መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የ5ቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እጩ ፓትርያርኮች አጭር የሕይወት ታሪክ
የካቲት 19 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ኅሩይ ባየ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስድስተኛውን ፓትርያርክ ለመምረጥ በዝግጅት ላይ እንደምትገኝ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት ቅዱስ ሲኖዶስ አስመራጭ ኮሚቴ በመሠየም እጩ ፓትርያርኮችን ለመምረጥ ከብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ከካህናት፤ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች፤ ከማኅበረ ቅዱሳን፤ እንዲሁም ከምእመናን ጥቆማ እንዲያካሒዱ ተደርጓል፡፡ አስመራጭ ኮሚቴው ጥቆማውን በግብአትነት በመጠቀም አምስት ሊቃነ ጳጳሳትን በእጩነት በማቅረብ የካቲት 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ አቅርቧል፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤም ከየካቲት 16 – 18 ቀን 2005 ዓ.ም. ድረስ ውይይት በማካሔድ አምስቱም ሊቃነ ጳጳሳት በእጩነት እንዲቀርቡ አጽድቋል፡፡ የካቲት 21 ቀን 2005 ዓ.ም. ለሚካሔደው የስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የፓትርያርክ ምርጫ የቀረቡት ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት፡- ብፁዕ አቡነ ማትያስ በኢየሩሳሌም የኢትዪጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የምዕራብና የደቡብ አዲስ አበባና የከፋ ቤንች ማጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የወላይታና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት አጭር የሕይወት ታሪካቸውን እንደሚከተለው እናቀርባለን፡-
አምስቱ እጩ ፓትርያርኮች ታወቁ
የካቲት 19 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ÷ አስመራጭ ኮሚቴ ዛሬ የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ÷ አምስቱ እጩ ፓትርያርኮችን ይፋ አደረገ፡፡
የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ሊካሔድ ነው
የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን በ2005 ዓ.ም. የሐዊረ ሕይወት /የሕይወት ጉዞ/ የተሰኘውና ወደ ቅዱሳን መካናት፤ አድባራትና ቤተ ክርስቲያናት የሚያካሄደውን የጉዞ መርሐ ግብር በሆለታ ደብረ ኤዶም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን መጋቢት 22 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደሚያካሄድ የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ዋና ጸሐፊና የጉዞው አዘጋጅ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ተሾመ ገለጹ፡፡
ፍርድ ለነነዌ÷ ሥልጣን ለነነዌ
የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኩኖአምላክ
ኮናኔ በርትዕ÷ ፈታሄ በጽድቅ÷ የሆነው መድኀኒዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ጻፍት ፈሪሳውያንን በቋንቋቸው በዕብራያስጥ ቢያስተምራቸው “እንደ ሙሴ፡- ባሕር ከፍለህ÷ ጠላት ገድለህ÷ ደመና ጋርደህ÷ መና አውርደህ፣ እንደ ኢያሱ፡- በረድ አዝንመህ÷ ፀሐይ አቁመህ÷ እንደ ጌዴዎን፡- ፀምር ዘርግተህ ጠል አውርደህ፣ እንደ ኤልያስ ሰማይ ለጉመህ እሳት አዝንመህ ልታሳየን እንወዳለን” የሚል ጥያቄ በቀረበለት ጊዜ የሰጣቸው ምላሽ “ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል÷ ከነቢዩ ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ በዓሣ አንበሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ÷ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል፡፡ የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈረዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና÷ እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ” የሚል ነው፡፡ ጻፍት ፈሪሳውያንን ምልክት ያስፈለጋቸው ዋነኛ ምክንያት በጌታችንና በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የባሕርይ አምላክነት ለማመን አልነበረም፤ ይልቅስ እንደ ዘማ ሴት ምልክት በምልክት እየተደራረበ ማየትን በመናፈቅ ነው፡፡
ማዕከሉ ዐውደ ጥናት ሊያካሂድ ነው
የካቲት 18 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ዮሴፍ ይኲኖ አምላክ
የጥናትና ምርመር ማዕከል በሁለት ታላላቅ ርእሶች ላይ ያዘጋጀውን ዐውደ ጥናት የካቲት 23 ቀን 2005 ዓ.ም በብሔራዊ ሙዚየም አዲሱ አዳራሽ ውስጥ እንደሚያካሂድ አስታወቀ፡፡
ጥናታዊ ጽሁፍ፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን፤ የዓድዋ ድልና አንድምታው
ኪዳነ ምሕረት
የካቲት 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በዲ/ን ኀይለ ኢየሱስ ቢያ
“ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ” 88፥3 በማለት በነቢዩ ቅዱስ ዳዊት አድሮ ራሱ እግዚአብሔር ከመረጣቸው አበው ነቢያት ጻድቃን ቅዱሳንና ሰማዕታት ጋር ቃል ኪዳን እንደ ገባና እንደሚገባ ተናግሯል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም እግዝአብሔር እንደሚጠራ እንደሚያከብር እንደሚቀድስ ቃል ኪዳን እንደሚሰጥ ነግሮናል፡፡ /እንግዲህ እርሱ ራሱ ከጸደቀ እግዚአብሔር የመረጣቸውን ሰዎት የሚቃወማቸው ማን ነው? ብሏል፡፡ ሮሜ.8፥33
መመለስ /ክፍል ሁለት/
የካቲት 15 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ዝምታቸው አስፈራኝ፡፡ “እባክዎ አባቴ ይርዱኝ” አልኩ የሰፈነውን ጸጥታ ሰብሬ፡፡
ዐይኖቻቸውን ከመስቀላቸው ላይ ሳይነቅሉ ‹‹ልጄ ነገ ከእኔ ስላለመኮብለልህ ምን ማረጋገጫ አለኝ?” ስጋታቸውን ገለጹ፡፡
“አመጣጤ የመጨረሻዬ ይሆን ዘንድ ነው፡፡ ውስጤ ተሰብሯል፡፡ ታከተኝ አባቴ!” የተቋረጠው የዕንባ ጎተራዬን ነካካሁት፡፡ ይፈልቅ ጀመር፡፡
ለመወሰን ተቸግረው በትካዜ ከያዙት የእጅ መስቀላቸው ጋር የሚሟገቱ ይመስል እያገላበጡት ዝምታን መረጡ፡፡
እኔ ደግሞ ውሳኔያቸው ናፈቀኝ፡፡ መልስ እሰኪሰጡኝ ድረስ እኔም በለቅሶና በዝምታ አገዝኳቸው፡፡
“አንድ ነገር ታደርጋለህ፡፡” ቀና ብለው እንኳን አላዩኝም፡፡ ዐይኖቻቸውን መስቀላቸው ላይ ተክለዋል፡፡
“ከቃልዎ አልወጣም – የፈለጉትን ይዘዙኝ፡፡”
ነቢዩ ዮናስ (ክፍል ሁለት) /ለሕፃናት/
የካቲት 14 ቀን 2005 ዓ.ም.
በወልደ ኢየሱስ /ቤካ ፋንታ/
እግዚአብሔር በጣም የሚወዳችሁ እናንተም እግዚአብሔርን በጣም የምትወዱት ሕፃናት እንደምን ሰነበታችሁልን?
ልጆችዬ ባለፈው በክፍል አንድ ጽሑፍ ስለ ደጉ ልጅ ስለ ዮናስ የተማርነውን ታስታውሳላችሁ? ዮናስ ለእግዚአብሔር ባለመታዘዙ ምክንያት በባሕር ላይ የሚሄድባት መርከብ ከባድ ችግር ደርሶባት ነበር፡፡ መጨረሻ ላይ ዮናስን ወደ ባሕር ውስጥ ሲጥሉት ንፋሱ ቆመ፡፡ መርከቧም በሰላም መሄድ ቻለች፡፡ ዮናስ ግን ወደ ስምጡ ባሕር እንደገባ አይተን ነበረ ያቆምነው፡፡ ዛሬ ካቆምንበት እንቀጥላለን፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን የቴሌቪዥን መርሐ ግብር እሁድ ይጀምራል
የካቲት 13 ቀን 2005 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ዋና ክፍል እየተዘጋጀ የሚቀርበው የቴሌቪዥን መርሐ ግብር እሑድ የካቲት 17 ቀን 2005 ዓ.ም. ከጠዋቱ 3፡30 – 4፡00 ሰዓት ድረስ በናይል ሳት ኢቢኤስ ላይስርጭቱን እንደሚጀምር ተገለጸ፡፡