መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
‹‹ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሺ፥ ተመለሺ›› (መሓልየ መሓልይ ዘሰሎሞን ፯፥፩)
በብሥራተ መልአክ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደችውን አንድያ ልጇን ሄሮድስ ሊገድልባት በፈለገው ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሀገር ወደ ሀገር መሰደዷን የሚያመለክተውን፣ ከስደትም እንድትመለስ ጠቢቡ በትንቢት ቀድሞ የተናገረው ይህን ቃል ነው፡፡ ወቅቱ አብዝተን ስለ ስደቷና ተያያዥ ታሪኮች የምንማርበት፣ የምንጸልይበት፣ የምናስተምርበትና የምንዘምርበት ወቅት በመሆኑ በዚህ ርእስ ተከታታይ ጽሑፎችን ለማቅረብ እንሞክራለን፤ ተከታተሉን!
የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን
በክርስቶስ ክርስቲያን ተሰኝቶ ክርስቶሳዊ የሆነ ሁሉ የድርሻውን የሚወጣና ሥርዓቱን የሚጠብቅ ከሆነ በዚህ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ክብሯ ልዕልናዋ ተጠብቆ ትኖራለች፣ ረድኤተ እግዚአብሔርና በረከቱ ዘወትር አይለየንም፤ ሀገር ጽኑ ሰላም ትሆናለች፣ በወዲያኛው ዓለምም የዘለዓለምን ርስት መንግሥተ ሰማያትን እንወርሳለን፤ የድርሻችንን የማንወጣና ቸልተኞች የምንሆን ከሆነ ግን የቤተ ክርስቲያንንም የሀገርንም ክብርም ልዕልናም ማስጠበቅ አንችልም፤
ዜና ዕረፍት
የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳምና የመንበረ መንግሥት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የበላይ ኃላፊ ሆነው በበአታቸው በመወሰን ሲያገለግሉ የቆዩት አባታችን ብፁዕ አቡነ ሰላማ ከዚህ ዓለም ተለይተዋል። ጸሎተኛ፣ ደግ፣ ርኀሩኁና ታጋሽ የነበሩት አረጋዊው አባት ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በአዲስ አበባ ሀሌሉያ ሆስፒታል በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም ፲፰ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ/ም ያረፉ መሆኑ ታውቋል።
‹‹በደስታ በዓልን አድርጉ›› (መዝ.፻፲፯፥፳፯)
ቀናትን ሁሉ ባርኮ የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ጊዜ የእርሱ ስጦታ በመሆኑ የከበረ ድንቅ ሥራውን ፈጽሞበታል፡፡ በእያንዳንዱ ዕለት ፍጥረታትን ከመፍጠሩ ባሻገር ለምስጋና፣ ለውዳሴ እና ለድኅነት ያከበራቸው በዓላትም አሉት፤ በእነዚህ ዕለታት ቃል ኪዳን አድርጓል፡፡
ቅዱስ መስቀል
ቅዱስ መስቀል ቀስት ከተባለ ጠላታችን ዲያብሎስ እንድናመልጥና ድል እንድናደርገው የተሰጠን ነው፤ ቅዱስ መስቀል መድኅን ዓለም ክርስቶስ ተሰቅሎ በክቡር ደሙ ቀድሶ የሰጠን፣ ሰላማችን የታወጀበት ኃይላችን፣ የሰላም አርማችን ነው!
የቤተ ክርስቲያን በዓላት አከባባር
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ አሸጋግሮ በሰላም ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! ዕንቁጣጣሽ እንዴት አለፈ? መቼም ደስ ብሏችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው!ልጆች! በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በዓላት እንዴት እንደሚከበሩ እኛም ደግሞ በምን ዓይነት መልኩ በበዓላት ላይ መሳተፍ አንዳለብን ልንነግራችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ!
ለሲኖዶሳዊ ልዕልና መከበር የምእመናን ድርሻ ከፍተኛ ነው!
ሲኖዶስ መሪ ነው፡፡ ሲኖዶስ የሕግ ሁሉ መገኛና የበላይ ባለ ሥልጣን ነው፡፡ ሲኖዶስ ሲኖዶስ ሆኖ ካልቀጠለ መሪነቱን ከተነጠቀ ውጤቱ ከባድ ነው፡፡
የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን ከምን ይጀምራል?
ቤተ ክርስቲያን የሁላችንም ቤት ናት፡፡ በቤታችን ሁላችንም የሥራ ድርሻ እንዳለን ሁሉ በመንፈሳዊት ቤታችን በቤተ ክርቲያንም እንዲሁ ሁላችንም ድርሻ ሊኖረን ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሊቀ ጳጳሳት፣ የካህናት እና በቤተ ክርስቲያን በአስተዳደር ሥራ ላይ የተሠማሩ ሰዎች ቤት ብቻ ሳትሆን የሁላችንም ቤት ናት፡፡
እስራት
ሰዎች በልዩ ልዩ ምክንያቶች በወኅኒ ቤት ይታሰራሉ፡፡ አንዳንዶች ወንጀል ፈጽመው፣ ያልታረመ ንግግር ተናግረው፣ በማታለል ተግባር ተሰማርተው፣ ሴት አስነውረው፣ ቤት ሰርስረውና የመሳሰሉትን እኩይ ተግባራትን ፈጽመው ሊሆን ይችላል፡፡ የሰው ልጆችም በሲኦል ወኅኒ ቤት ተጥለን ለአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመናት ስንሠቃይ የነበረው አባታችን አዳም ትእዛዘ እግዚአብሔርን ጥሶ፣ አምላክነትን ሽቶ፣ አትብላ የተባለውን በመብላቱ ነበር፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ ይህን አስመልክቶ ሲናገር ‹‹በሥጋ ሞተ በመንፈስ ግን ሕያው ሆነ በእርሱም ደግሞ ሄዶ በወኅኒ ለነበሩት ነፍሳት ሰበከላቸው›› ይላል፡፡ (፩ኛጴጥ.፫፥፲፱)
ዳግም ሥራኝ!
የጽድቅ አበባዬ ጠውልጎ የኃጢአት ችግኜ አፈራ
አዝመራው ለምልሞ በለሱም የጎመራ
ለዓለም ሳጎበድድ ጊዜዬን የጨረስኩ
በኃጢአት ብል ተበልቼ ባዶ ሆኜ የቀረሁ
ክርስትናዬን በነጠላ የሸፈንኩ
የራሴ ምሶሶ እያለ ጉድፍ ለማውጣት የሮጥኩ
እኩይ ግብሬ ጸጽቶኝ በንስሓ ያልታጠብኩ