መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹አባታችሁ አብርሃም የእኔን ቀን ያይ ዘንድ ተመኘ፤ አይቶም ደስ አለው›› (ዮሐ. ፰፥፶፮)
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌልን በሰበከበት በዘመነ ሥጋዌ እርሱ የሚያስተምረውን ትምህርት እና የሚያደርገውን ገቢረ ተአምራት ወመንክራት ሰምተውና አይተው አይሁድ ቅናት አደረባቸው፡፡ ጌታችንንም በክፋት በሚከታተሉበት ጊዜ የእርሱን ጌትነትና የባሕርይ አምላክነት በትምህርት እየገለጠ ብዙ ተአማራት ቢያሳያቸውም በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ እንዲሁም በሥጋ ተገልጦ ሲመላለስ ስላዩት አምላክነቱን ተጠራጥረው እንዲህ አሉት፤ ‹‹በውኑ ከሞተው ከአባታችን አብርሃም ትበልጣለህን? ነቢያትም ሞቱ፤ ራስህን ማን ታደርጋለህ?›› (ዮሐ. ፰፥፶፫-፶፱)…
‹‹መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ፤ ለሞት ግን አሳልፎ አልሰጠኝም›› (መዝ. ፻፲፯፥፲፰)
ተግሣጽ የሚለው ቃል እንደየገባበት ዐውድ እና እንደየተነገረበት ዓላማ የተለያየ ፍቺ ቢኖረውም በመዝገበ ቃላት ደረጃ ቤተ ክርስቲያናችን ካፈራቻቸው ሊቃውንት አንዱ የሆኑት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት ሐዲስ በተሰኘ መጽሐፋቸው (ገጽ ፫፻፳፯) ‹‹ተግሣጽ›› ማለት ትምህርት፣ ብርቱ ምክር፣ ምዕዳን፣ ኀይለ ቃል፤ እና ቁጣ ብለው ተርጉመውት ይገኛል፡፡
ዘመነ ስብከት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዘመን አከፋፈል መሰረት ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በፊት ከታኅሣሥ ፯ ጀምሮ እስከ ፳፱ ያለው ወቅት ዘመነ ስብከት ይባላል፡፡ እያንዳንዱ ሳምንታትም ስብከት፣ ብርሃን እና ኖላዊ በሚል ስያሜ ይታወቃሉ፡፡ በዚህም ወቅት ስለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድር መምጣት መወለድ ነቢያት የተናገሩት ትንቢት በስፋት ይነገርበታል፡፡
በአታ ለማርያም
ጥንትም ስትታሰብ በአምላክ ኅሊና
ትታወቅ ነበረ በሥሉስ ልቡና
በአቷን አደረገች የአርያም መቅደስ
የዓለሙን ፈጣሪ ዘወትር ለማወደስ…
‹‹ወደ ጠባቡ በር ትገቡ ዘንድ በርቱ›› (ሉቃ. ፲፫፥፳፬)
በምድራዊ ሕይወት ሰዎች የሥጋ ፈቃዳቸውን ብቻ መፈጸማቸው ለኃጢአታቸው መብዛት መንሥኤ ይሆናል፤ በጾም በጸሎት እንዲሁም በስግደት ስለማይተጉና በመከራ ስለማይፈተኑም እንደፈለጉ በመብላት በመጠጣት፣ ክፋት በመሥራት እንዲሁም ሰውን በመበደል በድሎት እንዲኖሩ ዓለም ምቹ ትሆንላቸዋለች፡፡ ዓለማዊነት መንገዱ ሰፊ በመሆኑ የሥጋ ፈቃዳችን የምንፈጽምበት መንገድም በዚያው ልክ ብዙ ነው፡፡
ክርስቲያናዊ አንድነት
ክርስቲያናዊ አንድነት በእምነት አንድነትና በአስተምህሮ ስምምነት የሚገለጥ ነው፡፡ በዚህም በክርስቶስ ክርስቲያን የተባልን ሰዎች የሥላሴን አንድነትና ሦስትነት በማመን፣ ከሀብተ መንፈስ ቅዱስ በመወለድ፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን በመቀበል በአጠቃላይ ለሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በመገዛት መኖር ማለት እንደሆነ እንረዳለን፡፡
የቃል ኪዳኑ ታቦት
ነቢዩ ሙሴ ዐርባ ቀንና ዐርባ ሌሊት ጸልዮና ጹሞ ዐሥርቱ ቃላት የተጻፈበትን ጽላት ከእግዚአብሔር ከተሰጠው በኋላ የቃል ኪዳኑን ታቦት ‹ታቦተ ጽዮንን› እንደሠራት መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጻል፡፡ ታቦተ ጽዮን ከማይነቅዝ እንጨት የተሠራችበት ምክንያት የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ንጽሕና ለማመልከት ነው፡፡ በውስጥም በውጪም በጥሩ ወርቅ የተለበጠች መሆኗ ደግሞ የእመቤታችን ድንግል ማርያም ቅድስናዋንና በሁለት ወገን ድንግል የመሆኗ ምሳሌ ነው፡፡
‹‹የሰው ሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል›› (መዝ. ፻፵፬፥፲፭)
ተስፋ ሲኖረን የነገን ለማየት እንናፍቃለን፤ ዛሬ ላይም በርትተን ለመጪው እንተጋለን፤ የመልካም ፍጻሜችንም መድረሻ በተስፋችን ይሰነቃልና፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ ‹‹የሁሉ ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ አንተም ምግባቸውን በየጊዜው ትሰጣቸዋለህ። ቀኝ እጅህን ትዘረጋለህ፤ በሥርዓትህ ለሚኖሩ እንስሳ ሁሉ ታጠግባለህ፡፡ እግዚአብሔር በመንገዱ ሁሉ ጻድቅ ነው፤ በሥራውም ሁሉ ቸር ነው። እግዚአብሔር ለሚጠሩት ሁሉ፥ በእውነት ለሚጠሩት ሁሉ ቅርብ ነው። ለሚፈሩት ምኞታቸውን ያደርጋል፥ ልመናቸውንም ይሰማል፥ ያድናቸዋልም። እግዚአብሔር የሚወድዱትን ሁሉ ይጠብቃል፤ ኃጢአተኞችንም ሁሉ ያጠፋል›› በማለት ገልጿል፡፡ (መዝ. ፻፵፬፥፲፭-፳)
የነቢያት ጾም
በዘመነ ብሉይ ነቢያት እግዚአብሔር ወልድ ከንጽሕተ ንጹሐን፤ ቅድስተ ቅዱሳን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ለአዳም የገባለትን ቃል ይፈጽም ዘንድ ትንቢት በመናገር ለሕዝቡ የምሥራችን ቃል ያበሥሩ ነበር፡፡… ነቢያቱ በጾም በጸሎት ተወስነው አምላክ ሰው ሆኖ ዓለምን የሚያድንበትን ዘመነ ሥጋዌ ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ የነቢያት ትንቢትና ጸሎትም በእግዚአብሔር ሰው መሆን ተፈጽሟል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ይህንን ታሳቢ በማድረግ በዘመነ ማቴዎስ፣ ማርቆስና ሉቃስ፤ ከኅዳር ፲፭ አስከ ታኅሣሥ ፳፱፤ በዘመነ ዮሐንስ ደግሞ እስከ ታኅሣሥ ፳፰ ጾም ታውጃለች፡፡
የብፁዕ አቡነ ኢሬኔጅ ዜና ዕረፍት
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ኢሬኔጅ የሰርቢያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ።