መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ደብረ ዘይት
መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም.
በአባ ዘሚካኤል ደሬሳ
የዓለሙ ፍጻሜ ምልክቱ ምንድ ነው?/ማቴ. 24፣3/
በዓቢይ ጾም ውስጥ ካሉት ሳምንታት ደብረ ዘይት 5ኛው ሳምንት ላይ ይውላል፡፡ ደብረ ዘይት ትርጉሙ የወይራ ዛፍ ተራራ ማለት ሲሆን፣ ይህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም በሚገኘው በደብረ ዘይት ተራራ ቅዱሳን ሐዋርያት” የዓለሙ ፍጻሜስ ምልክቱ ምንድነው?”/ማቴ. 24፣3/ ብለው ጠይቀውት እርሱም የማይቀረውን የዓለም ፍጻሜና አስቀድመው የሚፈጸሙ ምልክቶችን አስረድቷቸዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያንም ይህንኑ በደብረ ዘይት ሳምንት ታስበዋለች፤ ለምእመናኑም ከዘመኑ ሁኔታ አንጻር በመጻሕፍት የተጠቀሱትን የትንቢት ምልክቶቹን ከተግባራዊ የዓለም ክንዋኔዎች አንጻር በማገናዘብ ታስተምራለች፡፡ በመሆኑም በቤተ ክርስቲያናችን በደብረ ዘይት ሳምንት ምጽአትን አስመልክቶ የሚነገሩ ምስጢራት እጅግ ሰፊ ናቸው፡፡ ነገር ግን በዚህ ጽሑፍ በመጠኑ የምናየው ከቅዱሳት መጻሕፍት አንጻር በዓለም እየተከሰቱ ካሉ ወቅታዊ ምልክቶች ጋር በማገናዘብ ይሆናል፡፡
ዳግም ምጽአት(ለሕፃናት)
መጋቢት 26 ቀን 2005 ዓ.ም.
ቤካ ፋንታ
ልጆች እንደምን ሰነበታችሁ፡፡ በእኩለ ጾም /በጾሙ አጋማሽ/ ለምናከብረው ለደብረ ዘይት በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ፡፡ ልጆች ዛሬ የምንማረው ስለ ደብረ ዘይት በዓል ሲሆን ትምህርቱ በዋናነት ስለ ዳግም ምጽዓት ያስረዳል፡፡
ዳግም ምጽአት ማለት ለሁለተኛ ጊዜ መምጣት ማለት ነው፡፡ ይህም ማለት አምላካችን ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደገና ወደ እኛ የሚመጣበትን ቀን ያመለክታል፡፡ ልጆችዬ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ሰማያት ወርዶ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ ጊዜ ለፍጥረታት ሁሉ ለመጀመሪያ ጊዜ በግልጽ ታይቷል፡፡ በዳግም ምጽአት ጊዜ ደግሞ ሁሉም ሰዎች እያዩት እንደገና ስለሚመጣ ያቺ ቀን ዳግም ወደ እኛ የሚመጣበት ስለሆነች ዳግም ምጽአት ተባለች፡፡
“መራሔ ፍኖት” መንፈሳዊ ጉዞ ለግቢ ጉባኤያት ተዘጋጀ
መጋቢት 25 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል አስተባባሪነት በ60 ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሥር ለሚገኙ 5000 /አምስት ሺህ/ ግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች “መራሔ ፍኖት” /መንገድ መሪ/ የተሰኘ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ሱሉልታ ደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በዕለተ ሆሣዕና ሚያዚያ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ማእከል ዋና ጸሐፊ አቶ ካሳሁን ኃይሌ ገለጹ፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን የሚተላለፈው ቴሌቪዥን ዝግጅት የሰዓት ለውጥ ተደረገ
መጋቢት 25 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን የኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ዝግጅት ክፍል እየተዘጋጀ በNilesat/EBS የሚቀርበው የ30 ደቂቃ መርሐ ግብር በየሳምንቱ እሑድ ከጧቱ 3፡30-4፡00 ሲተላለፍ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ ሆኖም ሰዓቱ በቅዳሴ መጠናቀቂያ ላይ ይተላለፍ ስለነበር ለመከታተል አስቻጋሪ እንደሆነ ለክፍሉ ከሚደርሱት መልእክቶች ለመረዳት ተችሏል፡፡
“ተማሪ በሞተ በሰባት ዓመቱ ተምሮ ይመጣል ትላለች እናቱ”
ይህ ሥነ ቃል ከሞቀ ከደመቀ ቤቱ የላመ የጣመን ትቶ የነገው ካህን፣ መምህር፣ ሊቅ የመሆን ህልሙን ለማሳካት ቃለ እግዚአብሔር ፍለጋ የተሰደደው ተማሪ በረሃብ፣ በእርዛት፣ በሽታን መቋቋም ተስኖት ወደ ቤቱ አለመመለሱን ፤ወጥቶ መቅረቱን የተማሪውን መከራ ለማዘከር በሰፊው በማኅበረሰቡ ዘንድ የተነገረ ቃል ነው።
ምኲራብ
መጋቢት 18ቀን 2005 ዓ.ም.
በዳዊትደስታ
የዐብይ ጾም ሦስተኛው ሰንበት ምኲራብ ይባላል፡፡ ይህም ምኲራብ ከክርስቶስ ልደት በፊት እግዚአብሔርን ለማመስገን የእግዚአብሔር አማኞች ለጸሎት የሚሰባሰቡበት ቤት ስም ነው፡፡ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ጊዜ ወደ ምኲራባቸው በመግባት ሰዎችን አስተምሯል፡፡ ሰዎች የእግዚአብሔር መመስገኛ የሆነውን ምኲራብ ገበያ አድርገውት ስላገኘም “ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል ተብሎ ተጽፏል እናንተ ግን የሌባና የቀማኛ ዋሻ አደረጋችሁት” /ማቴ.21፥12-13/ በማለት ገሥጾ በዚያ የሚሸጡትንና የሚለውጡትን ሁሉ በትኗቸዋል፡፡ ይህንን ምክንያት በማድረግ ሦስተኛው የዐብይ ጾም ሳምንት ምኩራብ በሚል ሰያሜ ይጠራል፡፡ በምኲራብ ገብቶ እንዳስተማረ የሚያሳስብ ዕለት የሚነበበው የወንጌል ክፍልም ዮሐ.12 እስከ ፍጻሜው ያለው ነው፡፡
የሐዊረ ሕይወት ትኬት ሽያጭ ተጠናቀቀ!
በዚህ ጉዞ ለመርሀ ግብሩ ቅድመ ዝግጅት ሲባል ትኬቶች አሰቀድመዉ እንደሚጠናቀቁ የሚታወቅ ሲሆን መኪናዎችንና ምግብ ለማዘጋጀት እንዲያመች ትኬቱ ባያልቅ እንኳ በታቀደው መርሀ ግብር መሰረት ሽያጭ እንዲቆም ይደረጋል፡፡ ይሁንም እንጂ ከጉዞው አንድ ሳምንት አስቀድሞ የተዘጋጁት 5000 ትኬቶች ሙሉ በሙሉ የተሸጡ ሲሆን ትኬት ሽያጩም በተያዘው መርሀ ግብር መሰረት መጋቢት 16 /2005 ተጠናቅቋል፡፡ የጉዞ ኮሚቴው በየጊዜው እየጨመረ የመጣውን […]
የ ቆሙ መቃብሮች
መጋቢት 16 ቀን 2005 ዓ.ም.
በመ/ር ስምዓኮነ መላክ
መቃብር ሰዎች ሲሞቱ ወይም ነፍሳቸው ከሥጋቸው ሲለይ በክብር የሚያርፍበት ቦታ መቃብር ይባላል፡፡ መቃብር የሚላው ቃል የጎደጎደ ምድር ተብሎ ይተረጎማል፡፡ መዝ.14፥4፣ ኢሳ.22፥16 ሲዖልንም መቃብር ሲል ይገኛል፡፡ መትሕተ ታሕቲት ናትና፡፡
በማን ጊዜ እንደተጀመረ ባይታወቅም የሚቀበሩት በርስትነት በያዙት ቦታ ነበር ዘፍ.13፡፡ ያ ልማድ ሆኖልን ዛሬም በአዲስ ኪዳን የምንኖር ክርስቲያኖች እንደ አባቶቻችን ሁሉ በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ እንቀበራለን፡፡ ስለምን ቢሉ ሥጋውን ደሙን የበላንበትና የጠጣንበት ብቸኛዋ ርስታችን በምድር ቤተ ክርስቲያናችን ናትና ነው፡፡
ቅድስት
መጋቢት 12 ቀን 2005 ዓ.ም.
በአባ አሥራተ ማርያም ደስታ
የማቴ.6፥16-24 ምንባብ በአንድምታ ትርጓሜ
ቁ.16. በምትጾሙበት ጊዜ እንደ ግብዞች አትሁኑ፡፡ እነዚያ ፊታቸውን አጠውልገው ግንባራቸውን ቋጥረው ሰውነታቸውን ለውጠው ይታያሉና፡፡ እንደ ጾሙ ሰው ያውቅላቸው ዘንድ የወዲህኛውን ውዳሴ ከንቱ አገኙ የወዲያኛውን ዋጋቸውን አጡት ብዬ በእውነት እነግራችኋለሁ፡፡
ዘወረደ
መጋቢት 12 ቀን 2005 ዓ.ም.
በአባ አሥራተ ማርያም ደስታ
የዮሐ.3፥10-21 ምንባብ በአንድምታ ትርጓሜ
ቁ.11. ራሱን ከዮሐንስ አግብቶ፡፡ ያየነውን፣ የሰማነውን እናስተምራለን ብዬ እንድናስተምር በእውነት እነግርሃለሁ፡፡ ምስክርነታችንን ግን አትቀበሉም፡፡
ቁ.12. ምድራዊ ልደታችሁን ስነግራችሁ ብነግራችሁ ያልተቀበላችሁኝ ሰማያዊ ልደታችሁን ብነግራችሁ እንደምን ትቀበሉኛላችሁ፡፡ ለዚህ ምክንያት አለው በጥምቀት፣ በንፍሐት ይሰጣል፡፡ ለዚያ ግን ንቃሕ ዘትነውም ባለው ነው፡፡ ምክንያት የለውምና፡፡