መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ልሳነ አርድእት
ሰኔ 19 ቀን 2006 ዓ.ም.
በመ/ር ደሴ ቀለብ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፊሎሎጂ መምህር
ክፍል ፩
የግእዝ ቋንቋ እድገት ከየት ወዴት?
አንዲት ሀገር የራሷ የሆነው ባህሏ /ሥርዓቷ/ የሚያኮራትና ማንነቷንም የሚያንጸባርቅ በመሆኑ ልትጠብቀውና ከትወልድ ወደ ትውልድ ልታስተላልፈው የባለቤትነት ግዴታዋ ነው፡፡ በመሆኑም ሀገራችን ኢትዮጵያን ለጥቁር ሕዝቦች መኩሪያ እንድትሆን ያደረጋት የልጆቿ ሀገር ወዳድነትና ጀግንነትን የተመላው ባህሏ ብቻ ሳይሆን የሃይማኖት፤ የሥነ ፊደል ሀገር መሆኗም መጻሕፍተ ታሪክን ባነበቡ ሊቃውንት አንደበት ብቻ ሳይሆን በማዳመጥ ትውፊት /ርክክብ/ ለኅብረተሰቡ ኀቡእ ያልሆነ ነገር መሆኑ ነው ፡፡
በተጨማሪም ሀገራችን ኢትዮጵያ የዘመናት ዑደት ስፍር ቀምራ የራሷን አኀዝ ያደላደለች አፍሪካዊት እመቤት ናት ብንል ጽልመት ሊጋርደው የማይችለው ገሀድ ነው፡፡
የደብረ ሊባኖስ ገዳም አምስቱ ስያሜዎች
ሰኔ 17 ቀን 2006 ዓ.ም.
የደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም ገዳማዊ ሥርዓቱ እንደተጠበቀ ቢሆንም የጎርፍ አደጋ፤ የብዝኅ ሕይወት መመናመን፤ የሕገ ወጥ የመሬት ወረራና ሌሎችም ችግሮች እየተፈታተኑት ይገኛል፡፡ ይህንን ችግር ለመቅረፍና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት በገዳሙና በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ፕሮጀክቶች ተቀርጸው ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡
ፕሮጀክቶቹንም በተያዘላቸው እቅድ መሠረት ለማስፈጸም በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ሠኔ 8 ቀን 2006 ዓ.ም. የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ላይ ፕሮጀክቶቹንና ገዳሙን አስመልክቶ የተዘጋጀ መጽሔት ለምእመናን ተሰራጭቷል፡፡ ከመጽሔቱ ያገኘናቸውን ጥቂት መረጃዎች እናካፍላችሁ፡-
የማቴዎስ ወንጌል
ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም.
ምዕራፍ ሁለት
በዚህ ምዕራፍ ውስጥ የምንረዳውና የምንገነዘበው ጌታ በይሁዳ ቤተልሔም በንጉሥ ሄሮድስ ዘመን እንደተወለደ እንረዳለን፡፡ ቤተልሔም ማለት ቤተ ኅብስት ማለት ነው፡፡ ስምዋም የተሰየመው ካሌብ ኤፍራታ የተባለች ሚስት አግብቶ ወንድ ልጅ ከኳ በወለደ ጊዜ እንጀራ እገባ እገባ ብሎት ስለነበር የልጁን ስም ልሔም /ኅብስት/ አለው፡፡ በልሔም ቤተልሔም ተብላለች፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን በኦሮምኛ ቋንቋ የድረ – ገጽ አገልግሎት ሊጀምር ነው
ሰኔ 13 ቀን 2006 ዓ.ም
በእንዳለ ደምስስ
በማኅበረ ቅዱሳን የኅትመትና ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ዋና ክፍል የኦሮምኛ ድረ ገጽ አገልግሎት በቅርቡ እንደሚጀምር የዋና ክፍሉ ሓላፊ ዲያቆን ዶ/ር መርሻ አለኸኝ ገለጹ፡፡
ቅድስት አፎሚያ
ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በመ/ር ፍቃዱ ሣህሌ
በወርኃ ሠኔ መታሰቢያ ከሚደረግላቸው ቅዱሳን መካከል እግዚአብሔርን የሚፈራ የአስተራኒቆስ ሚስት የሆነች የቅድስት አፎምያን ታሪክ በአጭሩ እንዳስሳለን፡፡
ቅድስት አፎምያ በትዳር በነበረችባቸው ዘመናት እግዚአብሔርን ከሚወድ ባለቤቷ ጋር እግዚአብሔርን ስታገለግለው የኖረች ሴት ነበረች፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ እንደነበር ታሪካቸው ይነግረናል፡፡
ለማእከላት ሓላፊዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት
ማኅበረ ቅዱሳን ለማእከላት፤ ለማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎችና አስተባባሪዎች ከሰኔ 10- 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ሁለት ቀናት የቆየ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጠ፡፡
በሥልጠናው ከሀገር ውስጥና ከውጪ የተውጣጡ የ25 ማእከላት ጸሐፊዎች፤ የማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎች፤ የግቢ ጉባኤያት አስተባባሪዎችና መምህራን መካፈላቸውን የማኅበረ ቅዱሳን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና ጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ሓላፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡
ለማእከላት ሓላፊዎች የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም.
በሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት
ማኅበረ ቅዱሳን ለማእከላት፤ ለማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎችና አስተባባሪዎች ከሰኔ 10- 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ሁለት ቀናት የቆየ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ሰጠ፡፡
በሥልጠናው ከሀገር ውስጥና ከውጪ የተውጣጡ የ25 ማእከላት ጸሐፊዎች፤ የማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሓላፊዎች፤ የግቢ ጉባኤያት አስተባባሪዎችና መምህራን መካፈላቸውን የማኅበረ ቅዱሳን የሰው ሀብት ሥራ አመራርና ጠቅላላ አገልግሎት ክፍል ሓላፊ አቶ ዳንኤል ተስፋዬ ገልጸዋል፡፡
ጉባኤ ቃና
የደብረ ሊባኖስ ገዳምን ለመታደግ ጥሪ ቀረበ
ሰኔ 10 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የደብረ ሊባኖስ ገዳም የልማት ፕሮጀክት ትግበራ በመፋጠን ላይ ይገኛል
ሰኔ 5 ቀን 2006 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የጥናት ቡድኑ በገዳሙ የሚታዩትን ዋና ዋና ችግሮች በመለየትና ጥናት በማካሔድ፤ የፕሮጀክት ሰነድ በማዘጋጀት ወደ ተግባር ለመሸጋገር በርካታ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል፡፡