መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ አጠናቀቀ፡፡
ጉባኤው ከጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ላለፉት 10 ቀናት ተወያይቶ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች አስመልክቶ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በተገኙበት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ የመግለጫውን ሙሉ ቃል እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡
የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር እንደሚካሔድ ተገለጸ
ጥቅምት 19 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ማኅበረ ቅዱሳን ሐዊረ ሕይወት /የሕይወት ጉዞ/ የተሠኘውንና ምእመናንን በማሳተፍ በተመረጡ ቅዱሳት መካናት የሚያካሒደውን መርሐ ግብር ታኅሣሥ 6 ቀን 2006 ዓ.ም. በደብረ ዘይት ደብረ መድኀኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን እንዳዘጋጀ የመርሐ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ ገለጸ፡፡
አቶ ግርማ ተሾመ የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ዋና ጸሐፊና የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዝግጅቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ በመርሐ ግብሩ ላይ ከ5000 በላይ ምእመናን ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና የቲኬት ሽያጩንም በማሰራጨት ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡ ምእመናን ቲኬቱን በማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ጽ/ቤት፤ በማኅበሩ የንዋያተ ቅዱሳት ማከፋፈያና መሸጫ ሱቆች እንደሚያገኙ የተናገሩት አቶ ግርማ የቲኬት ሽያጩም ኅዳር 25 ቀን 2006 ዓ.ም. እንደሚጠናቀቅ አሳውቀዋል፡፡
ቅዱስ ሲኖዶስ ችግሮችን በውይይት መፍታት እንዳለበት ተገለጸ
ጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ቅዱስ ሲኖዶስ ችግሮችን በውይይትና በውይይት ብቻ በጋራ የመፍታት ባሕልን መደገፍና ማጎልበት እንደሚገባው ተገለጸ፡፡
በዛሬው ዕለት ጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ከመጀመሩ በፊት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በአሁኑ ጊዜ በጥልቀት፣ በማስተዋልና የሓላፊነት መንፈስ በተላበሰ ወኔ፣ አጥብቆ ሊወያይባቸውና ሊወስንባቸው፤ ከውሳኔ በኋላም ለተግባራዊነታቸው ሊረባረብባቸው የሚገቡ በርከት ያሉ ጉዳዮች እንዳሉ አመልክተዋል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ መክፈቻ በምሕላ ጸሎት ተጀመረ
ጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. በእንዳለ ደምስስ የጥቅምት 2006 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው እለት ጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ ዐሥር ሰዓት ጀምሮ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በምሕላ ጸሎት ተጀመረ፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከጥቅምት 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በሚያካሒደው […]
ለቅዱሳን ፓትርያርኮችና ለብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐት ተደረገ
ጥቅምት 8 ቀን 2006 ዓ.ም. በእንዳለ ደምስስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ሲመሩ ለነበሩና ከዚህ ዓለም በሞት ለተለዩ ቅዱሳን ፓትርያርኮችና ሊቃነ ጳጳሳት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጥቅምት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. የመታሰቢያ ጸሎተ ፍትሐትና ቅዳሴ ተካሔደ፡፡ በጸሎተ ፍትሐትና ቅደሴ ሥነ ሥርዓት ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም […]
መንፈሳዊ ኮሌጆች ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት ሊኖራቸው እንደሚገባ ተጠቆመ
ጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም.
