01admaa

አዳማ ማእከል የሐዊረ ሕይወት አካሔደ

መጋቢት 23 ቀን 2008 ዓ.ም

ከአዳማ ማእከል

01admaaበማኅበረ ቅዱሳን የአዳማ ማእከል ለ4ኛ ጊዜ ያዘጋጀውን የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር በመቂ ግራዋ ጃዌ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን መጋቢት 11 ቀን 2008 ዓ.ም አካሔደ፡፡

መርሐ ግብሩ በደብሩ ሊቀውንተ ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ወንጌል የተጀመረ ሲሆን በማእከሉ መዝምራንና በቀሲስ ምንዳየ ብርሃኑ መዝሙር ቀርቦ በዲ/ን ዳንኤል ክብረት ዓላማ(ተልዕኮ) ያለው ክርስቲያን€ በሚል ርዕስ የወንጌል ትምህርት ተሰጥቷል፡፡

በምክረ አበው መርሐ ግብር ከምእመናን የተሰበሰቡ ጥያቄዎችን መሠረት አድርጎ በተሐድሶ እንቅስቃሴ ላይ የምእመናንና የሊቃውንት ድርሻ፤ ገድላትና ድርሳናት ከመጽሐፍ ቅዱስ አንጻር ያላቸው አገልግሎት፤ ሉላዊነትን እንዴት መቋቋም ይቻላል፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለሀገራችን ያደረገችው አስተዋጽኦ፣ . . . አስመለክቶ በዲ/ን ዳንኤል ክብረት እና ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ መልስ ተሰጥቶባቸው የጠዋት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል፡፡

ከሰዓት በኋላ በተከናወነው ቀጣይ መርሐ ግብር በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ ጌታ ሆይ አድነኝ ብሎ ጮኸ€ በሚል ርዕስ የወንጌል ትምህርት፣ በመቂ ግራዋ ጃዌ አቡነ ገብረ መንፈስ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ በተከታታይ ቀርበዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ በግንባታ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ከምእመናን የ27 ሺሕ(27000) ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