ኒቆዲሞስና አዲሱ ልደት

መጋቢት 20 ቀን 2007 ዓ.ም.

በዲ/ን ታደለ ፈንታው

በቅዱስ ዮሐንስ ወንጌል በምዕራፍ ሦስት ብዙ አሕዛብ ወደ ክርስትና እምነት የተቀላቀሉበት ምዕራፍ ነው፡፡ድኅነትን በትጋት ለመፈጸም የሚታገሉ ክርስቲያኖች ይሄንን ምዕራፍ ሲያነቡ ከኒቆዲሞስ ጎን መቆማቸው የሚያጠራጥር አይሆንም፤ ከጌታ ጋር ምስጢራዊ የሆነ ውይይትን መቀጠል ይፈልጋሉ፡፡ በሕይወታቸው የተከፈተ የአዲስ ኪዳን መንገድን እንዳለ ሲገነዘቡም ጌታን ይከተላሉ፡፡ ከእርሱ ጋር ከቅዱስ መንፈሱም ጋር አንድ ይሆናሉ፡፡ አዲስ ልደትን ያገኛሉ ፤ይህም በጥምቀት የሚገኝ ልጅነት ነው፡፡

ይህ ምዕራፍ መልካም ሥነ ምግባር በነበረው ፈሪሳዊ ሕያውና መንፈሳዊ በሆነው ምንጭ በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መካከል የነበረውን ውይይት ይዟል፡፡

ኒቆዲሞስ እንደ ፈሪሳዊ በአይሁድ ትውፊትና በብሉይ ኪዳን ትምህርት የታጠቀ ነው፡፡ ጠንካራ ሞራል እንደገነባ ሰው ወደ ጽድቅ የሚወስደውን ትውፊት የሚያውቅ ሰው በፈቃዱ መታዘዝ እንዳለበት የሚያምን ነው፡፡ ይህ የሚሆነው ደግሞ ሰው በሚያደርገው ጠንካራ ትግል እንደሆነ ያምናል፡፡ይህ ትግል በሰው በጎ ፈቃድና ሕጉን በደረቁ በመተርጎም እንደሚገኝ ያምናል፡፡ ኒቆዲሞስ ጌታን ያገኘው ሕጉን የሚቃወም ሆኖ ሳይሆን ሕጉን በጥልቀት የሚተረጉም አይሁዳዊ ሆኖ ነው፡፡

ስለዚህም ነው ወደ መድኀኒታችን ከተሳቡ ወገኖች መካከል ወንጌላዊው የኒቆዲሞስን ጉዳይ በትኩረት የጻፈው፡፡ በዚህ ዐውድ ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ ይላል፡-በፋሲካ በዓልም በኢየሩሳሌም ሳለ ያደረገውን ምልክት ባዩ ጊዜ /ዮሐ.2፡23/፡፡ ኒቆዲሞስ ጌታ ከእግዚአብሔር እንደመጣ አወቀ፤ አመነም /ዮሐ.3፡2/፡፡ ነገር ግን ምናልባት ኒቆዲሞስ ጌታ ትምህርቱን ማኅበራዊ ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚያስተምር ሊያስብ ይችላል፡፡ የሕጉን ጥሬ ትርጉም እንጂ ፍካሬያዊ ትርጉም አልተገነዘበም፡፡ የአይሁድን ኑሮ ሊያሻሽል የመጣ ነው ብሎም ሊያስብ ይችላል፡፡

የኒቆዲሞስ አመለካከቱና ልምዱ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውን አዲስ ሕይወት ለመቀበል አያበቃውም፡፡ በአዲሱ ልደት የሚገኘው የጸጋ ልጅነት አይገነዘበውም፡፡ የመንፈሳዊው ሕግ ጥቅም ግን ይህ ነበር፡፡ ሥጋዊውን ከመንፈሳዊ ምድራዊውን ከሰማያዊ መለየት ያስችላል፡፡ ጌታ የኒቆዲሞስን አሳቡን፣ ልቡን፣ ስሜቱን፣ ዕውቀቱን ሁሉ ወደ ሰማያዊ ነገር እንዲያሸጋግረው ፈቀደ፡፡ ይህን በማድረግ ከሰማይ የወረደው እርሱም የሰው ልጅ በሰማይ የነበረው€ እንደሆነ ይገነዘባል፡፡ ወደ ሰማይ መውጣትም የሚቻለው እርሱ ነው፡፡ በእርሱ የሚያምኑ ወገኖችን ከፍ ከፍ የሚያደርጋቸው ከፍ ያለውንም ነገር እንዲመለከቱ የሚያደርጋቸው እርሱ ነው፡፡

የኒቆዲሞስና የጌታ ግንኙነት ትኩረታችንን ወደ ክርስቶስ እንድናደርግ ያደርገናል፡፡ ለእያንዳንዱ የሰው ልጅ ነፍስ መዳን ምን ያህል ትኩረት እንደሚሰጥ ከእያንዳንዱም ወገን ጋር ሲነጋገር ያለውን ትህትናም እንገነዘባለን፡፡ ከኒቆዲሞስ ጋር ሲወያይ የአዲሱን ልደት ጠባይ ዘርዝሯል፡፡ ኒቆዲሞስ የእግዚአብሔርን መንግሥት ማወቅ ፈልጓል፤ ይሄንን መንግሥት ለማወቅ በውኃና በመንፈስ ይጠመቅ ዘንድ ግድ መሆኑን ያስረዳል፡፡

ይህ ሁኔታ አስፈላጊ ነው፤ ክርስቲያን ዘወትር የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ እንዲኖር ያስችለዋልና ይጠመቅ ዘንድ የግድ ነው፤ በመንፈሱም እንዲኖር ያደርገዋል፡፡ በዚህ ምዕራፍ ጌታ ከምድራዊ ነገሮች ያወጣና አሳባችን ሰማያዊ በሆነው ጉዳይ እንዲያዝ ያደርጋል፡፡ ይህንን ማድረግ የምንችለው ከሰማያዊው ጋር ሕብረት ስንፈጥር መሆኑን ይነግረናል፡፡

ጌታ ጥምቀቱን ከመስቀሉ ጋር አያይዞታል ፡፡ እግዚአብሔር አብ ለሰው ልጆች ሁሉ ያለውን እውነተኛ ፍቅር የገለጠበት፣ የባሕርይ ልጁን ወደ ዓለም በመላክ ዓለሙ ዘላለማዊ ሕይወትን ያገኝ ዘንድ ልጁ ከፍ ከፍ ያለበትም የነገሠበትም ዙፋኑ ነውና፡፡ አዲሱን ልደትን በማንሣት ጌታ ከፍርሃት ባርነት አውጥቶ መለኮታዊ የሆነውን ብርሃን እንድንመለከት ያደርገናል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ጌታ ሲጠመቅ የነበረውን ሁኔታ ሲነግረን ለሚያምኑ ወገኖች ያለውን አንድምታም ሲገልጽ ደስታው ፍጹም ነበር፡፡ በዚህ ምዕራፍ ውስጥ

1.ስለ አዲሱ ልደት ገለጻ /1፡13/

2.አዲሱ ልደትና የመስቀሉ ሥጦታ /14-17/

3.አብርሆትና እምነት /18-21/

4.በጌታ ጥምቀት ጊዜ የዮሐንስ ሁኔታ /22-36/ ተዘርዝሯል፡፡

ስለ አዲሱ ልደት ገለጻ

ከፈሪሳውያንም ወገን የአይሁድ አለቃ የሆነ ኒቆዲሞስ የሚባል አንደ ሰው ነበረ /ቁ.1/€ ኒቆዲሞስ የአይሁድ ስም ሲሆን ትርጓሜው ሕዝብን ያሸነፈ€ ማለት ነው፡፡ የአይሁድ አካል የሰንሃድሪን አይሁድ ሸንጎም አባል ነው፡፡ መለኮታዊው ጥሪው መላውን የሰው ልጆች ያካተተ ነው፡፡ የመደብ ልዩነት አልተደረገበትም፡፡ ነገር ግን በከፍተኛ ሓላፊነት ከነበሩ የመንግሥትና የሃይማኖት መሪዎች መካከል ለዚህ ጥሪ መልስ የሰጡ ጥቂቶች ነበሩ፡፡ ከፈሪሳውያን መካከል እጅግ ጥቂቶች፤ ከጥቂቶቹ አንዱ ኒቆዲሞስ ነበር፡፡

ጌታን ሊያነጋግር የመጣው ብቻውን ነው፡፡ ምናልባት አንድ ወይም ሁለት አጃቢዎች ሳይኖሩት አይቀሩም፡፡ በአይሁድ ሸንጎ የተከበረ ሰው ነበረ፡፡ ጌታ ግን ይህችን አንዲት ለመዳን የወሰነች ነፍስ ዝቅ አላደረጋትም፤ ሞትን የተቀበለው ስለ እያንዳንዱ ነፍስ ነውና፡፡ ፈሪሳውያን ለመለኮታዊው እውነት የሰጡት መልስ ጥላቻና የዓመጽ መንፈስን የተመላ ነው፡፡ ነገር ግን ከተማሩ አይሁድ መካከል ጌታን ለማግኘት የቸኮሉ በሩም ተከፍቶ የጠበቃቸው ጥቂቶች ነበሩ፡፡ የእግዚአብሔር ጸጋ በተማሩም ባልተማሩም ወገኖች ላይ ይሠራል፡፡ በተራውም ሕዝብ፣ በአለቃውም፣ በየዋኁም፣ በዓመጸኛውም ላይ ይሠራል፡፡

ኒቆዲሞስ ደረጃው ከአመጸኞቹ ቢሆንም ወደ ጌታ መጣ፤ ጊዜው ሲደርስ የቻለውን ያህል ይጠይቅና ያውቅ ዘንድ ሞከረ፡፡ በጥያቄ ላይ እንደነበረ ታሪኩ ያስረዳል፡፡ ጊዜው ሲደርስ ለደቀ መዛሙርቱ ያልተቻለው ለዚህ ሰው ተቻለ፡፡ ከጲላጦስ አስፈቀዶ አዲስ ባሳነጸው መቃብር ላይ እንዲቀበር አደረገ፡፡

ቤን ረጊን በአይሁድ ታሪክ መጽሐፍ ስለ ኒቆዲሞስ ሲናገር ይህ ሰው በጣም ሀብታም ከመሆኑ የተነሣ በኢየሩሳሌም የነበሩ ብዙዎችን ለብዙ ዓመታት ይረዳ ነበር ይላል፡፡

እርሱም በሌሊት ወደ ኢየሱስ መጥቶ መምህር ሆይ እግዚአብሔር ከርሱ ጋር ከሆነ በቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና መምህር ሆነህ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደ መጣህ እናውቃለን /ቁ.2/አለው፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ኒቆዲሞስን በብዙ ቦታዎች ጠርቶታል፡፡ ጌታን ማታ ማታ ይጎበኝ እንደነበረ ተገልጧል፤ ይህ ሁኔታ ሦስት ጊዜ ያህል ተጠቅሷል /ዮሐ.ዮሐ.3፡2፣ 7፡50፣ 19፡39/

