• እንኳን በደኅና መጡ !

ዜናዎች፣ ወቅታዊ ክንውኖች እና ልዩ ልዩ ይዘቶች

ashetenKArsema.jpg

ጥንታዊው አሸተን ቅድስት አርሴማ ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ህንፃን ለመሥራት ጥሪ ቀረበ።

በወ/ኪዳን  ወ/ኪሮስ
በስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሰረተችው የአሸተን ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ህንፃ ለማሠራት እየተደረገ ባለው እንቅስቃሴ ምእመናኑን ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ።
ashetenKArsema.jpg

hall.jpg

በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና በመካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ የእግር ጉዞ ተዘጋጀ።

በኪ/ማርያም ወ/ኪሮስ
 
hall.jpg የደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ እና መካነ ጎልጎታ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ሰበካ ጉባኤ እያሰራ ላለው የሰንበት ት/ቤት እና የስብከተ ወንጌል ሁለገብ አዳራሽ ታህሳስ 10 ቀን 2003ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ጀምሮ መነሻው መስቀል አደባባይ መድረሻው በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን  የሚፈጸም  የእግር ጉዞ አዘጋጅተዋል።
  
 በዕለቱም ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት፣ታላላቅ የቤተክርስቲያን አባቶች፣ መምህራንና ዘማርያን፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ ጋዜጠኞች፣ አርቲስቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ።
styared.jpg

ቅዱስ ያሬድ በደብረ ታቦር ከተማ ተዘክሮ ዋለ

ደብረ ታቦርና ባህር ዳር ማዕከል
ሰንበት ትምህርት ቤቱ ለግቢ ጉባኤ ተማሪዎች አቀባበል አደረገ

«ዝክረ ቅዱስ ያሬድ» በሚል ርዕስ ከህዳር 11-12 ቀን 2003 ዓ. ም. ለሁለት  ቀናት የቆየ የሥዕል ዓውደ ርዕይና ሲምፖዚየም ተካሄደ፡፡ ዝግጅቱ የተካሄደበት ሰ/ት/ቤት አዲስ ለገቡ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች አቀባበል አደርጓል። 
styared.jpg
በደብረ ታቦር ከተማ የተካሄደውን መርሐ ግብር ያዘጋጀው በማኅበረ ቅዱሳን የደብረታቦር ማዕከል ሲሆን ኢትዮጵያ በብሉይና በሐዲስ፣ የቅዱስ ያሬድ ማንነት፣ ቅዱስ ያሬድና አፄ ገ/መስቀል፣በመርሐ ግብሩ በመሪጌቶች በዜማ ገለጻ የተደረገባቸው 8ቱ የዜማ ምልክቶችና የዜማ መሣሪያዎች በሥዕል ዓውደ ርዕዩ የተካተቱ ሲሆን የአሁኑን ሐመረ ተዋሕዶ እትም የሽፋን ሥዕል በመጠቀም ያለውን የተሃድሶ እንቅስቃሴ እንዲሁም የማኅበረ ቅዱሳን አርማና እንቅስቃሴ ገለጻ ተደርጐባቸዋል፡፡

ታቦት

እህተ ፍሬስብሐት

 ልጆች ታቦት ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ?

ልጆች ታቦት ማለት የእግዚአብሔር ትዕዛዝ የተፃፈበት ቅዱስ ሰሌዳ ማለት ነው፡፡ በመጀመሪያ ታቦትን ከእግዚአብሔር እጅ የተቀበለው ሙሴ ነበር።

የግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ ክፍል እንቅስቃሴ ተጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።

ከማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነት ክፍል
በማኅበረ ቅዱሳን የሀገር ውስጥ ማዕከላትና የግቢ ጉባኤያት ማደራጃና ማስተባበሪያ ዋና ክፍል በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥር እያስተማራቸው የሚገኙ ተማሪዎችን የክትትል እንቅስቃሴ አጠናክሮ መቀጠሉ ተገለፀ።
አቶ እንዳለ ደጀኔ፥ የግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያና ማጠናከሪያ ክፍል አስተባባሪ እንደተናገሩት፥ ማኅበሩ ተማሪዎችን ለማስተማር ሥርዓተ ትምህርት ቀርጾ 21 የመማሪያ መጻሕፍትን ያዘጋጀ ሲሆን፤ በአሁኑ ሰዓት ሥርዓተ ትምህርቱን ሙሉ በሙሉ በመከለስ የትምህርት አሰጣጥ ሥርዓቱን በማዘጋጀት ላይ ይገኛል።
debre_Tsege.jpg

የመነኮሳት አባቶች የጋራ መኖሪያ ቤት ተመረቀ

በደረጀ ትዕዛዙ
 
debre_Tsege.jpgበ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት በደብር ቅዱስ ደብረ ጽጌ ቅድስት ማርያም ገዳም የተሠራው የአረጋውያን አባቶች መነኮሳት የጋራ መኖሪያ ቤትና መጦሪያ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡መንፈሳዊ ዕውቀት ሀብታቸውን ሲያካፍሉ የኖሩ አባቶችን ለመንከባከብ የተደረገው ጥረት የሚያስመሰግን መሆኑን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ተናገሩ፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በገዳሙ ተገኝተው የመነኮሳቱን መኖሪያ ሕንፃ መርቀዋል፡፡

