መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::




ሥጋ ለነባቢት ነፍስ እንድትታዘዝና የፈቲው ፆርም እንዲደክም- ጾም
በፍትሐ ነገሥት መንፈሳዊ አንቀጽ 15 እንደተገለጸው ቅዱሳን አባቶቻችን ሥጋ ለነባቢት ነፍስ እንድትታዘዝና የፈቲው ፆርም እንዲደክም የሚያደርግ የሰውን ልጅ ከእግዚአብሔር ጋር እንዲገናኝ የለመነውም ልመና መልስ እንዲኖረው የሰይጣንን ፍላጻ ለመስበር የሚያስችል ኃይል ያለው መሣሪያ ጾም ነው ብለው ጽፈዋል፡፡
ቅርሶችን በተመለከተ ዐውደ ጥናት ተካሔደ
ኅዳር 22/2004 ዓ.ም
የማይዳሰሱ ባሕላዊ ቅርሶች አያያዝ /አተገባበር/ ስምምነት በሀገር አቀፍ ደረጃ /Implementation of the Intangible cultural Heritage convention at national level/ በሚል ርዕስ ዐውደ ጥናት ተካሔደ፡፡ ዐውደ ጥናቱ የባሕልና ቱሪዝም ሚኒስቴር የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን ከተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም /UNESCO/ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ሲሆን፤ ከኅዳር 4-8/2004 ዓ.ም ድረስ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ለመካሔድ ችሏል፡፡ በዐውደ ጥናቱ ላይ የዩኒስኮ ተወካይ በሆኑት በፕሮፌሰር አማርሰዋር ጋላ እና በቅርስና ጥበቃ ባለስልጣን ባለሙያዎች ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡
የፍትሕ ነፃነትን የሚያስከብር የመንፈሳዊ ፍርድ ቤቶች ማጠናከሪያ ሕግ በቅዱስ ሲኖዶስ ጸደቀ
ኅዳር 22/2004 ዓ.ም
የፍትሕ ነፃነትን የሚያስከብር የመንፈሳዊ ፍርድ ቤቶች ማጠናከሪያ ሕግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሙሉ ድምጽ ማጽደቁ ተገለጸ፡፡
ሕጉ የጸደቀው የሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ጥቅምት 23 ቀን 2004 ዓ.ም ባደረገው ዓመታዊ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ላይ ሲሆን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ፣ 30ኛውን ዓመታዊ አጠቃላይ ሰበካ ጉባኤ ሲከፍቱ በአስተላለፉት ቃለ በረከት “ውኃው ከአጠገባቸው እያለ ተጠምተው የሞቱ ብዙ ናቸው” ብለዋል፡፡ አያይዘውም የሕግ ምንጭ የሆነችው የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች ፍትሕ ፍለጋ የዓለማዊውን ፍርድ ቤት ሲናፍቁና ሲያጨናንቁ ማየት ችግር መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ መፍትሔውም የዳኝነት ነፃነትን የሚያስከብረውን የሕግ ረቂቅ ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ማቅረብና ማጽደቅ በመሆኑም ይህንኑ ማድረግ መቻሉም በማኅበረ ክርስቲያኑ ፍትሕን ለማስፈን የቆመ የመሠረት አለት ነው ብለዋል፡፡
በስልጤና ሀድያ፣ ጉራጌ፣ ከንባታ ሀገረ ስብከት በፖሊሶች የፈረሰው የጋራሬ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በአክራሪ ሙስሊሞች ፍርስራሹ ተቃጠለ፡፡
ኅዳር 21/2004 ዓ.ም
፠በቃጠሎው ወንጀል የስልጤ ቲትጎራ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የስልጢ 2ኛ ደረጃ ተማሪዎች ተሳትፍበውታል፡፡
፠የስልጢ አረጋውያን ሙስሊሞች ድርጊቱን ተቃውመዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስልጤና ሀድያ፣ ጉራጌ፣ ከንባታ ሀገረ ስብከት በስልጤ ደብረ ስብሐት ቅድስት ማርያምና ቆቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ስር የተመሠረተው የጋራሬ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር 19 ቀን 2004 ዓ.ም ረፋድ ላይ በአክራሪ ሙስሊሞች ሙሉ ለሙሉ መቃጠሉን ለመረዳት ተችሏል፡፡
