አትሮንስ የመጻሕፍት ንባብ ውይይት ተካሔደ

ጥር 6/2006 ዓ.ም.

በማኅበረ ቅዱሳን የኤዲቶያል ቦርድ መጻሕፍት አርትኦት ክፍል አማካኝነት በየወሩ የሚቀርበው አትሮንስ የመጻሕፍት ንባብ ውይይት ጥር 4 ቀን 2006 ዓ.ም. በማኅበሩ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተካሔደ፡፡

በዕለቱ ለውይይት የቀረበው መጽሐፍ በመጋቤ ሐዲስ ሮዳስ ታደሰ ተርጓሚነት የተዘጋጀው የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ የሰባቱ ጊዜያት የሃይማኖትና የጸሎት መጽሐፍ ሲሆን መጽሐፉን ገምግመው ለውይይት ያቀረቡት ዲ/ን አሻግሬ አምጤ ናቸው፡፡ ውይይቱ ከመጽሐፉ ኅትመት ጥራት፣ ይዘት፣ አቀራረብና ከዋቢ መጻሕፍት አጠቃቀም አንጻር ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በማንሳት ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ የጉባኤው ተሳታፊዎችም ከውይይቱ ትምህርትና ልምድ ለመቅሰም እንዳስቻላቸው ጠቁመው፤ ይህ በየወሩ የሚካሔደው የመጻሕፍት ውይይት ቀጣይነት እንዲኖረውና ሌሎችም መጻሕፍት አዘጋጆች ቢጋበዙ መልካም እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በቀጣይነት የአትሮንስ የመጻሕፈት ንባብ መርሐ ግብር ውይይት የሚደረግበት መጽሐፍ “የኢትዮጵያ እምነት በሦስቱ ሕግጋት” የሚለው የአለቃ አያሌው ታምሩ እንደሆነ ከክፍሉ አስተባባሪ ለማወቅ ተችሏል፡፡