በይብረሁ ይጥና
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥር የሚገኙት መንፈሳዊ ኮሌጆች አንድ ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርትና የትምህርት ጥራት ሊኖራቸው እንደሚገባ ተገለጠ፡፡
ከጥቅምት 4-11 ቀን 2006 ዓ.ም. በተካሄደው የ32ኛ መንፈሳዊ የሰበካ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ ላይ በተሳታፊዎች ተደጋግሞ እንደተነሣው የአቋም መግለጫው እንደሚያመለክተው የቅድስት ሥላሴ፣ የሰዋሰወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስና የቅዱስ ፍሬምናጦስ አባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጆች በርካታ ደቀ መዛሙርትን ድኅረ ምረቃ፣ በዲግሪ፣ ዲፕሎማና ሠርተፍኬት በማስተማር እንደሚያስመርቁ ተገልጿል፡፡
ሲያሳድዷችሁና ሲነቅፏችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን በውሸት ሲናገሩባችሁ ብጹዓን ናችሁ፡፡ ማቴ 5፡11
ጥቅምት 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 32ኛው የሰበካ መንሳዊ ጉባኤ ከጥቅምት 4 ቀን 20006 ዓ.ም. ጀምሮ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ በመካሔድ ላይ ይገኛል፡፡ በጉባኤው ላይ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ አኅጉረ ስብከት እንዲሁም የልዩ ልዩ መምሪያዎች ሪፖርቶች ቀርበዋል፡፡
በአንድ ሀገረ ስብከትም ማኅበረ ቅዱሳንን በሚመለከት የቀረበው ሪፖርት በቦታው የነበሩ አንዳንድ የቤተ ክርሰቲያን አባቶችንና ተሳታፊዎች ላይ ብዥታን ሲፈጥር አስተውለናል፡፡ በተለያየ አጋጣሚም ስለጉዳዩ በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚህም መሠረት ከሪፖርቱ ጋር በተያያዘ የተፈጠረውን ብዥታ ለማጥራትና ማኅበሩ ላይ የቀረበውን ጉዳይ አስመልክቶ ምላሽ እንዲሰጡን ከማኅበሩ ሰብሳቢ ቀሲስ ዶ/ር ሰሙ ምትኩ ጋር ቆይታ አድርገናል፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን አባላት በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ እየገቡ የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር ያዳክማሉ በማለት በአንድ ሀገረ ስብከት ዘገባ ላይ ቀርቧል፡፡ ይህንን በሚመለከት ማኅበሩ ምን ምላሽ አለው?
ግልጽነትና መገማገም የቤተ ክርስቲያኗ ባሕል መሆን ይገባዋል ተባለ
ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም.
ያለንበት ዘመን የግልጽነትና የመገማገም ዘመን ስለሆነ በሁሉም የቤተ ክርስቲያኗ አካላትና ደረጃዎች ሊለመድ የሚገባው ባሕል እንዲሆን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ገለጹ፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ይህንን ያሉት 32ኛው የቤተ ክርስቲያኗ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በመንበረ ፓትርያርክ ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሲያካሔድ የነበረውን ጉባኤ የዕለት ውሎ ባጠናቀቀበት ጊዜ ነው፡፡
የ32ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ቃለ ጉባኤ ቀረበ
ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም.
ከጥቅምት 4 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ ሲካሔድ የሰነበተው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እየተገባደደ ነው፡፡ በዛሬው የከስዓት በፊት መርሐ ግብር ጉባኤው ሲወያይባቸው በሰነበተው ዝርዝር ጉዳዮች ቃለ ጉባኤ በንባብ ተሰምቷል፡፡ በቃለ ጉባኤው ከቀረቡት ዝርዝር የጉባኤው አካሔድ ዘገባ በተጨማሪ ጉባኤው የተስማማባቸውና ቅዱስ ሲኖዶስ ይወስነባቸው ዘንድ የቀረቡ ነጥቦች ተካተዋል፡፡ ይሁን እንጂ ቃለ ጉባኤው በንባብ ከተሰማ በኋላ እንደበፊቱ ጉባኤው ተወያይቶ ማሻሻያ አላደረገባቸውም፡፡ ለዚህም የተሰጠው ምክንያት የጊዜ እጥረት የሚል ሲሆን፤ የጉባኤው አባላትና ተሳታፊዎች በተሰማው ቃለ ጉባኤ ላይ ያላቸውን የማስተካከያና የማሻሻያ ሀሳቦች በጽሑፍ ለቃለ ጉባኤ አርቃቂ ኮሚቴው እንዲሰጡ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል፡፡
በሁሉም አኅጉረ ስብከት ብልጫ ያለው ሀገረ ስብከት ተሸለመ
ጥቅምት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀገር ውስጥ ካሏት 50 አኅጉረ ስብከት በልዩ ልዩ መመዘኛዎች በ2005 ዓ.ም. የሥራ ብልጫ ያሳየው የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት አንደኛ ተብሎ ተሸለመ፡፡ በ32ው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ከየአኅጉረ ስብከቱ የቀረቡትን ሪፖርቶች ገምግሞ ተሸላሚውን የለየው ለዚሁ ተግባር በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ ቤት የተቋቋመው ኮሚቴ ነው፡፡ ኮሚቴው […]