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምና ታቦተ ጽዮን
ኅዳር 20/2004 ዓ.ም
እግዚአብሔር አምላክ ሕዝበ እስራኤልን ከግብጽ ባርነት ካወጣቸው በኋላ የአምልኮ ሥርዐታትን ይፈጽሙበት ዘንድ የምስክሩን ድንኳን፣ የቃል ኪዳኗ ታቦትንና ለአምልኮ ሥርዐቱ ማከናወኛ የሚያገለግሉ ልዩ ልዩ ንዋያተ ቅድሳትን እንዲሠሩ በሙሴ በኩል ታዘው ነበር፡፡ ከቃል
ኪዳኗ ታቦት ውስጥም በእግዚአብሔር ጣት ዐሥርቱ ትእዛዛት የተጻፉበት የሕጉ ጽላት፣ አርባ ዓመት ሙሉ እስራኤላውያን በሲና ምድረ በዳ የተመገቡትን መና የያዘች መሶበ-ወርቅ፣ አሮን ለክህነት አገልግሎት ስለመመረጡ ምስክር የሆነችው ለምልማና ፍሬ አፍርታ የተገኘችው የአሮን በትር ይገኙባታል፡፡(ዕብ.9፡4)
በስልጤና ሀድያ ጉራጌ ሀገረ ስብከት የጋራሬ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በወረዳው ፓሊስ አባላት እንዲፈርስ መደረጉ ተገለጠ፡፡
ኅዳር 19/2004 ዓ.ም
• ቤተ ክርስቲያኑ የፈረሰው እኩለ ሌሊት እንደሆነም ታውቋል፡፡
• የስልጢ 2ኛ ከፍተኛ ደረጃ ተማሪዎች በቤተ ክርስቲያኑ መፍረስ እንዲተባበሩ እየተቀሰቀሱ ነው፡፡
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስልጤና ሀድያ ሀገረ ስብከት በስልጤ የጋራሬ ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር 15 ቀን 2004 ዓ.ም ዓርብ ለቅዳሜ አጥቢያ እኩለ ሌሊት ላይ በወረዳው የፓሊስ አባላት የመፍረስ አደጋ እንደተጣለበት ከክልሉ የደረሰን ማስረጃ አረጋገጠ፡፡
በስልጤ ዞን በስልጢ ወረዳ በቆቶ ባለሦ ቀበሌ በቆቶ መንደር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም የይዞታ ቦታው በሰነድ እንዲረጋገጥ የደብሩ ሰበካ ጉባኤ ለደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግሥት ለግብርና ገጠር ልማት ቢሮ ለተፈጥሮ ሀብትና የገጠር መሬት አስተዳደር ዘርፍ ባቀረበው ጥያቄ አግባብነት ያለው የመንግሥት የሥልጣን አካል በቀን 15/04/2003 ዓ.ም የይዞታ ማረጋገጫ ሰነዱን ለደብሩ ሰበካ ጉባኤ መስጠቱን መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ
ከዲ/ን መስፍን ደበበ እርሱ እናቴ እኔን ቅሪት እያማጠኝ፤በልጅነት ሊገላገል በሐሳብ ያረገዘኝ፤በማኅፀን ሰፋድሉ በትምህርቱ እኔን ስሎ፤በመዶሻው እኔን ጠርቦ አስተካክሎ፤እጄን ይዘህ አለማምደህ እንዲያ ስድህ፤ቃለ ነገር ቃለ ምሥጢር እየጋትህ፤ጠንካራውን ጥሬ ቃሉን አስቆርጥመህ፤አንተ አብይ ባሕር የትምህርት ውቅያኖስ፤ምርጥ ዕቃ ማዕዘን ዕብነ አድማስ፤በእንቁላል ቅርፊት ቀድቼ የረካሁኝ ከአንደበትህ፤ርዕሰ እውቀት አንተ አፈ ዝናም በትምህርትህ፡፡አሕዛበ-ምድር ማንነቴን በጠብታህ ጎበኘሃት፤የነፍሴን እርሻ አጥግበህ በልምላሜ ከደንካት፡፡ሕሊናዬን በተመስጦ መንኮርኩር […]
ቅዱስ እሰጢፋኖስ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አስተምህሮ
ስለ ቅዱስ እስጢፋኖስ ክፍል አንድን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
አይሁድን ቀርቦ ለመረመራቸውም አሕዛብ ከሆኑት ከፋርስ ወገን እንደሆኑ እንዲሁም አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ተአምራትን ሳይሻ ለእግዚአብሔር መከራዎቹን ሁሉ ታግሦና ተቋቁሞ የተመላለሰው እንደሆነ እግዚአብሔር ልጁ እንደሚያደርገው፣ እንዲሁም የሁሉ አባት አብርሃም እንዳደረገው የአባቶችን መቃብርና ያለንን ሁሉ በመተው ልንታዘዝ እንደሚገባንም ጠቁሞናል ፡፡