ስለምን ወደ ጌታ በምሽት መጣ

1.የመጀመሪያው ምክንያት ጌታችን በአደባባይ የሚያስተምረውን ትምህርት ከሰዎች መስማቱ ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ ከምንም በላይ ጌታ በአደባባይ የሚያደርገውን ምልክት በሕዝብ መካከል በግልጽ መጥቶ ማየት አልወደደም፡፡ ድኅነትና ነፍስን የሚመለከቱ ጉዳዮችን በጥሞና ከጌታ ሥር ቁጭ ብሎ መነጋገር ልቡ ፈቅዷል፡፡ቃሌስ በቅንነት ለሚሄድ በጎ አያደርግምን /ሚክ.2፡7/ ተብሎ እንደተጻፈ የቅንነትን መንገድ መርጦ ወደ ጌታ ቀርቧል፡፡

ኒቆዲሞስ ከጌታ ጋር ይነጋገር ዘንድ ወደደ፡፡ ጌታ እንኳን ከሕዝቡና ከደቀመዛሙርቱ ተለይቶ ከአብ ጋር ሲነጋገር የሚያድርበት ጊዜ ነበር፡፡ እኛማ ሌሊቱን በሙሉ ከእግዚአብሔር ጋር እንደምን መነጋገር ይገባን ይሆን፡፡ በተለይ በሌሊት ሁሉንም ነገር ትተን ከጌታ ጋር የግል ጭውውት ማድረግ ይጠበቅብናል፡፡ አዲሱን ሕይወትና የዚህን ሕይወት ባህርይ፣ በዚህ ሕይወትም ውስጥ ካለች ከመንፈስ ሕብረት ተካፋዮች እንሆን ዘንድ ይገባናል፡፡

2.ሁለተኛው ምክንያት ምናልባት ጥበብን ለመማር የማታው ጊዜ የተሻለ እንደሆነ በመረዳቱ ነው፡፡ ጌታ ቀን ቀን ሕዝቡን በማስተማር ተይዞ እንደሚውል ያውቃል፡፡ ስለዚህ ኒቆዲሞስ ምሽት እስከሚመጣ ድረስ ጠበቀ፡፡ ጌታን ለማግኘትና የድኅነት ጨዋታን ይጨዋወቱ ዘንድ ወደደ፡፡

3.ሦስተኛው ምክንያት አንዳንድ ምልክቶችን ከተመለከተ በኋላ ጌታን ለማግኘት የመጀመሪያውን ዕድል በምሽት አግኝቶ ይሆናል፡፡ ሁሉም ሰው ሲተኛ ከጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር መንፈሳዊ የሆነች ምሽትን ማሳለፍ ፈልጎ ይሆናል፡፡ ምናልባትም እንዲህ አይነት ዕድል ወደፊት ሊገጥመው እንደማይችል ሥጋት አድሮበት ሊሆን ይችላል፡፡

4.አራተኛው እንደ ነቢዩ ዳዊት ምሳሌውን ሊከተል ፈልጎ ::ዳዊት ሌሊቱን ለምስጋና ይጠቀምበት ነበርና /መዝ.36፡6፤119፡148/

5.አምስተኛው ምናልባትም ኒቆዲሞስ ወደ ጌታ ዘንድ እየሄደ መማሩ ለካህናት አለቆች ወሬው ሊደርስ ይችላል ብሎ ከፍርሃት የተነሣ ሊሆን ይችላል፡፡

6.ስድስተኛው ኒቆዲሞስ ወደ ጌታ ዘንድ መድረሱን አይሁድ ቢያውቁ ጌታችንን ለመዋጋት ቁጣቸውን ይጨምርላቸዋል፡፡ ኒቆዲሞስን ራሱን ለመጉዳት አይሁድ ፈሪሳውያን ሊነሳሡበት ይችላሉ፡፡ ምንም እንኳን በጌታ ትምህርት የተሳበ ቢሆንም በቀን እንዳይሄድ እምነት አንሶት ሊሆን ይችላል፡፡

7.ሰባተኛው ምክንያት ከምንም በላይ ጌታ የዓለም ብርሃን መሆኑን በእርግጠኝነት አለመረዳቱ ነው፡፡ ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ ነው፤ የእስራኤል መምህር ነው፡፡ ሰማያዊውን ደስታ ገንዘብ ያደርግ ዘንድ አዲስ ልደት የሚያስፈልገው ሰው ነው፡፡ በምሽት ሲመጣ ደካማ የሆነ እምነትን ይዞ ነበር የመጣው፤ ነገር ግን የጌታ በር ተከፍቶ አገኘው፡፡ ጌታ ስሜቱን ሊጎዳው አልወደደም፡፡

ሁሉ ነገር የሚቆጠረው እምነት እንደሰናፍጭ ቅንጣት ቀስ በቀስ በልቡ ውስጥ እንደሚያድግ ነበር፡፡ ጌታ የፈለገው ያች ቅንጣት አብባ፣ አፍርታ፣ ጌታ በሚሰቀልበት ጊዜ ትልቅ ዛፍ ትሆን ዘንድ ነበረ፡፡ እንደዚያ ሲሆን ነው በዚያ እምነት ደረጃ ላይ ሲደርስ ነው በድፍረት የጌታን ሥጋ የቀበረው፡፡

ኒቆዲሞስ ከጌታ ጋር በተገናኘ ጊዜ የአይሁድ ድካም በእርሱም ላይ ይንጸባረቅ ነበር፡፡ አስቀድመን እንዳልነው በብርሃን ሳይሆን በጨለማ የመምጣቱም ምክንያት ይህ ነበር፡፡ ነገር ግን መኃሪው አምላክ አልጠላውም፤ ትምህርቱንም አልከለከለውም፡፡ ከዚህ በተቃራኒው ጌታ በጉጉት ከእርሱ ጋር ተነጋገረ፤ ከፍ ያለውንም ምስጢር ገለጠለት፡፡ በርግጥ ለኒቆዲሞስ የተሰወረ ነበረ፡፡ ጌታ ግን አብራራለት፤ ክፉ አሳብ ከነበራቸው ወገኖች አንጻር ሲመዘን ይህ ሰው ይቅርታን ያገኝ ዘንድ እንደሚገባው ጌታ ቆጥሯልና፡፡ ክፉ ሰዎች ይቅርታ የላቸውም፡፡

ምንም እንኳን ኒቆዲሞስ ከአይሁድ የተለየ ቢሆንም ጌታን የቆጠረው ሰው አድርጎ ነው፡፡ ይናገረው የነበረው እንደ ነቢይ ነው፡፡ ያደረገውን ምልክት እያደነቀ ነበር የጠየቀው፡፡

መምህር ሆይ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን /ቁ.2/ አለው፡፡

ታዲያ ኒቆዲሞስ ሆይ ስለምን በምስጢር በምሽት መጣህ? ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣ የእግዚአብሔር የሆነውንም ነገር እንደሚናገር እያወቅህ፡፡ ስለምን ከእርሱ ጋር ነገሮችን በግልጽ አልተወያየህም? ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኒቆዲሞስን እንዲህ ዓይነት ጥያቄዎችን አልጠየቀውም፡፡ አልወቀሰውምም፡፡ ነቢዩ እንዲህ ይላል €œአይጮኸም፤ ቃሉንም አያነሣም፣ ድምፁንም በሜዳ አያሰማም፡፡ የተቀጠቀጠ ሸምበቆን አይሰብርም፣ የሚጨስንም ክር አያጠፋም€ /ኢሳ.42፡3/ ጌታ ራሱ እንዲህ ብሏል፡፡ ዓለሙን ላድን እንጂ በዓለሙ ልፈርድ አልመጣሁም፡፡ /ዮሐ.12፡47/

€œእግዚአብሔር ከርሱ ጋር ከሆነ በስተቀር አንተ የምታደርጋቸውን እነዚህን ምልክቶች ሊያደርግ የሚችል የለምና /ቁ.2/

የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ትሕትና ተመልከቱ! እንዲህ አላለም €œእኔ ሁሉን በራሴ ማድረግ ይቻለኛልና የማንም እርዳታ አያስፈልገኝም፡፡ እኔ ራሴ እግዚአብሔር ነኝ፡፡ የያዝኩት ኀይል የአባቴን ኀይል ነው፤ ይህንን ቢል ለሚያዳምጡት ወገኖች ከባድ በሆነ ነበር፡፡

ነገር ግን ድርጊቱን ሲፈጽም በተመሳሳይ መንገድ አልነበረም፤ ምልክትን ሲያደርግ በኀይል ነው፤ ስለዚህም እንዲህ አለ €œልትነጻ እወዳለሁ /ማቴ.8፡3/ ጣቢታ ተነሽ /ማር.5፡4/ እጅህን ዘርጋ /ማር.3፡5/ ኀጢአትህ ተሠረየችልህ /ማቴ.9፡2/ ፀጥ በል /ማር.4፡39/ አልጋህን ተሸከምና ሂድ /ማቴ.9፡6/፤ አንተ ርኩስ መንፈስ ከዚህ ሰው ውጣ /ማር.5፡8/፤ ማንም ስለምን እንዲህ ታደርጋላችሁ ቢላችሁ ለጌታ ያስፈልገዋል በሉት ማር.11፡3/፤ ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትሆናለህ /ማር.23፡43/፡፡ ለቀደሙት አትግደል እንደተባለ ሰምታችኋል የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል እኔ ግን እላችኋለሁ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል፡፡ /ማቴ.5፡21-22/ ተከተለኝ ሰውን አጥማጅ አደርግሃለሁ /ማቴ.1፡17/፡፡

በማንኛውም ሁኔታ ታላቅ ሥልጣኑን እንመለከተዋለን፡፡ ስለዚህ ሲሠራ ማንም ወገን በርሱ ላይ ስህተትን ማግኘት አይቻለውም፡፡ ነገር ግን ሊያጠምዱበት የሚቻላቸው በአንድ መንገድ ብቻ ነው እርሱም በንግግሩ ብቻ ነው፤ ማለት ንግግሩን በተሳሳተ መንገድ በመተርጎም፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል፡-

ስለዚህ ነው ጌታ ኒቆዲሞስን በግልጥ ያናገረው፤ ነገር ግን የአብ የባሕርይ ልጅነቱን በመግለጽ አልጀመረም፤ ምልክት የሚያደርገው በተመሳሳይ ሥልጣን መሆኑን አልገለጠለትም፡፡

ኒቆዲሞስ በሥሙ ከሚያምኑ ከጌታ ጋር ግን ግንኙነት ከሌላቸው ወገኖች አንዱ ነበረ፡፡ ስለዚህ በምሽት ወደ ጌታ ዘንድ መጣ፡፡ የመጣው ወደ ብርሃን ቢሆንም በጨለማ መጣ፡፡

ምንም እንኳን ኒቆዲሞስ የመጣው ወደ ጌታ ቢሆንም የመጣው በምሽትና የሚናገረው በጨለማ ነፍሱ ነበር፡፡ ስለዚህ በሰው ሁሉ ላይ የሚያበራውን ብርሃን የሚናገረውን መልእክት ሊረዳው አልተቻለውም፡፡

