies

Leave a Reply

Want to join the discussion?
Feel free to contribute!

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *