መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
የ፳፻፯(2007)ዓ/ም ዐብይ ጾምና በዓላቱ
ጥር 29 ቀን 2007 ዓ.ም.
የ2007 ዓ.ም. ዘመን አቆጣጠር በዓላትና አጽዋማትን በአዲሱ ዓመት መባቻ ማቅረባችን ይታወሳል፡፡ አሁን ያለንበት ወቅት የነነዌ ጾም አልፈን ዐብይ ጾምን የምንቀበልበት ወቅት በመሆኑ መረጃውን ለማስታወስ ይህንን ዝግጅት ያቀረብን ሲሆን የምትፈልጉትን ቀን ለማወቅ ከማኅበሩ ድረ ገጽ ላይ ያለውን የዘመን መቁጠሪያ በመቀያየር መጠቀም ትችላላችሁ፡፡
የነነዌ ሰዎች የንስሐ ምስክሮች
ጥር 24 ቀን 2007 ዓ.ም.
በዲ/ን በረከት አዝመራው
የነነዌ ጾም ከሰባቱ የቤተ ክርስቲያን አጽዋማት አንዱና የዐቢይ ጾም ማዘጋጃ ደወል ነው፡፡ ይህ የነነዌ ሰዎች የንስሐ ታሪክ በቤተ ክርስቲያናችን በጣም ታላቅ ዋጋ ያለውና የራሱ መዝሙር የሚዘመርለት፣ ቅዳሴ የሚቀደስበት ታላቅ መታሰቢያ ያለው ታሪክ ነው፡፡
የጀበራ ቅድስት ማርያም ገዳምን ዳግም በማቅናት ላይ የነበሩት አባ ዘወንጌል ዐረፉ
ጥር 22 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የማቴዎስ ወንጌል
ምዕራፍ 13
ጥር 14 ቀን 2007 ዓ.ም.
1. ስለ ዘሪው ምሳሌ
2. ስለ ሰናፍጭ ቅንጣት ምሳሌ
3. ስለ እርሾ ምሳሌ
4. ስለ እንክርዳድ ምሳሌ
5. ስለ ተሰወረው መዝገብ ምሳሌ
6. ስለ ዕንቁ ምሳሌ
7. ስለ መረብ ምሳሌ እና
8. ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ አደገባት መንደር ወደ ናዝሬት ስለመሄዱ፡፡
የከተራ በዓል በጃን ሜዳ
ጥር 10 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
የከተራ በዓል ቅድመ ዝግጅት
ጥር 11 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
ወተጠሚቆ ሶቤሃ ወጽአ እማይ ጌታችን … ከተጠመቀ በኋላ ከውሃው ወጣ
ጥር 10 ቀን 2007 ዓ.ም.
ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
የአራቱ ጉባኤያት መምህርና የጎንደር መ/መ/መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ
የታክሲ ሾፌሮች፤ ረዳቶችና ተራ አስከባሪዎች ጉባኤ 8ኛ ዓመት ተከበረ
ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም.
በደመላሽ ኃይለ ማርያም
የብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት ለታክሲ ሹፌሮች፣ ተራ አስከባሪዎችና ረዳቶቻቸው አገልግሎት እንዲሰጥ የመሠረተውን ጉባኤ 8ኛ ዓመት አስመልክቶ ታኅሣሥ 25 እና 26 ቀን 2007 ዓ.ም. “ለፍቅርና ለመልካም ሥራ እንድንነቃቃ እርስ በርሳችን እንተያይ” በሚል የመጽሐፍ ቅዱስ መሪ ቃል በቤተ ክርስቲያኑ ቅጥር ግቢ አባላቱና በርካታ ምዕመናን በተገኙበት ተከበረ፡፡
ቅዱስ ፓትርያርኩ የልደት በዓልን አስመልከቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ
ታኅሣሥ 27 ቀን 2007 ዓ.ም.
1ዐ.4 ቦ / አለ/ በመራሕያን ሲረባ/ Verb to have/
ግእዝን ይማሩ
ታኅሣሥ 24 ቀን 2007 ዓ.
1ዐ.4 ቦ / አለ/ በመራሕያን ሲረባ/ Verb to have/
ብየ= አለኝ ምሳሌ ምንት ብየ ምስሌኪ ካንቺ ጋር ምን አለኝ
ብከ= አለህ ምንት ብከ ምስሌሃ ከርሷ ጋር ምን አለህ
ብኪ = አለሽ ምንት ብኪ ምስሌሃ ከርሷ ጋር ምን አለሽ
ብነ = አለን ምንት ብነ ምስሌክሙ ከእናንተ ጋር ምን አለን