ኒቆዲሞስ መምህር ነበረ ወደ እውነተኛው ብርሃን በጨለማ የመምጣቱ ምስጢርም ምናልባት ለክብሩ ተጠንቅቆ ነው፡፡ የሚናገረውን ማንነት ገና አላወቀምና፤ መማሩ እንዲያፍር አደረገው፤ በግሌ እኔ መምህርን ማዳመጥ እንጂ ሰዎች እንደመምህር ሲያዳምጡኝ አይደለም የምጠቀመው፡፡ የመጀመሪያ በመሆን ፍላጎትና ዝንባሌ ያላቸውን ወገኖች ጌታ እንዲህ ብሎ ሲገሥጻቸው አውቃለሁ፡፡ እናንተ ግን መምህር ተብላችሁ አትጠሩ መምህራችሁ አንድ ነውና /ማቴ.23፡8/

በማንኛውም ሁኔታ ኒቆዲሞስ በምሽት ወደ ጌታ የመጣው ለመጠመቅ አልነበረም ለመማርና የጌታ ደቀመዝሙርም ለመሆን አይደለም፡፡

በአይሁድ ትውፊት መሠረት ማንም ወገን በምሽት ወደ አይሁድ እምነት፣ ለመገረዝ ወይም ለመጠመቅ አይመጣም፡፡ ይህ ሕግን መተላለፍ ነው፡፡ እንደ ተማሪ ከጌታ ሥር ቁጭ ብሎ ለመማር ሳይሆን የጌታን አሳብ ለማወቅና በጎዳናውም ይጓዝ ዘንድ ነው፡፡

ለአንድ ቅዱሳት መጻሕፍትን ጠንቅቄ አውቃለሁ ለሚል የአይሁድ መምህር ረቢ ብሎ ጌታን መጥራት ቀላል ነገር አይደለም፡፡ የሕዝብ አለቃ ነኝ ብሎ የሚያስብ ሰው በትህትና ረቢ ብሎ ሲናገር መመልከት በርግጥም ያስደንቃል፡፡€œመምህር ሆይ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን/ቁ.2/ ምንም እንኳን ኒቆዲሞስ የአይሁድ መምህር ቢሆንም የተናገረው ፖለቲካ ወይም የአገር ጉዳይ አይደለም፡፡ ነፍሱ ስለምትድንበት ሁኔታ ብቻ ነው የጠየቀው፡፡

ኒቆዲሞስ ስለ ጌታ አንድ ነገር ያውቃል፤ ጌታ በአይሁድ ምሁራን ወይም በታወቀ የአይሁድ ትምህርት ቤት ገብቶ የተማረ አይደለም፡፡ ትምህርቱ ከሰማይ ነው፡፡ ጌታ የያዘው የእውነትን ኀይል እንጂ የሰይፍን ኀይል አለመሆኑን ተገነዘበ፡፡ የሰውን ጥበብ ባለፈ ፍጹም መለኮታዊ ጥበብ እንደሚናገር ተገንዝቧል፡፡ የሚያደርገው ምልክት በመለኮታዊ ኀይል መሆኑን ተገንዝቧል፡፡

በጣም አስደናቂው ንግግሩ €œእናውቃለን€ የሚለው ነው፡፡ ምናልባት ከርሱ ጋር ሌሎች ሰዎች እንዳሉ ያመለክታል፤ ወይም ፈሪሳውያንን ወክሎ እየተናገረ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም ምግባቸውም መጠጣቸውም ወሬአቸውም ክርስቶስ ሆኗልና፡፡ ከእነርሱ መካከል ኒቆዲሞስ የሚያምነውን እምነት የሚያምኑ ፈሪሳውያን ሊኖሩ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ከእነርሱ መካከል ጌታን በግልጥ ወይም በስውር ሊያገኘው የፈለገ ወገን የለም፡፡

ኢየሱስም መልሶ እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው /ቁ.3/€

ኒቆዲሞስ ምልክትን ማድረግ ለክርስቶስ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደሆነ ለማመኑ ማሣያ አድርጎ ቆጥሮ ነበር፡፡ ምክንያቱም የአይሁድ ረበናት እምነትን ምልክት ከመሥራት ጋር አያይዘውታልና፡፡ ስለ ክርስቶስ ማንነት ለመመስከር ከዚህ ወንዝ ባሻገር ያቋረጠው የለም፡፡ ስለዚህ ጌታን ዕሤተ በጎነት ያለው መምህር፣ የእግዚአብሔር ሰው አድርጎታል፡፡ እግዚአብሔር ይስሐቅን €œአትፍራ እኔ ከአንት ጋራ ነኝና /ዘፍ.26፡24/ እንዳለው ሰው ዓይነት አድርጎ ገምቶት ነበር፡፡ ወይም እንደ መበለቲቱ ልጅ ኢያሱ ከሙሴ ጋር እንደ ነበርሁ ከአንተም ጋር እሆናለሁ /ኢያ.1፡5/ ያለው ዓይነት ነቢይ ነበር ጌታ ለኒቆዲሞስ፡፡

ሌሎች ብዙ አለቆችና ነቢያት ተመሳሳይ ልምድ ነበራቸው፤ ነገር ግን ኒቆዲሞስ ምንም እምነትን ይዞ ቢመጣም ከፈሪሳውያን ጠባብ አስተሳሰብ ልጓም እንዳይወጣ የሚያደርግ አዕምሮ ነበረው፡፡ የተማረውም ይኼንን እውነታ ነው፡፡ በጌታና በኒቆዲሞስ መካከል የነበረው ውይይት የሚከተሉት ነጥቦች የትኩረት አቅጣጫዎቹ ነበሩ፡፡

1.የዳግም ልደት አስፈላጊነት እርሱም ውስጣዊው ዓለም የተሻለ እንደሆነ የሚያሳይ ነው፤ እርሱም የእግዚአብሔር መንግሥት ነው፡፡ ይህ አባባል በቅብጥ፣ በሶርያ፣ በላቲን በመጀመሪያይቱ ቤተ ክርስቲያን አባቶች ጽሑፍ የተካተተ ነው፡፡ ዮስጢኖስ፣ ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ፣ ጠርጡለስ፣ አውግስጢኖስና፣ ዠሮም ለአብነት ይጠቀሳሉ፡፡ጌታችን ኒቆዲሞስን እንደገና እንዲወለድ እንደጋበዘው ተረድቷል፡፡ ይህ አስደነቀው፡፡ አሳቡ በልቡ ውስጥ መዳህ ጀምሯል፡፡ ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል አለ፡፡

2.አዲሱ ልደት ከላይ ነው ሰማያዊ ነው /3/ ይህ ድርጊት በቅዱሱና በሰማያዊው የእግዚአብሔር መንፈስ ብቻ የሚፈጸም ነው፡፡ የሰውን አሳብ ሁሉ ያለፈ ስጦታ ነው፡፡

3.አዲሱ ልደት የሚፈጸመው በውኃና በመንፈስ ነው /5/

4.ይህ ልደት በኀይል ያለ በነፍስ የተመሰለ ነው፡፡ ስለዚህ ማንም ምስጢሩን ሊገነዘበው አይችለም፡፡

በአይሁድ ጽሑፍ እውነት የሚለው ቃል መደገሙ በእውነት ቅዱስ ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ነው፤ ጌታችን የሚናገረው ነገር በጣም ጠቃሚና ትኩረት የሚያሻው መሆኑን ለመናገር ይጠቀምበታል፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱሱ ክርስቶስ በርጋታ ለኒቆዲሞስ የገለጸለት ኢየሱስ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ዘንድ መምህር መሆኑን ማመን ብቻውን በቂ አለመሆኑን፣ ተአምራቱንም ማድነቅና የተለዩ መሆናቸውን ማወቅ በራሱ ግብ አለመሆኑን ነው፡፡ በርግጥም የሚያስፈልገው እንደገና መወለድ ነው፡፡ እርሱም ሰማያዊ የሆነ ልደት ነው፡፡ ሰማያዊ መንፈሳዊ የሆኑ ጉዳዮችን ለማየት ያስችላልና፡፡ በእናቱ ማኅፀን ያለ ፅንስ በዚህ ዓለም እየሆነ ስላለው ነገር የሚያውቀው ነገር የለም፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ አንድ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በስተቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት መመልከት አይቻለውም፡፡ እንደገና ከተወለደ ብቻ ነው የአዲሱን ዓለም ብርሃን መመልከት የሚችለው፡፡

ሊያይ የሚለው ጌታችን አጽንዖት ሰጥቶ የተናገረው ግሥ ለእውነተኛ ክርስቲያን አስፈላጊ ነው፡፡ አዲሱን ልደት ያጣጥም ዘንድ ስለተወለደ እንዲመካ አይደለም የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊመለከት ለመንግሥቱም እንደሚገባ ሊመላለስ ይገባዋል እንጂ፡፡

ይህ ማለት አዕምሮውና ልቡ ሰማያዊ በሆነ ነገር ላይ ማተኮር አለበት ማለት ነው፡፡ ከሰማያዊ ሕግ ጋር አብሮ የሚሄድ ሕግን ያለማወላወል ሊከተል ይገባዋል፡፡ አዲስ ግብ፣ አዲስ ተስፋ አዲስ ኀይልን ገንዘብ አድርጎ፡፡

በአዲሱ ልደት ክርስቲያን በአይነቱ የተለየ ኑሮን መኖር ይጀምራል፤ አሮጌውን የሰውነቱን ሕንፃ አፍርሶ መሠረቱ ክርስቶስ የሆነውን አዲስ ሕንፃ በማነጽ አሮጌው ሰዋችን ተወግዶ የክርስቶስን መልክ የያዘው አዲሱ ሰው ሊታይ ይገባዋል፡፡

አስቀድመን ኀጢአት ጥንተ ተፈጥሮአችንን ስላጠፋው፣ የልባችንም ጥልቅ በኀጢአት ተይዞ ስለኖረ፣ ሥጋውያን በሥጋ ሕግና ፈቃድም የምንመራ ሆነናል፡፡ የምንመራውም የመልካም ነገር ጠላት በሆነ በዲያብሎስ ነበረ፤ ስለዚህ አዲሱ ልደት ልንሸሸው የማይገባ ጠቃሚ ጉዳይ ሆኖ ቀርቧል፡፡ እውነት እውነት እልሃለሁ የሚለው የጌታ ቃል ለዚህ እውነት ማሣያ ነው፡፡

የእግዚአብሔር መንግሥት ምንድነው? ከሰማያዊው መሲሕ ሌላ መመልከት እንደሌለብን የምታሳስብ መንግሥት አይደለችምን! በእኛ መካከል መንግሥቱን መሥርቶ ይኖራል፡፡ ከእርሱ ጋር አንድነትን ፈጥረን የምናየው፣ የምንኖረው ሁሉ ለዚህ ሕይወት እንደሚገባ ነው፡፡ እርሱ ቅዱስ ስለሆነ እኛም ቅዱሳን እንሆናለን፡፡ በእኛ የሚኖረው የእግዚአብሔር መንግሥት ትክክለኛ ትርጉምም ይኼው ነው፡፡ ጌታ መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንሥሐ ግቡ /ማቴ.4፤17/ አለ፡፡ እንደገናም መንግሥተ ሰማያት በመካከላችሁ ናት /ሉቃ.17፡21/ ብሏል፡፡ በእግዚአብሔር መንግሥት ያለንን ሥፍራ ሲናገር፡፡ ጌታ መንግሥትም ለአምላኩና ለአባቱም ካህናት እንድንሆን ላደረገ /ራዕ.1፡6/ ይላል፡፡

ይህ መንግሥት ከጌታችን ከመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ኅብረትን የምንፈጥርበት መንግሥት በመሆኑ እንዲህ ተብሏል፡-€œየእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችም€ /ሮሜ.14፡17/

ይህ መንግሥት ለዘላለማዊ ሕይወት ዋስትና ነው፡ ወደ ሰማይ እንድንጓዝ ጌታ በጌትነቱ ሲመጣ አስደናቂውን ክብር እንድንካፈል ያደርገናል፡፡ ከምንም በላይ አሳባችንን ከፍ ከፍ አድርጎ ውስጣዊ ነፍሳችንን የመጨረሻውን ቀን እንድትመለከት ጌታ ሲመጣ ሰማያዊ ዘውድን ደፍተን ያለፍርሃት በፊቱ እንቆም ዘንድ የሚያስችለንን ጸጋ እንይዝ ዘንድ ያስችለናል፡፡

የጌታን ቃል እንደገና በሌላ አባባል እንግለጠው ብንል ዳግመኛ ካልተወለድህ ከመንፈስ ጋር ኅብረት ካልፈጠርህ በጥምቀት ልጅነትን ካላገኘህ እኔን በተመለከተ ትክክለኛ የሆነውን አሳብ አታገኝም´የሚል ይሆናል፡፡

€œኒቆዲሞስም ሰው ከሸመገለ በኋላ እንዴት ሊወለድ ይችላል ሁለተኛ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን? /ቁ.4/ በማለት ጠየቀ፡፡

የኒቆዲሞስ ጥያቄ የእውቀት ድካሙን ይገልጣል፡፡ ጌታ የሚናገረው በመንፈሳዊ ቋንቋ ነው፡፡ የኒቆዲሞስ ልብ ነገሮችን የሚያገናኘው ቁሳዊ ዓለማዊ ከሆኑ ነገሮች ጋር ነው፡፡ ቁሳዊ ነገሮችን ከልቡናው ከአእምሮው ካላወጣ መንፈሳዊና ሰማያዊ የሆኑ ምስጢራትን እንደምን ሊገነዘብ ይችላል? ያኔ ነው ወደ እውነት መድረስ የሚቻለው፡፡ በእግዚአብሔር መንፈስ አዲስ መንፈሳዊ ጉልበትን ይዞ ምስጢርን መረዳት የሚቻለው፡፡

ኒቆዲሞስ ጌታ በተናገረው አዲስ ልደት ተደንቋል፤ ልክ እንደ ሌሎች አይሁድ ዘመዶቹ የአብርሃም ዘር በመሆኑ የሚመካ ነው፡፡ ጌታ ደግሞ እንደገና ተወለድ እያለው ነው፤ አይሁድ ለእግዚአብሔር የተመረጡና የተወደዱ አድርገው ራሳቸውን ይቆጥሩ ነበር፡፡

በነቢያትና በተስፋው ቃል ኪዳን የተቀደሱ ሕዝቦች ነን ይሉ ነበር፡፡ ከምንም በላይ እግዚአብሔር ከእነርሱ አባቶች ጋር ቃል ኪዳን ገብቶ ነበር፡፡ ልዩ መቅደስና መሥዋዕትም ነበራቸው፡፡ ኒቆዲሞስ እስራኤላዊ ብቻ አልነበረም ፈሪሳዊም ጭምር እንጂ፡፡

ምን ዓይነት ከዚህ የበለጠ ልደት ጌታ ይሰጠኛል ብሎ ሊያስብ ይችላል? አይሁድ መሲሑ ሲመጣ የእስራኤል መንግሥት እንደሚያምንበት እንደገናም እንደሚወለዱ ይገምታሉ፡፡ ነገር ግን አስቀድሞ በነበራቸው ኩራትና ትምክህት አንጻር ሲመዝኑት ይህ የሚሆን አይመስላቸውም ነበር፡፡ እነርሱ አሁን ከያዙት የአብርሃም ልጅነት የከበረ ልደት ያለ መስሎ አይታያቸውም ነበር፡፡ ስለ ትውልድ ሀገራቸው ይመኩ ነበር፤ ስለዚህ ሌላ ልደት መስማት የሚሆንላቸው አይደለም፡፡

ይህ ሁሉ ነገር እያለ ኒቆዲሞስ ጀርባውን ለጌታ አልሰጠም፤ እርሱ የጎደለው አንድ ነገር እንዳለ አምኖ ትምህርቱን ቀጥሏል፡፡ በግብሩ ምንም እንኳን መምህርና አለቃ ቢሆንም በትሕትና እውነተኛ የሆነ ነገርን ለመማር የተዘጋጀ መሆኑን ገልጧል፡፡ ነገር ግን ጌታ የሚለው አዲስ ልደት የማይቻል እንደሆነ ገምቷል፡፡ አስደናቂ ሰው ነው፡፡ ረጅም ዘመን የትምህርትና የአመራር ልምድ ያለው ሰው ከጌታ እግር ሥር ተንበርክኮ አዲስ ነገርን ሲማር መመልከት ያስደንቃል፡፡ ለእውነተኛ አለቃ ጌታ የሰጠው ምሳሌ አስቸጋሪ ሊሆንበት ይችላል፡፡ አሁን ኒቆዲሞስ ስለ ትምህርትና ስለ አመራር ልምዱ ሲመካ አንመለከተውም፡፡ እስከመጨረሻው እስትንፋሱ ድረስ ሲማር እንጂ፡፡ አምብሮስ እንዲህ ይላል፡- የኒቆዲሞስ ሁኔታ የሚያሳየን መማር የማያስፈልገው እግዚአብሔር ብቻ መሆኑን ነው ይላል፡፡

ኒቆዲሞስ ወደ ጌታ መጣ፤ ከፍ ያሉ ነገሮችን አዳመጠ፡፡ እንዲህ ዓይነት ጉዳዮች ተራ ሰው የሚገልጣቸው አይደሉም፡፡ ማንም ሰውም ከዚህ አስቀድሞ ሰምቷቸው አያውቅም፡፡ በቅፅበት ኒቆዲሞስ ወደ ከፍታ ወጣ፤ ነገር ግን መረዳቱ ጨለማ ነበር፡፡ ነገር ግን በራሱ ማስተዋል ገና የቆመ በመሆኑ ሊሸከማቸው ስላልቻለ ወደቀ፤ የጌታን ቃል እንዴት ሊሆን ይችላል? በማለት ጠየቀ፡፡ ጌታ የተናገረውን ነገር እንዲያብራራለት ሰው ከሸመገለ በኋላ ወደ እናቱ ማኅፀን ገብቶ ይወለድ ዘንድ ይችላልን በማለት ማብራሪያ ጠየቀ፡፡

ኒቆዲሞስ ስለ መንፈሳዊ ልደት ሰምቷል፡፡ ነገር ግን በመንፈስ አልተለማመዳቸውም /አያውቀውም/፡፡ኒቆዲሞስ ትውክልቱን ያደረገው ቁሳዊ መረጃ ላይ ነው ፤ይህንን ትልቅ ትርጉም ለመረዳትና ለመተርጎም ምሳሌ አድርጎ ያቀረበው የሰውን የሥጋ ልደት ነው፡፡ ይህንን ሁኔታ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ በማለት ይገልጠዋል €œለፍጥረታዊ ሰው የእግዚአብሔር መንፈስ ነገር ሞኝነት ነውና አይቀበለውም በመንፈስም የሚመረመር ስለሆነ ሊያውቀው አይችልም€ /1ቆ.2·14/

በዚህ ሁሉ ነገር ኒቆዲሞስ ክብርና ጉጉት ይታይበታል፡፡ ጌታ የነገረው ነገር አላስቆጣውም፡፡ ነገር ግን ይህ ሁኔታ የማይቻል መሆኑን አስቦ ጥያቄ ጠይቆ ዝም አለ፡፡ ሁለት ነገሮችን ተጠራጥሯል፡፡ ምን አይነት እንደገና መወለድ እና የእግዚአብሔር መንግሥት፡፡ አይሁድ በየትኛውም ጊዜ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት የተናገሩት ነገር የለም፡፡ ስለ ዳግም ልደትም እንዲሁ፡፡ ስለነዚህ ነገሮች ሰምተውም አያውቁም፡፡ ኒቆዲሞስን ያስደነቀውም ነገር ይህ ነው፡፡

ቅዱስ አውግስጢኖስ እንዲህ ይላል፡- ይህ ሰው ከአዳምና ከሔዋን የሚደረግ ልደትን ሰምቷል፤ ከእግዚአብሔርና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስለሚደረገው ልደት ግን አያውቅም፡የሚያውቀው ዘርን የሚተኩ ወላጆች በሞት ፍጻሜያቸውን እንደሚያገኙ ነው፡፡ ነገር ግን ሕይወትን ስለሚሰጠው ስለ አዲሱ ልደት ያለው ግንዛቤ ከመረዳት በታች ነው፡፡ ንብረታቸውን የሚወርሱ ልጆችን የሚወልዱ ቤተሰቦች ያውቃል፡፡ ነገር ግን ዘወትር የሚኖሩ ልጆችን የሚወልዱ የማይሞቱ ወላጆችን በተመለከተ እውቀት የለውም፡፡ ሁለት ዓይነት መወለድ አለ፡፡ አንደኛው በምድር የሚደረግ ሁለተኛው ሰማያዊ፡፡ የመጀመሪያው ከሥጋና ከደም ሁለተኛው ከውኃና ከመንፈስ፤ የመጀመሪያዎቹ ለሞት የተጋለጡ ናቸው የኋለኞቹ ዘላለማውያን ናቸው፡፡ የመጀመሪያዎቹ የተወለዱት ከወንድና ከሴት የኋለኞቹ ከእግዚአብሔርና ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ኒቆዲሞስን በተመለከተ የሚያውቀው አንድ ልደትን ብቻ ነው፡፡

ኢየሱስም መለሰ እንዲህ ሲል እውነት እውነት እልሃለሁ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በስተቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡ /5/

