06Epiphany19

የከተራ በዓል በጃንሜዳ በድምቀት ተከበረ

  ጥር 10/2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ 

የከተራ በዓል በጃን ሜዳ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቀነ ጳጳሳት፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዘምራንና ምእመናን እንዲሁም የተለያዩ የውጭ ሀገራት አምባሳደሮችችና ሀገር ጎብኚዎች በተገኙበት በድምቀት ተከበረ፡፡06Epiphany19

06Epiphany20ከአሥራ አንድ ታቦታት በላይ ከየአብያተ

ክርስቲያናት በክብር በመውጣት በዝማሬና በእልልታ እንደታጀቡ ወደ ጃንሜዳ አምርተዋል፡፡ የእለቱ ተረኛ አዘጋጅ የሆነው የደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን “ወረደ ወልድ እምሰማያት ውስተ ምጥማቃት፤ በፍስሐ ወበሰላም” በማለት እለቱን06Epiphany18 በማስመልከት ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡ የደብሩ ፍቁረ እግዚእ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላትም “በሰላም አስተርዐየ፡ አስተርዐየ ወልደ አምላክ፤ ወተወልደ በሀገረ ዳዊት ተወልደ፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ ከመይቤ ዘወነ” እያሉ ዝማሬ በማቅረብ በዓሉን አድምቀውታል፡፡

06Epiphany15

ስለበዓሉ አከባበር ከሰሜን አሜሪካ የመጣችው ሀገር ጎብኚ በዓሉን አስመልከተን ላቀረብንላት ጥያቄ ስትመልስ “ከዚህ በፊት ለአንድ ጊዜ የመስቀልን በዓል አከባበር ተመልክቼ ነበር፡፡ እሰከዛሬም ከምደነቅባቸው ሃይማኖታዊ በዓላት አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ የጥምቀት በዓላችሁ ደግሞ የተለየ ነው፡፡ ልታከብሩትና ልትኮሩበት ይገባችኋል” ስትል አስተያየቷን ሰጥታለች፡፡

06Abune Mathias

 

በመጨረሻም ቅዱስነታቸው በሰጡት ቃለ ምእዳን “ጌታን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ መጣ፡፡ ለአምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመናት በላያችን ተጭኖ የነበረውን መርገመ ነፍስ መርገመ ሥጋን አስወግዶ በረከተ ነፍስ በረከተ ሥጋን ለማደል በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ ኃጢዓታችንንም አስወገደ፡፡ ከዲያብሎስ ቁራኝነትም አላቀቀን፡፡ ወደ ወገኖቹ መጣ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም፡፡ ነገር ግን ለተቀበሉት የእግዚአብሔር ልጅ መባልን ሰጣቸው፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን የመንግሥቱ ወራሾች እንድንሆን የተጠራነው በጥምቀት ነው” ብለዋል፡፡