የአብርሃም አባትና ዘመዶቹ ምንም እንኳ ረጅም ጉዞ ከአብርሃም ጋር ቢጉዋዙም ከንዓንን ይወርሱ ዘንድ የተገባቸው ካልሆኑ ልጆቹስ ላይ እንዴት ይህ እጣ ፈንታ አይደርስባቸው ይሆን? “ነገር ግን ልጅ ሳይኖረው ለእርሱ ከእርሱም በኋላ ለዘሩ ርስት አድርጎ ይሰጠው ዘንድ ተስፋ ሰጠው፡፡” አለ፡፡ በዚህ የእግዚአብሔርን ድንቅ ስጦታንና የአብርሃምን እምነት ታላቅነት እንመለከታለን፡፡ “ልጅ ሳይኖረው” የሚለው አገላለጽ የእርሱን በእምነት መታዘዝን የሚገልጥ ነው፡፡ “ለእርሱ ከእርሱም በኋላ ለዘሩ ርስት አድርጎ ይሰጠው ዘንድ”የሚለው በድርጊት ከታየው ጋር ስናነጻጽር የተቃረነ መስሎ ይታየናል፡፡ ምክንያቱም አስቀድሞ “በዚችም የእግር ጫማ ስንኳ የሚያህል ርስት አልሰጠውም” እንዲሁም ልጅም አልነበረውም ይለናልና፡፡ እነዚህ ዐረፍተ ነገሮች አብርሃም በእምነቱ ከተሰጠው ጋር የሚጣጣሙ ላይመስሉን ይችላሉ፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር ሊሰጥ ያሰበውን ያንኑ ነው የሚሰጠው፡፡ በዚህ ቦታ ግን ቃሉና ድርጊቱ የተቃረኑ ይመስሉናል፡፡ ነገር ግን እንደ እኛ አስተምህሮ ፈጽሞ የሚጣረሱ አይደሉም፡፡ እንደውም ፈጽመው የሚጣጣሙ እንጂ፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በዚህ እንደምንደክም ነገር ግን እረፍታችን በላይ በሰማይ እንደሆነ አስተምሮናል፡፡ ስለዚህም ቅዱስ እስጢፋኖስ እንዲህ አለ፡፡
የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ያስገነባው ሕንፃ ተመረቀ
ዲ/ን ቴዎድሮስ ኃይሉ
• የብፁዕ አቡነ ቄርሎስ 25ኛ ዓመት የብር እዩቤልዩ በዓልም ተያይዞ ተከብሯል
{gallery count=1 width=350 height=300 counter=1 links=0 alignment=center animation=3000}abunekerilos{/gallery}
መልአከ ሐይል ስጦታው ሞላ በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ኃላፊ የአዳጎ ሕንፃ መሠራቱ ቤተ ክርስቲያኒቱ በስብከተ ወንጌል የምታደርገውን እንቅስቃሴ በጉልህ የሚደግፍ ነው ብለዋል ፡፡ የወልድያ ከተማ ከንቲባ አቶ ሓየሎም ጣውዬ በምረቃው ወቅት ‹‹ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሕዝቡን በእምነቱ የጸና፣ ሀገር ወዳድና በልማት ዋነኛ ተሳታፊ ለማድረግ እያከናወናቸው ያለው አበረታች የልማት ተግባራት መንግሥት ከያዛቸው የድኅነት ማስወገጃ ስትራቴጂዎች አንፃር የሚሄዱ ለመሆናቸው ምስክርነት የሚያሻው ጉዳይ አይደለም፡፡ ሀገረ ስብከቱ ከጀመራቸው የልማት ሥራዎች መካከል የወልድያ ከተማችን የኢንቬስትመንት እድገት የሚያሠራውን አዳጎ ላይ የተገነባው ሕንፃ ለሌሎችም አርአያ ከመሆን አልፎ ለብዙ ዜጎች የሥራ ዕድል ፈጥሮ ያለፈና አሁንም እየፈጠረ ያለነው ቢባል መጋነን አይሆንም ›› በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
የቅዱስ ኤፍሬም ቅኔያዊ መዝሙራት /ክፍል ሁለት/
ህዳር 14/2004 ዓ.ም
በዚህ ርእስ ግሩም የሆነውን የቅዱስ ኤፍሬም መጽሐፍ ቅዱስን የመረዳት ጸጋውን እንመለከታለን፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ለሰዎች በመጽሐፍ ቅዱስ በኩል ሲናገር የሰውን የአካል ክፍል እና ጠባይ ለራሱ በመጠቀም ነው፡፡ ይህ መዝሙር እንዴት የሰው ልጅ በእርሱና በእግዚአብሔር መካከል ያለውን ታላቅ የሆነውን ልዩነት አልፎ ስለእግዚአብሔር ባሕርያት ማወቅ ይችላል? ብሎ ይጠይቃል፡፡ በፈጣሪና በፍጡር መካከል ያለውን ልዩነት ቅዱስ ኤፍሬም ታላቅ ገደል ወይም ቅዱሱ ጸጥታ ብሎ ይጠራዋል፡፡ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም አስተምህሮ ለሰው የሚሰጠውን መጠሪያና ተፈጥሮ ለራሱ በመጠቀም በእርሱና በሰው መካከል ያለውን ሰፊ የሆነ ልዩነት ያጠበበው እግዚአብሔር ራሱ ነው፡፡ እንዲህ ማደርጉ ክብር ይግባውና ለሰው ልጆች ካለው ጥልቅ ፍቅር የተነሣ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን እግዚአብሔር ለሰው የሚሰጠውን መጠሪያና ጠባይ ለራሱ ተጠቅሞበት እናገኛለን፤ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም ትምህርት ደግሞ እንደ ልብስ ለብሶአቸው እናገኛቸዋለን፡፡