ጌታ ይህንን እውነት ዝቅ አድርጎ እንዳይመለከተው በማሰብ አስቀድሞ የተናገረውን ነገር ደገመለት ፡፡ በርግጥ የእግዚአብሔር ቃል አዎ አይደለም ከሚለው አፍአዊ ነገር በዘለለ መልስን የሚጠይቅ ነው፡፡ ምንም እንኳን ኒቆዲሞስ ከመረዳት አቅሙ በላይ ቢሆንም ጌታ እንደገና መወለድ ትምህርቱ ላይ ጠንከር ብሎ ሄዷል፤ ያለዚህ ልደት የእግዚአብሔርን መንግሥት ለማየትም ለመግባትም የሚያስችል መንገድ የለም፡፡

ሰው ከውኃና ከመንፈስ መወለድ አለበት ይላል፤ ስለምን ውኃን ይጠቀማል? ውስጣዊ የመንፈስ መታጠብን ለማመልከት ነው፡፡ /ቲቶ.3፡5፣ 1ቆሮ.6፡11፣ ሕዝ.36፡25/ €œ

ይህ ውስጣዊ የመንፈስ መታጠብ በመንፈስ ቅዱስ የሚፈጸም ነው፡፡ እርሱ ብቻ ያጥባል ያነጻል ውስጣዊ ልባችንን አዲስ ያደርጋል፡፡ ጌታ በሰርግ ቤት ተገኝቶ ውኃውን ወደ ወይን በመቀየር በሰርጉ ቤት ለነበሩ ዕድምተኞች ደስታን እንደሰጠ በመንፈሱ የሰጠው ውጫዊ የሰውነት መታጠብ አይደለም፡፡

ይህ ውኃ ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣ ይጠጣ በማለት ለሳምራዊቷ ሴት የነገራት የሕይወት ውኃ ነው፡፡ በያዕቆብ ጉድጓድ ውስጥ እንዳለው ውኃ አይነት አይደለም ያዕቆብ፣ ልጆቹና፣ ከብቶቹ የጠጡት ውኃ የሚያረካው የሥጋን ጥማት ነው፡፡ ጌታችን የሚሰጠን ውኃ ግን የነፍስን ጥማት የሚያረካ ነው፡፡

በአዲሱ ልደት ውኃ አስፈላጊ ሆኗል፤ ጥምቀት የሚፈጸመው በመዘፈቅ ነውና፡፡ ይህም ሞትን የመቀበልና ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር የመቀበር ምልክት ነው፡፡ ከእርሱ ጋር እንነሣ ዘንድ የግድ ያስፈልገናል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይላል፡-

እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፣ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን€

ከውኃና ከመንፈስ መወለድ የአሮጌውን ሰው መሞትና የአዲሱን ሰው ትንሣኤ ይጠይቃል፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የሆነውን አዲስ ሕይወትም መቀበል ነው፡፡ እርሱም የትንሣኤ መንፈስ ነው፡፡ ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር የሚያደርገንን አዲሱን ሰው የመፍጠር ሂደት ነው፡፡ በፈጣሪያችን መልክ የተፈጠረውን አዲስ ሰው መመልከት ነው፡፡

በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አምነው መስቀሉን ሊሸከሙ የሚወዱ ወገኖች በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም መጠመቅ አለባቸው፡፡ የጌታ ቃል ትርጉም ለኒቆዲሞስ ምንድነው ብላችሁ ብትጠይቁኝ መልሴ የሚሆነው ጌታ ከሥጋ ትውልድ ወጣ ብሎ መንፈሳዊውን ትውልድ እንዲያስብ ሳበው የሚል ይሆናል፡፡

ጌታ እንዲህ በማለት የነገረው ይመስላል፡፡ ኒቆዲሞስ ሆይ እየተናገርሁህ ያለሁት ስለ ሌላ ልደት ነው፡፡ ስለምን ነው ንግግሬን ወደ ምድራዊ ነገር የምታወርደው፡፡ ስለምን የምነግርህ ነገር በተፈጥሮ ሕግ እንዲገዛ ታደርጋለህ? ይህ ትውልድ /ልደት/ በአይነት በሥጋ /በምጥ/ ከሚደረገው ትውልድ የተለየ ነው፡፡ አጠቃላይና የተለመደ ከሆነ ልደት ራስህን አውጣ፤ እኔ ሌላ ልደት ወደሚገኝበት መንፈሳዊ ዓለም ሾሜሃለሁና፡፡ ሰዎች ሁሉ ከዚህ አዲስ ልደት እንዲወለዱ እወዳለሁ፡፡ አዲስ ዓይነት ልደትን ይዤ ወደ ምድር መጥቻለሁ፡፡ ሰውን የፈጠርሁት ከምድር አፈርና ከውኃ ነበር፡፡ ይህ ያገለግለኛል ብዬ የፈጠርሁት ምርጥ ዕቃ የተፈጠረበትን ዓላማ ዘንግቶ አግኝቸዋለሁና እንደገና ከአፈርና ከውኃ ልሠራው አልፈቅድም እንደገና በውኃና በመንፈስ እንዲወለድ እፈቅዳለሁ እንጂ፡፡

ምናልባት ከመካከላችሁ አንዱ እግዚአብሔር ሰውን እንዴት ከውኃ ፈጠረው ብሎ ሊጠይቅ ይችላል፡፡ እኔ መልሼ እጠይቀዋለሁ፡፡ ሰውን እንዴት ከምድር አፈር አበጀው? ጭቃን እንደምን አድርጋችሁ ወደተለያየ ክፍል ትከፋፍሉታላችሁ? አጥንት፣ ነርብ፣ የደም ሥር፣ የደም ቧንቧ ከየት ተሠሩ? ቆዳ፣ ደም፣ ጉበት ከየት ተሠሩ? ይህ ታላቅ ሥራ ለምን የተከናወነ ይመስላችኋል? የተለያየውስ ቀለም? እነዚህ ሁሉ አይነቶች ውሁዶች ከየት ተገኙ? እነዚህ ሁሉ ነገሮች የምድርም የጭቃም አካል አይደሉምና፡፡

ምድር ዘርን ስትቀበል እንዴት አድርገው ሥር ይሰድዳሉ? ነገር ግን በእኛ አካል ውስጥ ሲሆኑ እነዚህ ዘሮች ይፈጫሉ፡፡ ምድር ዘርን ምን መግባ ዘር ፍሬ እንዲያፈራ ታደርጋለች? እንደገናስ ሰውነታችን እንዴት በእነዚህ ዘሮች ይገነባል? ምድር ውኃን ትቀበላለች ወደሚያፈራ ወይንም ትቀይረዋለች፡፡ የእኛ ሰውነት ግን ወይንን ተቀብሎ ወደ ውኃ ይቀይረዋል፡፡ በአሳብ የምትሰጠው ፍሬ ሁሉ የእርሷ ውጤት መሆኑን በምን በምን በምን መንገድ ነው የሚለውን ግን ማስረዳት ቀላል ነገር አይደለም፡፡ ምድር በፍሬዋ ሰውነታችንን ታጠግባለች፤ በእግዚአብሔር ላይ ያለኝ እምነት ብቻ ነው እነዚህ ሁሉ ነገሮች የምድር ውጤቶች ናቸው ብዬ እንድቀበል የሚያደርገኝ፡፡

አሁን እነዚህ ሁሉ ዓይነት ተጨባጭ ነገሮች በየቀኑ የሚከሰቱ ስለሆነ እምነት የሚይጠይቁ ስለሆነ መንፈሳዊ የሆነው ጉዳይ በቂ የሆነ ትኩረትና ቅድምና ማግኘት እንደሚኖርበት ትገነዘባላችሁ፡፡ የማይንቀሳቀሰው ምድር ለእግዚአብሔር ፈቃድ መልስ ይሰጣል ምድር የምትሸከመው ይህ ሁሉ ነገር የተገኘው ለዚህ ፈቃድ ነውና፤ በተመሳሳይ ሁኔታ ከመረዳታችን በላይ የሆነ ጽንፍ የያዘ ብዙ ምልክት ይፈጠራል፤ መንፈስ ቅዱስ በውኃ ላይ በኖረ ጊዜ ምን ተከሰተ?

ምናልባት ከመካከላችሁ አንዱ ውኃ ለዚህ ልደት ለምን ያስፈልጋል? ብሎ ቢጠይቀኝ መልሴ የሚሆነው ይህ ልደት አምላካዊ ጠቀሜታ አለው የሚል ነው፡፡ መቃብር፣ መቀበር እምነት፣ ሕይወትና፣ ትንሣኤ እነዚህ ሁሉ ምሥጢራት በጥምቀት ጊዜ የሚከናወኑ ናቸው፡፡ጭንቅላታችንን ውኃ ውስጥ እንነክራለን፤ ወደመቃብር እንደምንወርድ ሁሉ አሮጌውን ሰዋችን እንቀብር ዘንድ ጭንቅላታችንን ስናነሣ አዲሱ ሰው በተመሳሳይ ሁኔታ ይገኛል፡፡

ከመንፈስ የሚወለድ እርሱ ማነው €œእንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዶ በአእምሮው መንፈስ ከሚታደስ ሰው በስተቀር€ /ኤፌ.4፡23/ በእርግጥ ይህ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ እንደገና የተወለደ ሰው ነው፡፡

ይህ በዘላለማዊ ሕይወት የመተማመን ውጤት ነው፡፡ ይህም በጥምቀት አማካኝነት የሚፈጸም ነው፡፡ በእርግጥም እንዲህ ዓይነት ሰው እንደምሕረቱ መጠን በአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብም በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ /ቲቶ.3፡5/ መንፈሳዊ ልጅነትን የተቀበለ ነው፡፡ በሌላ ንባብ ቅዱስ ጴጥሮስ እንዲህ ይላል €œበመንፈስ ቅዱስ ስም ትጠመቃላችሁ€ /ሥራ.11፡16/፡፡ ከውኃና ከመንፈስ ከተወለደ ወገን ውጭ በመንፈስ ቅዱስ የተጠመቀ ማነው? እውነት እውነት እላችኋለሁ ከውኃና ከመንፈስ ከተወለደ ወገን ውጭ በመንፈስ ቅድስ የተጠመቀ ማነው? እውነት እውነት እላችኋለሁ ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለዳችሁ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት አይቻላችሁም፡፡

የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ በተጠመቀ ሰው ላይ ያደረ መንፈስ ቅዱስ የሚናገረውን ምስጢር ይናገራል፡፡ ጥምቀት €œለአዲስ ልደት የሚሆን መታጠብ /ቲቶ.3፡5/ ተብሏል በመንፈስ ቅዱስ የሚሆን መታደስ ነው፡፡

በምስጢረ ጥምቀት የኀጢአት እሥራት ይፈታል ስለዚህ ምክንያት ሕፃናት ሳይቀሩ ይጠመቃሉ፡፡€

€œሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በስተቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ይገባ ዘንድ አይቻለውምና፡፡

ጥምቀት ኀጢአታችን ሁሉ ያጥባል፡፡ ለእግዚአብሔር የተቀደሰ መቅደስ እንድንሆን ያደርገናል፡፡ ሰማያዊ ተፈጥሮአችንን ያድሳል ይህም በመንፈስ ቅዱስ ግብር የሚፈጸም ነው፡፡

