በዓለ ደብረ ታቦር

በታቦር ተራራ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ዕለት ነሐሴ ፲፫ ”በዓለ ደብረ ታቦር‘ የከበረ በዓል ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም በድምቀት ታከብረዋለች፡፡ ደብረ ታቦርም የቤተ ክርስቲያን አምሳል ነች፤ ከብሉይና ከሐዲስ በውስጧ ሰብስባለችና።

‹‹ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታ ናቸው›› (መዝ.፻፳፯፥፫)

ከፍጥረታት ሁሉ የሰው ልጅ በቅድስት ሥላሴ አርአያና አምሳል የተፈጠረ ክቡር ፍጥረት ነው፤ የፍጥረት ሁሉ መፈጠር ትርጉም ያገኘው የሰው ልጅ ሲፈጠር ነው፤ እግዚአብሔር ፍጥረታትን በአርምሞ የፈጠራቸው፣ በመናገር የፈጠራቸው እና ካለሞኖር ወደ መኖር በማምጣት ፈጠራቸው፤ አዳምን (የሰው ልጅን) ሲፈጥር ግን በሦስቱም ግብር ነው፤ በማሰብ ‹‹…ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር›› ብሎ በመናገር፣ ከዚያም ከምድር አፈር (ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ ከውኃ፣ ከመሬት፣ ከነፋስ እና ከእሳት) በማበጀት በኋላም የሕይወትን እስትንፋስ እፍ በማለት ፈጥሮታል፤ (ዘፍ.፩፥፳፮)ሰው ክቡር ፍጥረት ነው መባሉ ለዚህ ነው፡፡

ፅንሰታ ለማርያም

የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እናት ቅድስት ሐና የተወለደችው በቤተ ልሔም ይሁዳ ውስጥ ነው፡፡ ኢያቄም የሚባል ሰው አግብታ ትኖር ነበር፡፡ ሁለቱም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ ነበሩ፡፡ ሆኖም ግን ሐና መካን ስለነበረች ልጅ መውለድ አልቻሉም፡፡ በዚህም ለበርካታ ዓመት ሲያዝኑና አምላካቸውን ሲማጸኑ ኖሩ፡፡ በዚህም መካከል ስዕለትን ተሳሉ፤ ፈጣሪ ልጅ ቢሰጣቸው ለቤተ ክርስቲያን አገልጋይ እንደሚሰጡም ቃል ገቡ፡፡

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል

መልአኩ ዑራኤል “አፍህን ክፈት፤ እኔም የማጠጣህን ጠጣ” … ብሎ አእምሮ ለብዎውን ገልጦለታል። (ዕዝ.ሱት. ፲፫፥፴፰) የዚህን ተአምር መታሰቢያ ሐምሌ ፳፪ በየዓመቱ ቤተ ክርስቲያናችን ታከብራለች።

“ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አባቴ ነህ!”

መኮንኑ አፈረና ጽኑ ሥቃይ ሊያሠቃያቸው ወድዶ እንደ ክረምት ነጎድጓድ ድምፅ ወደ ሚያስተጋባው የፈላ ውኃ እንዲጥሏቸው አዘዘ፤ ያን ጊዜ እናቱ ፈራች፤  ሕፃኑ ግን ለእናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ እንዲህም አላት፤ “እናቴ ሆይ አትፍሪ! ጨክኝ፤ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳነ አምላክ እኛንም ያድነናል” አላት። እናቱ ቀና ብላ ብትመለከት ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁትን የብርሃን ማደርያቸውን ተመለከተች፤ ደስም ተሰኝታ እንዲህ አለች፤ “ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አባቴ ነህ፤ እኔም ልጅህ ነኝ፤ አንተን የወለድኩባት ቀን የተባረከች ናት፡፡”

‹‹አቤቱ በፊትህስ ባለሟልነትን አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈው›› (ዘፍ.፲፰፥፫)

ሥላሴ ሊቃውንት ‘የወይራ ዛፍ’ ብለው በተረጎሙት በመምሬ ዛፍ ሥር ተገለጠ፤ አብርሃምም ጎልማሳ እንግዶች መስለውት ወደ ቤቱ ወስዶ ያስተናገዳቸው ዘንድ ወደ እነርሱ ሮጠ፤ ‹‹ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ሮጠ›› እንዲል (ዘፍ.፲፰፥፪)። ቀርቦም ከምድር ወድቆ እጅ ነሣ፤ እንዲህም አላቸው። ‹‹አቤቱ በፊትህስ ባለሟልነትን አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈው፤ ውኃ እናምጣላችሁ፤ እግራችሁን እንጠባችሁ።›› (ዘፍ.፲፰፥፫)

‹‹እስከ ሞት ድረስ የታመንክ ሁን›› (ራእ.፪፥፲)

የክርስትናን ሕይወትና ጉዞ መጀመር ቀላል ሲሆን ዳገት የሚሆነው መፈጸሙ ነው፡፡ ‹‹እስከ ሞት›› የመባሉም ዋናው ምክንያት ይህ ነው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ዕለተ ምጽአቱ ባስተማረበት የወንጌል ክፍልም ከዚህ ኃይለ ቃል ጋር በእጅጉ አንድ በሆነ መንገድ ‹‹እስከ መጨረሻ የሚጸና እርሱ ይድናል››  በማለት ያስተማረው ትምህርት መፈጸም እንደመጀመር ቀላል እንዳልሆነ የሚያስረዳን ነው፡፡ (ማቴ.፳፬፥፲፫)

‹‹አናቅጸ ሲኦል ኢይኄይልዋ፤ የገሃነም ደጆች አይችሏትም›› (ማቴ.፲፮፥፲፱)

በፊልጶስ ቂሳርያ ‹‹ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል›› ብሎ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጠየቀ ሰዓት የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስ የተናገረው ቃል ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ሆነ ነው፡፡ (ማቴ.፲፮፥፲፫) ቅዱስ ጴጥሮስ ‹‹የሕያው እግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ነህ›› በማለት በሰጠው ምስክርነት ጌታችን ‹‹የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ …..አንተ ዓለት ነህ፥ በዚያችም ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሠራለሁ፥ የገሃነም ደጆችም አይችሏትም›› በማለት ለሐዋርያቱ ቃል ኪዳን ገባላቸው። (ማቴ.፲፮፥፲፰) ቤተ ክርስቲያን የሚለው የተለያየ ዐውዳዊ ፍች ቢኖረውም የሰውን ድካም የሚያውቅ እግዚአብሔር በዚህች ቀን በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ስም በፊልጵስዩስ ከሦስት ደንጊያዎች ቤተ ክርስቲያንን ሠራልን። ዓለት ያለውን ቅዱስ ጴጥሮስንም ‹‹አርሳይሮስ›› ብሎ ሾመው፤ ትርጓሜውም ሊቀ ጳጳሳት ማለት ነው። (መጽሐፈ ስንክሳር፣ ሰኔ ወር፣ ፳ እና ፳፩ ቀን)

‹‹የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፤ ያድናቸውማል›› (መዝ.፴፫፥፯)

ልበ አምልክ ቅዱስ ዳዊት የተናገረው ይህ ኃይለ ቃል እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሰዎች ጠባቂ መልአካቸው በዙሪያቸው ሰፍሮ የሚጠብቃቸው መሆኑን የሚገልጽ ነው፡፡ ሰዎች የሚጠበቁት በሦስት በኩል ነው፤ …. በየዓመቱ በዓለ ቅዱስ ሚካኤል የሚታሰበው በዓል የመላእከትን ጥበቃ መሠረት ያደረገ ነው፡፡

በዓለ ጰራቅሊጦስ

ጰራቅሊጦስ ማለት ናዛዚ፣ ከሣቲ፣ መንጽሒ፣ መጽንዒ፣ መስተስርዪ፤ መስተፍሥሒ ማለት ነው። መንጽሒ ማለት ከኃጢአት የሚያነጻ፣ የሚቀድስ፣ የቅድስና ነቅዕ፣ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ በሰውነታችን የሚያሳድር ነው። መጽንዒ ማለት የሚያጸና፣ ኃይል፣ ብርታት፣ ጥብዓት የሚሆን፣ ቅዱሳንን ከሀገር ምድረ በዳ ከዘመዳ ባዳ አሰኝቶ ዳዋ ጥሰው፣ ጤዛ ልሰው፣ ደንጋይ ተንተርሰው፣ ግርማ ሌሊቱን፣ ጸብአ አጋንንቱን ታግሠው፣ ጸንተው እንዲኖሩ የሚያደርግ ማለት ነው። መሥተፍሥሒ ማለት ሙሐዘ ፍሥሓ የደስታ መፍሰሻ፣ ሰዎችን ደስ የሚያሰኝ፣ በመከራ በኀዘን ውስጥ ደስታን የሚሰጥ ነው። “ሐዋርያትንም ወደ እነርሱ ጠርተው ገረፉአቸው፥ በኢየሱስም ስም እንዳይናገሩ አዝዘው ፈቱአቸው። እነርሱም ስለ ስሙ ይናቁ ዘንድ የተገባቸው ሆነው ስለ ተቈጠሩ ከሸንጎው ፊት ደስ እያላቸው ወጡ” እንዲል፤ (የሐዋ.፭፥፵)