«በአዳም ምክንያት ሁላችን እንደምንሞት፣ እንዲሁም በክርስቶስ በኲርነት ሁላችን እንነሣለን፡፡» 1ኛ ቆሮ. 15፥22

                            ክፍል አራት

በጸጋ እግዚአብሔር አምላኩ የከበረ ይህ ሐዋርያው ጳውሎስ ትምህርቱን የበለጠ ተቀባይነት ያለው ለማድረግ  ብርሃነ እግዚአብሔር ኦሪትን ለሐዲሱ ምስክር እያደረገ ያስተማምናል፡፡ስለሆነም «ነሥአ መሬተ ወገብሮ ለእጓለ እመሕያው ወነፍሐ ላዕሌሁ መንፈሰ ሕይወት፤እግዚአብሔር አዳምን ከምድር ዐፈርን ወስዶ ፈጠረው፡፡ የሕይወትንም እስትንፋስ አሳደረበት፡፡»ብሎ መጽሐፍ እንደተናገረ በዚች ነፍስ ሕይወትነት የሚኖር ሥጋ አስቀድሞ መፈጠሩን ይገልጽና፤ከትንሳኤ ዘጉባኤ በኋላ ግን መንፈስ ቅዱስ ሕይወት ሆኖት የሚኖር ሥጋ እንደሚገኝ /እንደሚነሳ/ ለአጽንዖተ ነገር ደጋግሞ ይናገራል፡፡ ዘፍ 2÷7

የኅዳር ጽዮን በዓል አከባበር ዛሬም ቀጥሎ በድምቀት ተከብሯል።

ዲ/ን አሉላ መብራቱና በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

ኅዳር 20 ቀን ከዋዜማው ጀምሮ መከበር የጀመረው የኅዳር ጽዮን በዓል ዛሬም ቀጥሎ በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

ከትናንትና ማታ 2፡00 ደወል ከተደወለበት ጀምሮ፥ ሊቃውንት ካህናትና ዲያቆናት  ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በስብሐተ ማኅሌት በማድረስ ሌሊቱን አሳልፈዋል።

አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል

በሰሙነ ሕማማት ጠቅለል ባለ መልኩ የምናስባቸው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማማት አሥራ ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል ይባላሉ፡፡ ለክርስቲያኖች እነዚህን ሕማማተ መስቀል ማወቅና ዘወትር ማሰብ ተገቢ በመሆኑ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

የቤተክርስቲያን ፈተና እና ምዕመናን

በዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ

መግቢያ

የቤተክርስቲያን ታሪክ የሚጀምረው ከዓለመ መላእክት ነው፡፡ ታዲያ ፈተና ሁሌ አብሯት የሚኖር ቤተክርስቲያን መፈተን የጀመረችው በዚሁ በዓለመ መላእክት ነበር፡፡ ዲያብሎስ ትዕቢትንና ሐሰት ከራሱ አንቅቶ መላእክትን «እኔ ፈጠርኋችሁ» በማለት ባሰማው የሐሰት አዋጅ ከሰው ልጅ ወደዚህ ምድር መምጣት ጀምሮ በብሉይ ኪዳንም በርካታ ፈተናዎች ተፈራርቀዋል፡፡

በፌስቡክ የትስስር ገጽ ያግኙን

ስለ ማኅበረ ቅዱሳን መሰረታዊ መረጃዎች

ስያሜ

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ያከበራቸው የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት በአጠቃላይ የቅዱሳን ገድል፣ ትሩፋትና አማላጅነት የሚዘከርበት በመሆኑ ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› የሚል ስያሜውን አግኝቷል፡፡

የማኅበሩ ርእይ

ቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ የመሪነት ሚናዋን ስትወጣ ማየት

ተልእኮ

ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት እና ለሕልውናዋ የሚተጋ፣ የተደራጀ ፣ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ፤ ርቱዕ ዘመናዊ፤ ሁለገብ መሪ ትውልድ ማፍራት እና ማሰማራት

እሴቶች

  • መንፈሳዊነት

    ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
  • አገልጋይነት

    የማኅበሩ አባላት አገልግሎትን የክርስቲያናዊ ሕይወታቸው መገለጫ አድርገው በመቀበል በበጎ ፈቃድ ሰማያዊውን ክብርና ጸጋ በመሻት፣ ምድራዊ ክብርና ውዳሴ ከንቱን ሳይፈልጉ፣ በትሕትና እና በክርስቲያናዊ ፍቅር በታማኝነት ያገለግላሉ::
  • የሐሳብ መሪነት

    ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን ዘላቂ አገልግሎት የሚያስፈልጉ፣ ኦርቶዶክሳዊ እሳቤን የተከተሉና ዘመኑን የዋጁ የመሪነት ሐሳቦችን በማፍለቅ ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጋር በመመካከር ይሠራል::
  • ተባባሪነት

    ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሁሉም የቤተ ክርስትያን አካላት የወል ተግባር ነው ብሎ ያምናል:: በመሆኑም እንደየጉዳዩ አግባብነት ካላቸው ባለ ድርሻ እና አጋር አካላት ጋር በመግባባት፣ በመመካከር እና በቅንነት ለተልእኮ አንድነት ብዝኃ ጸጋን በማክበር አብሮ ይሠራል::
  • ሙያ አክባሪነት

    የማኅበሩ አባላት ባላቸው ልዩ ልዩ ሙያ /ዕውቀት/ ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የተሰባሰቡ በመሆናቸው፣ በማኅበሩ አሠራሮች ሁሉ ከኦርቶዶክሳዊው ትምህርተ ሃይማኖት ጋር በማይጋጩ በእውነተኛ መረጃ ለሚደገፉ ሙያዊ ምክረ ሐሳቦች ተገቢውን ክብርና ቅድሚያ ይሰጣል:: በቤተ ክርስቲያንም ለመንፈሳዊ እና ለዘመናዊው (አስኳላ) ሙያ ተገቢው ክብር እንዲሰጥ ይሠራል::
  • ምክንያታዊ ሞጋችነት

    ማኅበሩ በእውነተኛ መረጃ ላይ ተመሥርቶ ቤተ ክርስቲያንን ከውስጥም ሆነ ከውጭ የሚፈትኑ አስተሳሰቦችን፣ አሠራሮችን፣ ልማዶችን እና ትርክቶችን በግልጽና በመንፈሳዊ ጥብዓት እና በእውነት እንዲሞገቱና መፍትሔ ላይ እንዲደረስ ይሠራል::
  • ተጠያቂነት

    የማኅበሩ አገልግሎት ግብ ሰማያዊ ዋጋ ማግኘት ስለሆነ ኀላፊነትን በአግባቡ አለመወጣት በእግዚአብሔር እና በሰዎች ዘንድ የሚያስጠይቅ በመሆኑ በየትኛውም እርከን ላይ ያለ አባል እና አመራር በማኅበሩ አሠራር መሠረት በተሰጠው ኀላፊነት ተጠያቂ ይሆናል፡፡

ዓላማዎች

  • የቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ አስተዳደር፣ የአሠራር ሥርዐትና አስተሳሰብ፣ በቴክኖሎጂ እና በልዩ ልዩ መንገዶች በመደገፍ ዘመኑን ለዋጀ ጠንካራ አገልግሎት ማብቃት፤
  • የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን ሙሉ ሰብእናን የሚገነባ ሥርዐተ ትምህርት በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር የሚያገለግሉ እንዲሁም በማኅበራዊ፣ በኢኮኖሚያዊ በፖለቲካዊ እና በሀገር አስተዳደር ጉዳዮች መሪ/ንቁ ተሳታፊ አገልጋዮችን ማፍራት እና ማሠማራት፤
  • የተተኪውን ትውልድ ምንጭ ለማጎልበት የሰ/ት/ቤቶችን አቅም በማጠናከር የሕጻናት እና የወጣቶችን የተተኪነት ሚና ማሳደግ፤
  • ኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነትን በተግባር የሚገልጽ ቤተሰብ እና አንድነቱን የጠበቀ ኦርቶዶክሳዊ ማኅበረሰብ በመገንባት የተደራጀ እና የተናበበ አገልግሎት መስጠት፤
  • በተደራጀ እና ተደራሹን ማእከል ባደረገ መንገድ ስብከተ ወንጌልንና ሐዋርያዊ ተልእኮን ዘርፈ ብዙ በሆኑ መንገዶች በመላው ዓለም ማስፋፋት፤
  • በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚነዙትን የርእዮተ ዓለም፣ የሐሰት ትርክቶች እና የአጽራረ ቤተ ክርስቲያንን እንቅስቃሴ ጥናት እና ምርምር ላይ ተመርኩዞ መሞገት እና የተሳሳቱትን በማረም፣ በጠንካራ የዕቅበተ እምነት አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ሕልውና ማስጠበቅ፤
  • በተመረጡ ገዳማት እና አብነት ትምህርት ቤቶች የልኅቀት ማእከል እና የተለየ ክርስቲያናዊ ተልእኮ የሚፈጽሙ እንዲሆኑ የሚያስችል ሁለገብ የአእምሮ ልማት ድጋፍ ማድረግ፤
  • ማኅበሩ ዘመኑን የዋጀ ተቋማዊ የአሠራር ሥርዓት በመዘርጋት ተልእኮውን ማሳካት የሚችልበት አቅም መፍጥር ( በአመራር፣ በሰው ኃይል፣ በመንፈሳዊነት፣ በግንኙነት፣ በዕውቀት፣በልማት፣ በፋይናንስ፣ በቴክኖሎጂ)፤
  • ዓለም አቀፍ ግንኙነትና የትብብር አገልግሎትን መርሕ ያደረገ የኦርቶዶክሳውያን ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ማሳደግ፣

አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
የሸዋ ሊቀ ጳጳስ ፲፱፻፴፪-፲፱፻፹፪ዓ.ም.

የማኅበሩ ህንጻ