ብፁዕ አቡነ በርናባስ፣ የካቲት 12 2003 ዓ.ም

የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርናባስ አጭር የሕይወት ታሪክ

ከባሕር ዳር ማዕከል

ግንቦት23፣ 2003ዓ.ም

ብፁዕ አቡነ በርናባስ ግንቦት 20 ከምሽቱ 3.00 ማረፋቸው ይታወሳል፡፡

ብፁዕ አቡነ በርናባስ፣ የካቲት 12 2003 ዓ.ምየብፁዕነታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ግንቦት 22 ቀን 2003 ዓ.ም የተፈጸመ ሲሆን በሥርዓቱ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል፣  ብፁዕ አቡነ አረጋዊ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልሣዕ  ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ እንዲሁም የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አያሌው ጎበዜና የክልሉ ባለ ሥልጣናት፣ ከአዲስ አበባ የመጡ የደብር አስተዳዳሪዎች፣ የቅድስት ሥላሴ ኮሌጅ የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የሆኑት መምህር ደጉ ዓለም ካሣ፣  የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ ጸሐፊ አቶ ዘላለም አጥናፉ እንዲሁም ሌሎች በርካታ እንግዶችና ምዕመናን ተገኝተዋል፡፡

በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በብፁዕነታቸው ጥረት የተመሠረተውና ሀገረ ስብከቱ የሚገኘው የቤዛ ብዙኃን አጸደ ሕፃናት ተማሪዎች፣ በማኅበረ ቅዱሳን የአቡነ ጎርጎርዮስ አጸደ ሕፃናትና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንዲሁም የማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማዕከል የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢና ኢንጂነሪንግ ፋኩልቲ ግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የአበባ ጉንጉን በመያዝ አስከሬናቸውን አጀበዋል፡፡

የብፁዕነታቸው የቀብር ሥነ ሥርዓት ከቀኑ 6.00 ላይ የሀገረ ስብኩቱ መንበር በሆነው በፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም ተፈጽሟል፡፡