መንፈሳዊነት
ኦርቶዶክሳዊነት ርትዕት ሃይማኖት፣ ጽኑ እምነት፣ መልካም ምግባርና መንፈሳዊ እውቀት በአንድነት የተዋሐዱበት፤ አርአያ እግዚአብሔርን አጽንቶ በሐዋርያዊ የሕይወት ተጋድሎ እግዚአብሔርን በግብር ወደ መምሰል የሚታደግበት ፍጹም ሰማያዊ ሕይወት በመሆኑ፤ አባላት በየትኛውም ቦታ፣ ጊዜና ሁኔታ በማሰብ፣ በመናገር እና በመሥራት/በተግባር በሚገለጽ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ታንጸው፣ ፍኖተ አበውን ተከትለው፣ በታማኝነት እና በፈሪሐ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ያገለግላሉ::
ቤተ ክርስቲያናችን ፳፰ ቤቶቿን አስመለሰች
አስመላሽ ኰሚቴው ባደረገው ያለሰለሰ ጥረት በሦስት ክፍለ ከተሞች ማለትም በልደታ ፲፰፤ በየካ ፭ እና በቂርቆስ ፭ በድምሩ ፳፰ ቤቶች ነሐሴ ፲፱ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም ለባለንብረቷ ለቤተ ክርስቲያን መመለሳቸው ተረጋግጧል፡፡
ዘመነ ክረምት ክፍል ሦስት
‹‹ለነፍሳችሁ በምትበሉት ወይም ለሰውነታችሁ በምትለብሱት አትጨነቁ፡፡ ነፍስ ከመብል ሰውነትም ከልብስ ይበልጣልና፡፡ ቍራዎችን ተመልከቱ፤ አይዘሩም፤ አያጭዱምም፡፡ ዕቃ ቤትም ወይም ጎተራ የላቸውም፤ እግዚአብሔርም ይመግባቸዋል፡፡ እናንተ ከወፎች ትበልጡ የለምን? … የእናንተም አባት ይህ እንዲያስፈልጋችሁ ያውቃል:: ዳሩ ግን መንግሥቱን ፈልጉ፤ ይህም ኹሉ ይጨመርላችኋል፡፡››
ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ማወቅ የችግሮች መፍትሔ መኾኑን ብፁዕ ሥራ አስኪያጁ ገለጡ
‹‹ኹሉም ሕዝበ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ መብትና ግዴታውን ዐውቆ እናት ቤተ ክርስቲያንን በፍቅር በማገልገል መንፈሳዊ አደራውን ሊወጣ ይገባል››
በዓለ ፍልሰታና ሻደይ
ከነሐሴ ፲፮ እስከ ነሐሴ ፳፩ ቀን ድረስ የሚከበረው ይህ በዓል በዋግ ኽምራ ‹‹ሻደይ››፣ በላስታ ‹‹አሸንድዬ››፣ በትግራይ ‹‹አሸንዳ››፣ በቆቦ አካባቢ ‹‹ሶለል››፣ በአክሱም አካባቢ ደግሞ ‹‹ዓይነ ዋሪ›› እየተባለ ይጠራል።
‹‹አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፤ አንተና የመቅደስህ ታቦትም›› /መዝ.፻፴፩፥፰/
ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት በትንቢቱ «ተንሥእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅድስከ፤ አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፤ አንተና የመቅደስህ ታቦትም» /መዝ.፻፴፩፥፰/ በማለት አስቀድሞ የክርስቶስን ትንሣኤ ከገለጸ በኋላ ቀጥሎ የመቅደሱ ታቦት እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ከሞት እንደምትነሣ ተናግሯል /ማቴ.፭፥፴፭፤ ገላ.፬፥፳፮፤ ዕብ. ፲፪፥፳፪፤ ራእ.፫፥፲፪/፡፡
አስደናቂው የድንግል ማርያም ሞትና ትንሣኤ
መንፈስ ቅዱስ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና መውለዷን በትንቢት እንዳናገረ ትንሣኤዋንም በትንቢት ሲያናግር ኖሯልና ይህ ታላቅ ምሥጢር በቅዱስ ዳዊት አንደበት ‹‹ተንሥእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ አንተ ወታቦተ መቅደስከ፤ አቤቱ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፤ አንተና የመቅደስህ ታቦትም›› ተብሎ ተገልጿል /መዝ.፻፴፩፥፰/፡፡
ደብረ ታቦርና ቡሄ
ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት እረኞች ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጥተዋል፡፡ «ቡሄ» ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና ችቦ የሚበራው ከዚህ በመነሣት ነው፡፡
አስተርእዮተ እግዚአብሔር በደብረ ታቦር
እግዚአብሔር አምላክ በሐዲስ ኪዳን በአካለ ሥጋ ያደረገውን መገለጥ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ከምሥጢረ ሥላሴ ጋር በማያያዝ በሦስት መንገድ ይገልጹታል፡፡ ይኸውም በእመቤታችን፣ በዮርዳኖስና በደብረ ታቦር ላይ ነው ይላሉ፡፡ ‹‹በላዕሌኪ ወበዮርዳኖስ ወበታቦር ሥልሰ ጊዜያተ ዘአልቦ ተውሳከ ወአልቦ ሕጸተ ለውሉደ ሰብእ ያርኢ ዘሥላሴሁ ገጻተ ጽጌኪ ድንግል ተአምሪሁ ከሠተ ወበፀዳሉ አብርሀ ጽልመተ›› እንዳለ ደራሲ /ማኅሌተ ጽጌ/፡፡
የአብነት ትምህርት ቤቶች ችግር አሳሳቢ መኾኑ ተገለጠ
ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ እና ብፁዕ አቡነ ሙሴ የአብነት ትምህርት ቤቶችን መከባከብ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ማስቀጠል መኾኑን በማስረዳት በመላው ዓለም የሚኖሩ ምእመናን በአንድነት ኾነው ለአብነት ት/ቤቶች መጠናከር የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡
ትምህርት ቤቱ በ፳፻፱ ዓ.ም ሥራ እንደሚጀምር ተገለጠ
‹‹መረዳዳቱ፣ አንድነቱና መፈቃቀሩ ካለ ከዚህ የበለጠ ገቢ ሊያስገኙ የሚችሉ ሌሎችንም የልማት ሥራዎችን መሥራት ይቻላል!››