በቅዱስ ጥምቀት ሰው ከሰይጣን ኀይል ነጻ ይሆናል፤ እንደ አርባ ቀን ሕፃንም ይሆናል፡፡ ይህም በመንፈስ ቅዱስ የሚከናወን ነው፡፡ የተጠመቀውን ሰው የሚቀድስና የሚያነጻ መንፈስ ነው፡፡ በእንደዚህ ዓይነት ሰው ላይ ሰይጣን የወደደውን ያደርግበት ዘንድ አቅሙ አይኖረውም፡፡

ሰው በጥምቀት ከክርስቶስ ጋር አንድነትን ሲፈጥር እንደገና ከመወለዱ ባሻገር ክርስቶስን በሁለንተናው ይለብሰዋል /ገላ.3፡27/ ይህን በንባብ ብቻ የምንረዳው አይደለም፡፡የፍቅር መግለጫ ነውና፡፡ይህንን የምንረዳው ጌታ ሥጋችንን ተዋሕዶ በእኛ መጠን መወለዱና ስለእኛም ሲል ለአብነት በመወለዱ ነው፡፡

የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ቅድመ ዝግጅት በኦሎንኮሚ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን

â€Â¢ መርሐ ግብሩ በማኅበሩ ድረ ገጽ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በቀጥታ ይተላለፋል፡፡

መጋቢት 11 ቀን 2007 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

002 olonkomiማኅበረ ቅዱሳን መጋቢት 13 ቀን 2007 ዓ.ም. በምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በደንዲ ወረዳ ቤተ ክህነት ኦሎንኮሚ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የሚካሔደው የሐዊረ ሕይወት መርሐ ግብር ቅድመ ዝግጅት በመጠናቀቅ ላይ ነው፡፡

አዘጋጅ ኮሚቴው ከቤተ ክርስቲያኑ ሰበካ ጉባኤና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት በመሥራት መርሐ ግብሩን የተሳካ ለማድረግ በእንቅስቃሴ ላይ ይገኛል፡፡ ኮሚቴው ወደ ስፍራው በመጓዝም ክንውኑን ገምግሟል፡፡

 

የድንኳን ተከላው እየተፋጠነ ሲሆን፤ ጊዜያዊ የመጸዳጃ ቤቶች ዝግጅት ሙሉ ለሙሉ መጠናቀቁን አረጋግጧል፡፡ የተግባር ቤት፤ የመኪና ማቆሚያ፤ የምግብ መስተንግዶ ስፍራዎች ተለይተዋል፡፡ በምእመናን አቀባበል ሁኔታም ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

የማኅበሩ ኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ክፍል በማኅበሩ ድረ ገጽ ላይ የቀጥታ ሥርጭት ለማድረግ ባለሙያዎችን ስፍራው ድረስ በመላክ ማስተላለፍ እንደሚችል ሙከራ አድረጎ ተመልሷል፡፡ በዚህም መሠረት በእለቱ ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ መርሐ ግብሩን በቀጥታ ያስተላልፋል፡፡

001 olonkomiየኦሎንኮሚ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በ1907 ዓ.ም. የተተከለ ሲሆን፤ 100ኛ ዓመቱን ጥር 16 እና 17 ቀን 2007 ዓ.ም. በድምቀት አክብሯል፡፡ ታቦቱም በ1906 ዓ.ም. ከወሎ ክፍለ ሀገር ወረኢሉ እንደመጣ፤ አሁን ባለበት ቦታ ላይ ከመተከሉ በፊት በኤጄርሳ ለፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ለአንድ ኣመት በደባልነት ቆይቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑ የተተከለው በከፍታ ቦታ ላይ በመሆኑ ቀድሞ የአካባቢው ልጆች በየዓመቱ የደብረ ታቦርን በዓል ያከብሩበት ነበር፡፡ ቦታውም “የልጆች ተራራ” እየተባለ ሲጠራ ቆይቷል፡፡

በአሰቦት ገዳም ደን ተቀስቅሶ የነበረው እሳት ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል

መጋቢት 11 ቀን 2007 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

በአሰቦት ገዳም ደን ላይ ተቀስቅሶ የነበረው እሳት ሙሉ ሙሉ መጥፋቱን ከገዳሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ማኅበረ መነኮሳቱ፤ የፌደራል ፖሊስ አባላት እና ምእመናን ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት በአሁኑ ስዓት ሙሉ ለሙሉ ለማጥፋት በመቻሉ በገዳሙ ውስጥ ማኅበረ መነኮሳቱ የተለመደውን አገልግሎታቸውን ቀጥለዋል፡፡ 

የመምህር አካለ ወልድ የሐዲስ ኪዳን የመጻሕፍት ትርጓሜ ት/ቤት የበግ ማድለብ ፕሮጀክት ተግባራዊ ሊደረግ ነው

መጋቢት 9 ቀን 2007 ዓ.ም

ከደሴ ማእከል

beg madleb 02የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ከ20 በላይ የወረዳ ቤተ ክህነት ሲኖሩት፤ እነዚህም ብዛት ያላቸው ጥንታውያን ገዳማትና አድባራትን እንዲሁም የአብነት ት/ቤቶችን አቅፎ የያዘ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱ ካሉት ጥንታውያን የአብነት ት/ቤቶች የቦሩ ሥላሴ የመምህር አካለ ወልድ የሐዲስ ኪዳን የመጻሕፍት ትርጓሜ ት/ቤት አንዱ ነው፡፡

ት/ቤቱ በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በደሴ ወረዳ ቤተ ክህነት ቦሩ በሚባል ቀበሌ በቦሩ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ ከደሴ የ10 ኪ.ሜ መንገድ ነው፡፡ ይህ ትምህርት ቤት በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻ የቀለም ቀንድ ተብለው በሚጠሩት በዐራት ዓይናው በመ/ር አካለ ወልድ የተቋቋመ ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያን የጠቀሙ ሊቃውንትን ሲያፈራ የነበረ ነው፡፡

በአሁኑ ወቅት 16 የሚደርሱ የሐዲሳት ትርጓሜ መጻሕፍት ተማሪዎችን ተቀብሎ በሀገረ ስብከቱ፣ በማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል እና በጎ አድራጊ ምእመናን ድጋፍ እየተደረገላቸው እያስተማረ ይገኛል፡፡ ት/ቤቱ በአቅም ማነስና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት ለብዙ ዓመታት ተዘግቶ የነበረ ሲሆን፤ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ቀናኢ በሆኑት በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከፍተኛ ጥረት ካለፉት 9 ዓመታት ወዲህ እንደገና ተከፍቶ ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት መፋጠን የሚያግዙ ተተኪ አገልጋዮችን እያፈራ ይገኛል፡፡

beg madlebት/ቤቱ ቀድሞ ለብዙ ዓመታት እንዲዘጋ ያደረገውና አሁንም አገልግሎቱን እየተፈታተነው ያለውን መሠረታዊ የኢኮኖሚ ችግር ቀርፎ የተማሪዎችን ቁጥር እና የጉባኤያቱን ዓይነት በመጨመር ለቤተ ክርስቲያን ተተኪ አገልጋዮችን በማፍራት ሐዋርያዊ አገልግሎትን ለማጠናከር ይቻል ዘንድ በማኅበረ ቅዱሳን የደሴ ማእከል የቅዱሳት መካናት ማኅበራዊ አገልግሎትና ልማት ክፍል ከበጎ አድራጊዎች በተገኘ ድጋፍ የበግ ማድለብ ፕሮጀክት ቀርጾ ከደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ጋር የፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የውል ሰነድ መጋቢት 3 ቀን 2007 ዓ.ም ተፈራርሟል፡፡

በእለቱ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መምህር ቆሞስ አባ ገብረ ሥላሴ በላይ እና የሀገረ ስብከቱ ሰራተኞች የተገኙ ሲሆን፤ ገንቢና ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት ከተደረገባቸው በኋላ ከሀገረ ስብከት፣ ከማኅበረ ቅዱሳን ደሴ ማእከል፣ ከት/ቤቱ፣ ከደብሩ ሰበካ ጉባኤና ከምእመናን የተውጣጡ ስድስት አባላት ያሉት ኮሚቴ ተቋቋሟል፡፡

በአሁኑ ወቅት የመገልገያ ቁሳቁሶች ተገዝተው የበጎች ማድለቢያና ማቆያ ቤት መሠራቱን የደሴ ማእከል ጸሐፊ ዲ/ን ሰለሞን ወልዴ በውይይቱ ወቅት ገልጸዋል፡፡

እንደ ጸሐፊው ገለጻ የፕሮጀክቱ ሙሉ ሥራ በሁለት ዙር የሚጠናቀቅ ሲሆን የመጀመሪያውን ዙር ቀሪ ሥራዎች በአጭር ቀናት ውስጥ በማጠናቀቅ የበግ ማድለቡ ሥራ እንዲጀመር ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡የፕሮጀክቱን የመጀመሪያ ዙር ሥራ አጠናቆ አገልግሎት ለማስጀመርም ብር 135,993 /አንድ መቶ ሰላሳ አምስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሶስት/ ብር እንደሚያስፈልግ ለማወቅ ተችሏል፡፡

በዝቋላ ገዳም የተቀሰቀሰው እሳት ለማዳፈን ጥረት እየተደረገ ነው

የካቲት 26 ቀን 2007 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

abune gm 003ከማክሰኞ የካቲት 24 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የተቀሰቀሰው እሳት በትናንትናው እለት ተባብሶ የነበረ ቢሆንም ወደ ሌላ ቦታ ሳይዛመት ከሸለቆው ውስጥ ለማዳፈን ጥረት የተደረገ መሆኑን የገዳሙ አበምኔት አባ ገብረ ማርያም ዛሬ ጠዋት በስልክ ገልጸዋል፡፡

በሸለቆው ውስጥ የተዛመተው እሳት ማኅበረ መነኮሳቱ፤ ምእመናንና የፖሊስ ኃይል ባደረጉት ርብርብ ከሸለቆው ሳይወጣ ለማቆም ተችሏል፡፡ ነገር ግን ከተዳፈነው እሳት ከፍተኛ ጭስ እየወጣ በመሆኑ እሳቱ እንዳይቀጣጠል ጥረት በማደረግ ላይ እንደሚገኙም አበምኔቱ ገልጸዋል፡፡

በገዳሙ ደን ላይ ለተከሰተው እሳት ቃጠሎ መንስኤ ከሰል በማክሰል ላይ በነበረ አንድ ግለሰብ እንደሆነ ከገዳሙ ያገኘነው መረጃ አመልክቷል፡፡

ግለሰቡ በድብቅ ከሰል በማክሰል ላይ ሳለ እሳቱ ከቁጥጥሩ ውጪ በመሆኑ ሲገለገልበት የነበረውን አካፋና ሹራብ ጥሎ እንደተሰወረ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

የካቲት 25 ቀን 2007 ዓ.ም. የእሳቱን መንስኤ ለመጣራት በወንበር ቀበሌ ጽ/ቤት ከወረዳና ከዞን ከመጡ የፖሊስ ባለሥልጣናት ጋር በተደረገ ውይይት የግለሰቡ ማንነት ታውቋል ሲሉ በስብሰባው የተሳተፉ መነኮሳት ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ ግለሰቡን ለመያዝ ክትትል እያደረገ ሲሆን፤ እሳቱ ዳግም እንዳይነሳም ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል፤፤

 

ምኩራብ(የዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት)

የካቲት 20 ቀን 2007 ዓ.ም.

