መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመዋቅር፣ አደረጃጀትና አሠራር ረቂቅ መመሪያ ርክክብ ተካሔደ
የካቲት 6 ቀን 2006 ዓ.ም.
በመምህር ሳሙኤል ተስፋዬ
መንፈሳዊ ጉባኤ በባሕር ዳር ከተማ
ጾመ ሰብአ ነነዌ
የካቲት 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
ርዕሰ ደብር ብርሃኑ አካል
ጾመ ነነዌ ከአዋጅ አጽዋማት አንዱ ሲሆን የምትጾመውም ለሦስት ቀናት ነው፡፡ ጾሙ የሚጀመርበት ዕለትም ልክ እንደ ዐቢይ ጾም ሰኞን አይለቅም፡፡ ጾሙ የሚጀመርበት ቀን ደግሞ ሲወርድ ወይም ወደ ኋላ ሲመጣ እስከ ጥር 17 ቀን ድረስ ነው፡፡ ሲወጣ ወይም ወደፊት ሲገፉ ደግሞ እስከ የካቲት 21 ድረስ ነው፡፡ በእነዚህ 35 ቀናት/ዕለታት/ ስትመላለስ ትኖራለች፡፡ ከተጠቀሱት ዕለታት አይወርድም አይወጣም ማለት ነው፡፡
የሦስት ቀኑን ጾም የጾሙት በነነዌ ይኖሩ የነበሩ ሕዝቦች ሲሆኑ ከተማዋ በጤግሮስ ወንዝ ዳርቻ የምትገኝ መሥራቿም ናሞሩድ ነው፡፡ ዘፍ.10፥11-12 ጥንታዊቷ የነነዌ ከተማ ለአሦር መነሻ የሆነ ከተማ እጅግ ሰፊና ያማረ ፤ የከተማው ቅጥር ርዝመት አሥራ ሁለት ኪሎ ሜትር ነበር፡፡ ሰናክሬም ብዙ ሕንፃዎችንም ሠርቶበት ነበር፡፡ /ዮናስ. 4፥11/
ሕይወት ተገለጠ አይተንማል
የካቲት 3 ቀን 2006 ዓ.ም.
ዲ/ን ታደለ ፈንታው
ስለሕይወት ቃል ከመጀመሪያ የነበረውንና የሰማነውን በዓይኖቻችንም ያየነውን የተመለከትነውም እጆቻችንም የዳሰሱትን እናወራለን፡፡ ሕይወትም ተገለጠ አይተንማል፡፡እንመሰክራለንም፡፡/1ኛ ዮሐ 1፡1/
ቅዱስ ዮሐንስ በቀዳማይ መልእክቱ ለዓለም የሚያስተዋውቀው ሕይወት ዓለም የማያውቀው አስቀድሞ ከእግዚአብሔር አብ ዘንድ የነበረ በኋለኛው ዘመን ሰው ይሆን ዘንድ ሥጋን ተዋሕዶ በምድር ላይ ይመላለስ ዘንድ የወደደ፣ ከአብ ዘንድ የነበረውን፣ ለእኛም የተገለጠውን ሕይወት ነው፡፡ አስቀድሞ በወንጌሉ ይህንን ሕይወት ‹‹ በመጀመሪያ ቃል ነበረ፤ ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ ነበረ ቃልም እግዚአብሔር ነበረ፤ ሁሉ በእርሱ ሆነ ከሆነው አንዳች ስንኳ ያለእርሱ አልሆነም/ዮሐ 1፡1/ በማለት የገለጠው ነው፡፡
ወንጌላዊው ከመጀመሪያ የነበረውን ሲል እያስተማረን ያለው ቀዳማዊ ቃል ዘመን የማይቆጠርለት መሆኑንና በየዘመናቱ የሰራው ታላቅ ሥራ መገለጡን የሚያመለክት ነው፡፡ እርሱ ከባህርይ አባቱ ከእግዚአብሔር አብ ጋር ህልው ሆኖ የሚኖር ነው፡፡ አይቀዳደሙም፣ ወደኋላ አይሆኑም፡፡ አብን መስሎ አብን አክሎ የተወለደ ነው፡፡ በኅላዌ ፣በአገዛዝ፣ በመለኮት፣ በአገዛዝ፣ በመለኮት፣ ከባሕርይ አባቱ ጋር የተካከለ ነው፡፡
የሰናፍጭ ቅንጣትማቴ 13÷31
ጥር 30 ቀን 2006 ዓ.ም.
ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መላክ
በምዕ/ጎጃም ሀገረ ስብከት
የ፬ቱ ጉባኤያት መምህር
ታላቅነትን በታናሽነት ሰውራ የያዘች እንከን የለሽ፤ዙሪያዋን ቢመለከቷት ነቅ የማይገኝባት አስደናቂ ፍጥረት ናት፡፡ የሰናፍጭ ቅንጣት፡፡ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስወንጌልን በምሳሌ ካስተማረባቸው መንገዶች አንዱ ሰናፍጭ ነው፡፡ ስትዘራ ታናሽነቷ ስትበቅል ግን ታላቅነቷ የገዘፈ ምሥጢር ያለው በመሆኑ ለዚህ ተመርጣለች በመጽሐፍ እንደተባለ ሰናፍጭ ስትዘራ እጅግ ታናሽናት ስትበቅል ግን ባለብዙ ቅርንጫፍ እስከመሆን ደርሳ ታላቅ ትሆናለች ከታላቅነቷ የተነሳ እጅግ ብዙ አእዋፍ መጥተው መጠጊያ እንደሚያደርጓትም አብሮ ተገልጿል አሁን ታናሽነቷን በታላቅነት መሰወር ችላለችና ብዙዎችን ልታስገርም ትችላለች፡፡
የአብነት መምህራን የምክክር ጉባኤ ሊካሄድ ነው፡፡
ጥር 29 ቀን 2006 ዓ.ም.
በታመነ ተ/ዮሐንስ
የማኅበረ ቅዱሳን የቅዱሳት መካናት ልማትና ማኅበራዊ አገልግሎት ዋና ክፍል የአብነት መምህራን የምክክር ጉባኤን ለሦስተኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሊያካሂድ ነው፡፡ መርሐ ግብሩ ከየካቲት 6 እስከ 9 ቀን 2006 ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት ይከናወናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በመርሐ ግብሩ ይዳሰሳሉ ተብለው ከተያዙ አጀንዳዎች መካከል የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነጻ የትምህርትና ሥልጠና ዕድል፣ የአብነት ት/ቤቶች የጤና ግንዛቤን ባካተተ እና ትርጓሜ መጻሕፍትን በተመለከተ በዋነኝነት የሚነሡ ርዕሰ ጉዳዮች ሲሆኑ፤ የአብነት ት/ቤቶች የምስክር አሰጣጥና የአገልግሎት ሁኔታ እና ሌሎች ተዛማጅ ርዕሰ ጉዳዮችም ይወሳሉ፡፡
ሐዋርያዊ ጉዞ በምሥራቅ ኢትዮጵያ
ጥር 29 ቀን 2006 ዓ.ም.
በማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል አስተባባሪነት ከጥር ፲፮ እስከ ፳፭ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ለአሥር ተከታታይ ቀናት በምሥራቅ ኢትዮጵያ ሲካሔድ የሰነበተው ሐዋርያዊ ጉዞ ተጠናቀቀ፡፡
በሐዋርያዊ ጉዞው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ክፍል አባላትን ጨምሮ የማኅበረ ቅዱሳን መምህራን፣ መዘምራንና ጋዜጠኛ በድምሩ ሃያ አራት አባላት ያሉት የልዑካን ቡድኑ መነሻውን ከዋናው ማእከል ማኅበረ ቅዱሳን በማድረግ በአፋር፣ ድሬዳዋ፣ ምሥራቅ ሐረርጌና ሱማሌ ሀገረ ስብከት በመዘዋወር ሰፊ የስብከትና መዝሙር አገልግሎት ፈጽሞ ጥር ፳፮ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ሲመለስ የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል አባላት ደማቅ አቀባበል አድርገውለታል፡፡
ገነትህን ጠብቅ ዘፍ.2፡15
ጥር 26 ቀን 2006 ዓ.ም.