የዕለተ ሰንበት መዝሙር (ከጾመ ድጓ)

ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሐረ ቃለ ሃይማኖት ወይቤሎሙ ምጽዋተ አበድር እመሥዋዕት አነ ውእቱ እግዚኣ ለሰንበት ወአቡሃ ለምሕረት እግዚኣ ውእቱ ለሰንበት ወልደ እጓለ እመሕያው ኢትግበሩ ቤተ አቡየ ቤተ ምስያጥ ቤትየሰ ቤተ ጸሎት ይሰመይ ቦአ ምኩራቦሙ ወገሠፆሙ ያርምሙ አንከሩ ምህሮቶ ሞገስ ቃሉ ወጣዕመ ነገሩ ወሣዕሣዓ አፉሁ፡፡

 

ትርጉም:- ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ፤ ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን እወዳለሁ፤የሰንበት ጌታዋ የምሕረት አባቷም እኔ ነኝ፤ የሰው ልጅም የሰንበት ጌታዋ ነው ፡፡ያባቴን ቤት የንግድ ቦታ አታድርጉት፤ቤቴስ የጸሎት ቤት ይባላል (እያለ የሃይማኖትን ቃል አስተማራቸው፡)፡ ወደ ምኩራባቸውም ገብቶ ዝም ይሉ ዘንድ ገሠፃቸው፤ እነርሱም ትምህርቱን፣ የቃሉን ግርማ፣ የአነጋገሩን ጣዕምና፣ የአንደበቱን ቅልጥፍና አደነቁ።

 

ምንባባት

መልዕክታት

(ቆላ. 2÷16-ፍጻ.)፡- እንግዲህ በመብልም ቢሆን÷ በመጠጥም ቢሆን÷ በልዩ ልዩ በዓላትም ቢሆን÷ በመባቻም ቢሆን÷ በሰንበትም ቢሆን የሚነቅፋችሁ እንዳይኖር ተጠንቀቁ፡፡ ይህ ሁሉ ይመጣ ዘንድ ላለው ጥላ ነውና። አካሉ ግን የክርስቶስ ነው፡፡ በመታለልና ራስን ዝቅ በማድረግ ለመላእክት አምልኮ ትታዘዙ ዘንድ ወድዶ÷ በአላየውም በከንቱ የሥጋው ምክር እየተመካ የሚያሰንፋችሁ አይኑር፡፡ ሥጋ ሁሉ ጸንቶ በሚኖርበት÷ በሥርና በጅማትም በሚስማማበት÷ በእግዚአብሔርም በሚያድግበትና በሚጸናበት በሚሞላበትም በራስ አይጸናም፡፡

 

ከዚህ ዓለም ኑሮ ከክርሰቶስ ጋር ከሞታችሁ እንደገና በዓለም እንደሚኖሩ ሰዎች እንዴት ትሠራላችሁ? እንዴትስ ይህን አትዳስስ÷ ይህን አትንካ÷ ይህንም አትቅመስ ይሉአችኋል? ይህ ሁሉ እንደ ሰው ትእዛዝና ትምህርት ለጥፋት ነውና፡፡ ይህም ስለ ልብ ትሕትናና እግዚአብሔርንም ስለ መፍራት÷ ለሥጋም ስለ አለማዘን ጥበብን ይመስላል፤ ነገር ግን ከሥጋ በላይ ነው እንጂ ምንም ክብር የለውም፡፡

(ያዕ. 2÷14-ፍጻ.)፡- ወንድሞቻችን ሆይ÷ እምነት አለኝ፤ ምግባር ግን የለኝም የሚል ሰው ቢኖር÷ ምን ይጠቅመዋል? በውኑ እምነቱ ልታድነው ትችላለችን? ከወንድሞቻችን÷ ወይም ከእኅቶቻችን÷ የታረዙ ወይም የዕለት ምግብ ያጡ ቢኖሩ÷ ከእናንተም አንዱ÷ “በሰላም ሂዱ÷ እሳት ሙቁ÷ ትጠግባላችሁም” ቢላቸው÷ ለችግራቸውም የሚሹትን ባይሰጣቸው ምን ይጠቅማቸዋል? እንዲሁም ሥራ የሌለው እምነት ቢኖር በራሱ የሞተ ነው፡፡

 

ነገር ግን አንድ ሰው÷ “አንተ እምነት አለህ÷ እኔም መልካም ሥራ አለኝ፤ እስቲ ሃይማኖትህን ከሥራህ ለይተህ አሳየኝ፤ እኔም እምነቴን በሥራዬ አሳይሃለሁ” ይላል፡፡ አንተም እግዚአብሔር አንድ እንደ ሆነ ታምናለህ፤ መልካምም ታደርጋለህ፤ እንዲህስ አጋንንትም ያምናሉ፤ ይንቀጠቀጣሉም፡፡ አንተ ሰነፍ ሰው÷ እምነት ያለ ምግባር የሞተች እንደ ሆነች ልታውቅ ትወዳለህን? አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ወደ መሠዊያው ባቀረበው ጊዜ÷ በሥራው የጸደቀ አይደለምን? እምነት ለሥራ ትረዳው እንደ ነበር÷ በሥራውም እምነቱ እንደ መላችና ፍጽምት እንደ ሆነችም ታያለህን?

 

መጽሐፍ÷ “አብርሃም በእግዚአብሔር አመነ፤ ጽድቅ ሆኖም ተቈጠረለት” የሚለው ተፈጸመ፤ የእግዚአብሔርም ወዳጅ ተባለ፡፡ ሰው በሥራ እንደሚጸድቅ በእምነት ብቻም እንዳይደለ ታያለህን? እንዲሁ ዘማይቱ ረአብ ደግሞ ጒበኞችን ተቀብላ÷ በሌላ መንገድ ባወጣቻቸው ጊዜ በሥራ አልጸደቀችምን? ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደ ሆነ÷ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው፡፡

 

ግብረ ሐዋርያት

(የሐዋ.10÷1-8)፡- በቂሳርያም ቆርኔሌዎስ የሚባል አንድ ሰው ነበር፤ ኢጣሊቄ ለሚሉት ጭፍራም የመቶ አለቃ ነበር፡፡ እርሱም ጻድቅና ከነቤተሰቡ እግዚአብሔርን የሚፈራ ነበር፤ ለሕዝቡም ብዙ ምጽዋት ይሰጥ ነበር፤ ዘወትርም ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ ነበር፡፡ የእግዚአብሔር መልአክም በራእይ ከቀኑ በዘጠኝ ሰዓት በግልጥ ታየው፤ ወደ እርሱም ገብቶ÷ “ቆርኔሌዎስ ሆይ÷” አለው፡፡ ወደ እርሱም ተመልክቶ ፈራና÷ “አቤቱ÷ ምንድን ነው?” አለ፤ መልአኩም እንዲህ አለው÷ “ጸሎትህም ምጽዋትህም መልካም መታሰቢያ ሆኖ ወደ እግዚአብሔር ዐርጎአል፡፡ አሁንም ጴጥሮስ የሚባለውን ስምዖንን ይጠሩልህ ዘንድ ወደ ኢዮጴ ከተማ ሰዎችን ላክ፡፡ እርሱም ቤቱ በባሕር አጠገብ ባለው በቊርበት ፋቂው በስምዖን ቤት እንግድነት ተቀምጦአል፡፡ልታደርገው የሚገባህን እርሱ ይነግርሃል፡፡” ያነጋገረውም መልአክ ከሄደ በኋላ ከሎሌዎቹ ሁለት÷ ከማይለዩት ጭፍሮቹም አንድ ደግ ወታደር ጠራ፡፡

 

ምስባክ

መዝ.68፡9፡- እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ፤ ትዕይርቶሙ ለእለይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ፤ ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ፡፡

ትርጉም፦ የቤትህ ቅንዓት በልታኛለችና የሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና ነፍሴን በጾም አስመረርኋት፡፡

 

ወንጌል

(ዮሐ. 2÷12-ፍጻ.)፡- ከዚህም በኋላ እርሱና እናቱ÷ ወንድሞቹና ደቀ መዛሙርቱም ወደ ቅፍርናሆም ወረዱ፤ በዚያም ብዙ ያይደለ ጥቂት ቀን ተቀመጡ፡፡ የአይሁድም የፋሲካቸው በዓል ቀርቦ ነበር፤ ጌታችን ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ፡፡ በቤተ መቅደስም በሬዎችንና በጎችን÷ ርግቦችንም የሚሸጡትን÷ገንዘብ ለዋጮችንም ተቀምጠው አገኘ፡፡ የገመድም ጅራፍ አበጀ፤ በጎችንና በሬዎችን÷ ሁሉንም ከቤተ መቅደስ አስወጣ፤ የለዋጮችንም ገንዘብ በተነ፤ ገበታዎቻቸውንም ገለበጠ፡፡ ርግብ ሻጮችንም÷ “ይህን ከዚህ አውጡ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉ” አላቸው፡፡ ደቀ መዛሙርቱም÷ “የቤትህ ቅናት በላኝ” የሚል ቃል ተጽፎ እንዳለ ዐሰቡ፡፡

 

አይሁድም መልሰው÷ “ይህን የምታደርግ ምን ምልክት ታሳያለህ?” አሉት፡፡ ጌታችን ኢየሱስም÷ “ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፤ በሦስተኛውም ቀን አነሣዋለሁ” ብሎ መለሰላቸው፡፡ አይሁድም÷ “ይህ ቤተ መቅደስ በአርባ ስድስት ዓመት ተሠራ፤ አንተስ በሦስት ቀኖች ውስጥ ታነሣዋለህን?” አሉት፡፡ እርሱ ግን ይህን የተናገረው ቤተ መቅደስ ስለ ተባለ ሰውነቱ ነበር፡፡ ከሙታን በተነሣ ጊዜም ደቀ መዛሙርቱ ስለዚህ እንደ ነገራቸው ዐሰቡ፤ በመጻሕፍት ቃልና ጌታችን ኢየሱስ በነገራቸውም ነገር አመኑ፡፡

 

ጌታችን ኢየሱስም በፋሲካ በዓል በኢየሩሳለም ሳለ ብዙ ሰዎች ያደረገውን ተአምራት ባዩ ጊዜ በስሙ አመኑ፡፡ እርሱ ጌታችን ኢየሱስ ግን አያምናቸውም ነበር፤ ሁሉን እያንዳንዱን ያውቀዋልና፡፡ የሰውንም ግብሩን ሊነግሩት አይሻም፤ እርሱ በሰው ያለውን ያውቅ ነበርና፡፡

 