ሊቀ ሊቃውንት ስምዐ ኮነ መላክ
በምዕ/ጎጃም ሀገረ ስብከት
የ፬ቱ ጉባኤያት መምህር
እግዚአብሔር አምላክ ሰውን ካሰለጠነባቸው ስፍራዎች መካከል አንዱ ኤዶም ገነት ነች፡፡ ታላቁ መጽሐፍ እንደሚነግረን “እግዚአብሔር አምላክም በስተምስራቅ ኤዶም ገነትን ተከለ የፈጠረውንም ሰው በዚያ አስቀመጠው” ካለ በኋላ ገነትን እንዲጠብቃትና እንዲንከባከባት ሓላፊነትን ሰጥቶታል፡፡
ገነት የአራቱ አፍላጋት መነሻ ሰው ከፍሬው ተመግቦ ለዘለዓለም ሕያው የሚሆንበት የዕፀ ሕይወት መገኛ ነበረች፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሐዋርያው አትናቴዎስ በቅዳሴው ስለገነት ውበት ሲገልፅ ዕፅዋቶቻቸው ቅጠላቸው እስከ 15 ክንድ ይደርሳል፡፡ መዓዛቸው ልብን ይመስጣል፡፡ ፍሬአቸው ከጣዕሙ የተነሣ ሁሌም ከአፍ አልጠፋም ብሎ ነበር፡፡
ንዋያተ ቅዱሳቱ የማን ናቸው?
ጥር 26 ቀን 2006 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዜማ መሣሪያዎች ከቅዱስ ያሬድ ጀምሮ በርካታ ሊቃውንት ሲያገለግሉበት የነበረና የሰማያዊውን የዝማሬ ሥርዓት መነሻ ያደረገ፣ ሰማያዊውንም ዓለም የሚያሳስብ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃልም መነሻ ተደርጎ የተመረጠ፣ ኢትዮጵያዊ መልክ ኖሯቸውም የተዘጋጁ ናቸው፡፡
እነዚህ የዜማ መሣሪያዎች ቤተክርስቲያናችን ይዛ በምትጠቀምበት ቅርጽና ይዘት የሚገኙት በኢትዮጵያና ኢትጵያውያን እጅ ብቻ ነው፡፡ ይልቁንም ደግሞ የአንድ ቤተ ሃይማኖት ማለትም የኦርቶዶክስ ሃይማኖት መጠቀሚያ ሆነው እያገለገሉ ያሉ ናቸው፡፡
ሕገ ወጥ ልመናን የሚያስፋፉ ግለሰቦች ላይ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠቆመ፡፡
ጥር 26 ቀን 2006 ዓ.ም.
በቅርቡ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በቤተ ክርስቲያን ዕድሳት ስም ፈቃድ ሳይሰጣቸው በየዐደባባዩና በአልባሌ ቦታዎች ልመናን የሚያስፋፉ ሕገ ወጥ ግለሰቦች ላይ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ተጠቆመ፡፡
የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ እንዳስታወቁት በየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ ለሚደርሰው ተፈጥሮአዊና ሰው ሠራሽ አደጋ እንዲሁም አዲስ ለሚታነፁ አብያተ ክርስቲያናት ለማሠሪያ የሚሆን ገንዘብ ምእመናንንና በጐ አድራጊዎችን ለመጠየቅ የሚያስችል ፳፬ አንቀጾች ያሉት ደንብና መመሪያ ተዘጋጅቷል፡፡ ደንቡና መመሪያው ለሁለት ዓመት የሚያገለግል ሲሆን ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጥያቄ ሲቀርብ ፈቃድ ይሰጣል፡፡