በዝቋላ ገዳም የኢሬቻ በዓል እንደሚከበር በሚዲያ የተሰራጨው ዜና ማረሚያ እንዲሰጥበት ቅዱስ ፓትርያርኩ አሳሰቡ

የካቲት 14 ቀን 2007 ዓ.ም.

abune gm 003በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ላይ በመጋቢት ወር መጨረሻ የኢሬቻ በዓል እንደሚከበር መስከረም 15 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬሽን በኦሮምኛና በአማርኛ ቋንቋ መተላለፉ ተገቢ እንዳልሆነና ችግር ሊፈጥር የሚችል መሆኑን በመግለጽ የተላለፈው መረጃ እርማት እንዲደረግበት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳድር ለክቡር አቶ ሙክታር ከድር በጻፉት ደብዳቤ ጠየቁ፡፡

abune gebre menfes kidus 004“የሃይማኖቶች እኩልነት በታወጀበት የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕግ መንግሥት አንዱ ቤተ እምነት የሌላውን እምነት መንቀፍም ሆነ መንካት እንደሌለበት ተደንግጓል” ያሉት ቅዱስነታቸው፤ በሚዲያ ሽፋን የተሰጠው ጉዳይ ሕገ መንግሥቱን የሚተላለፍ፤ የገዳሙን መናንያን መነኮሳትና በአካባቢው የሚኖሩ ሕዝበ ክርስቲያኖችን የሚያስቆጣ በመሆኑ የክልሉ መንግሥት ለተዘገበው ጉዳይ እርማት እንዲሰጥበት ለኦሮምያ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መስተዳደር ለክቡር አቶ ሙክታር ከድር በጻፉት ደብዳቤ አሳስበዋል፡፡

ዝርዝሩን ከሚመለከታቸው አካላት እንደደረሰን የምናቀርብ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

 

የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ባለ 4 ፎቅ ሁለገብ ህንጻ እና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት አስመረቀ

 

የካቲት 09ቀን 2007ዓ.ም.

ዲ/ን ያለው ታምራት

hawassa 1aበሲዳማ፣ጌዲኦ.አማሮና ቡርጂ ሀገረ ሰብከት በሐዋሳ ወረዳ ቤተ ክህነት የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም አዲስ ያሰገነባውን ባለ 4 ፎቅ ሁለ ገብ ህንጻ እና ት/ቤት ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ፣የክልሉ ከፍተኛ ባለ ሥልጣናት እና ምዕመናን በተገኙበት የካቲት 7 ቀን 2007 ዓ.ም በድምቀት አስመረቀ፡፡

 

ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የምርቃ መርሐግብሩን በጸሎት ባርከው ከከፈቱ በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት “ዛሬ በምንመርቃቸው የልማት ሥራዎች ለቤተ ክርስቲያን እና ለመንግስት ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኙ ከመሆናቸው በተጨማሪ ከፍተኛ የሥራ ዕድል ይፈጥራሉ” ብለዋል፡፡ ብፁዕነታቸው አክለውም “ት/ቤቱ በሃይማኖት ሳይለይ የልዩ ልዩ ቤተ እምነት ተከታዮች ልጆች ተቀብሎ በሥነ ምግባር ታንጸው እንዲያድጉ በማድረግ ለሀገር የሚጠቅም ትውልድ አያፈራ ይገኛል” ብለዋል፡፡hawassa2b

 

የዕለቱ የክብር እንግዳ የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የንድግና ኢንደስትሪ ቢሮ ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙ እንደገለጹት “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ሰላምና ልማትን ከመገንባት አንጻር እያበረከተችው ያለችው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ የተገነባው ሁለ ገብ ህንጻ ለሀዋሳ ከተማ ተጨማሪ ውበት ሆኗል” ብለዋል፡፡

 

hawassa3a

የገዳሙ የልማት ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ተከስተ ብርሃን ሀጎስ በሪፖርታቸው እንደገለጹት “ይህ ከስድስት ዓመት በፊት ግንቦት 2001 ዓ.ም የመሰረት ድንጋይ ተጥሎ ዛሬ ለምረቃ የበቃው ሁለገብ ህንጻ 30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚገመት ሲሆን ከገዳሙ ካዝና ወጪ የተደረገው 8 ሚሊየን ብር ብቻ ነው፡፡ ቀረው ወጪ ግን በኮሚቴው አባላትና እና በከተማው በሚገኙ ባለ ሀብት የቤተ ክርስቲያን ልጆች የተሸፈነ እንደ ሆነ” ገልጸዋል፡፡ የኮሚቴው ሰብሳቢ ህንጻው የተሰራበትን ዓላማ ሲገልጹ “ይህን ህንጻ በማከራየት የሚገኘው ገቢ ለገጠር አብያተ ክርስቲያናት መርጃ እንዲሆን ታስቦ የተገነባ ነው” ብለዋል፡፡

 

በመጨረሻ በገዳሙ የተሠሩት የልማት ሥራዎች ሁለ ገብ ባለ 4 ፎቅ ህንጻ እና የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት በተጋዛዥ እንግዶችና ምዕመናን ተጎብኝተዋል፡፡ ከጉብኝቱ በኋላ ያናገርናቸው ምዕመናን እንደገለጹልን የገጠር አብያተ ክርስቲያናን ከመዘጋት አደጋ ለመታደግ በከተማ የሚገኙ አድባራት እንደዚህ አይነት የልማት ሥራ መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡

 

የማቴዎስ ወንጌል

የካቲት 2 ቀን 2007 ዓ.ም.

ምዕራፍ ዐሥራ አራት

በዚህ ምዕራፍ፡-
1. ስለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አሟሟት
2. ጌታችን አምስት ሺሕ ሰዎችን ስለመመገቡ
3. ጌታችን በባሕር ላይ ስለመራመዱ እንመለከታለን

1.የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አሟሟት
እሥራኤል በአራት ክፍል ተከፍላ በምትዳደርበት ዘመን የአራተኛው ክፍል ገዥ ሆኖ እስከ 39 ዓ.ም. በገሊላ የገዛው ሄሮድስ አንቲጳስ ይባል ነበር፡፡ ይህ ሰው የወንድሙን የሄሮድስ ፊልጶስን ሚስት ሄሮድያዳን በማግባቱ፣ መጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ሳይፈራና ሳያፍር ገሰጸው፡፡ ዘሌ.18፡16 በዚህም ምክንያት ዮሐንስን አሲዞ አሳሰረው፡፡ እንዳይገድለው ግን ሕዝቡን ፈራ፡፡

ሄሮድስ የልደቱ በዓል ባከበረበት ቀን የሄሮድያዳ ልጅ በዘፈኗ አስደሰተችው፡፡ ከደስታውም የተነሣ የምትለምነውን ሁሉ እንዲሰጣት ቃል ገባላት፡፡ እርስዋም በእናትዋ ተመክራ የመጥምቁን ዮሐንስን ራስ በዚህ በወጭት አድርገህ ስጠኝ አለችው፡፡ ለጊዜው በያዝንም ነገር ግን ስለ መሐላው አንድም በዙሪያው የተሰበሰቡ ሰዎች “ቃሉ ግልብጥብጥ ነው፤” ይሉኛል ብሎ ፈርቶ የጠየቀችውን ፈጸመላት፡፡ በወጭት መሆኑም ለጊዜው እስራኤል ደም ስለማጸየፉ ሲሆን፤ ለፍጻሜው ግን የከበረች የቅዱስ ዮሐንስ ራስ በዚህች በርኲሰት እጅ እንዳይያዝ እግዚአብሔር በጥበብ ያደረገው ነው፡፡

ሄሮድስን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ጠባዩ ቀበሮ ብሎታል፡፡ ሉቃ.23፡6-12 ቀበሮ የተንኮለኛና የደካማ ሰው ምሳሌ ነው፡፡ መኃ.2፡15፣ ነህ.4፡3፡፡ ጲላጦስ ኢየሱስ ክርስቶስን ይዞ በላከበት ጊዜም በንቀት ዘብቶበታል፡፡ ሉቃ.23፡6-12፡፡

2.አምስት ሺህ ሰዎችን እንደ መገበ
ጌታችን የቅዱስ ዮሐንስን ሞት ሰምቶ ወደ በረሃ ፈቀቅ አለ፡፡ ሕዝቡም ሰምቶ ተከተለው፡፡ በመሸም ጊዜ ደቀመዛሙርቱ ሕዝቡን እንዲያሰናብት ጠየቁት፡፡ ይህም ለዚያ ሁሉ ሕዝብ የሚሆን ምግብ ስለሌለ የሚበሉትን እንዲገዙ ነበር፡፡ እርሱ ግን ለጊዜው የተገኘውን አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ ባርኮ ሁሉንም እስኪጠግቡ ድረስ መገባቸው፡፡ ተርፎም አሥራ ሁለት መሶብ ተነሣ፡፡ የተመገቡትም ሕዝብ ሴቶችና ሕፃናት ሳይቆጠሩ አምስት ሺህ ወንዶች ነበሩ፡፡ ሴቶቹ ያልተቆጠሩበት ምክንያት በአደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው፤ ሕፃናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ስለሚበዛ ነው፡፡

ጌታችን ያን ሁሉ ሕዝብ በመንደር አጠገብ መመገብ ሲችል ርቆ ወደ ምድረ በዳ የወጣበት ምክንያት ነበረው፡፡ ይህም፡-

 

1ኛ “ጥንት አባቶቻችሁን ከመንደር አውጥቼ /ከግብፅ አውጥቼ/ አርባ ዘመን ሙሉ መና የመገብኋቸው እኔ ነኝ፡፡ አሁንም በሥልጣኔ፣ በተአምራቴ መገብኋችሁ፡፡” ሲላቸው ነው፡፡

 

2ኛ. ተአምራቱን ከመንደር አጠገብ አድርጐት ቢሆን ኖሮ “ፈጣን ፈጣን ደቀመዛሙርቱን በጐን ወደ መንደር እየላከ ያስመጣው ነው፤” ብለው በተጠራጠሩ ነበር፡፡ ስለሆነም ለጥርጥር ምክንያት እንዳይኖራቸው አድርጎ ተአምራቱን ገልጦላቸዋል፡፡ ከዚህም ሌላ በበረሃ ያውም በምሽት ሕዝቡን በውኃ አጠገብ በሣር ላይ አስቀምጧቸው መመገቡ “በፍጻሜው ዘመን በምቹ ሥፍራ በመንግሥተ ሰማያት መንፈሳዊ ምግብ እመግባችኋለሁ፡፡ በውኃ /በጥምቀት/ በሚገኝ ክብርም አከብራችኋለሁ፡፡” ሲላቸው ነው፡፡

 

በዚህ ታሪክ ውስጥ አምስቱ እንጀራ የአምስቱ አዕማደ ምሥጢር ምሳሌ ነው፡፡ እነኚህም፡- 

1ኛ. ምሥጢረ ሥላሴ
2ኛ. ምሥጢረ ሥጋዌ
3ኛ. ምሥጢረ ጥምቀት
4ኛ. ምሥጢረ ቁርባን
5ኛ. ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ናቸው፡፡

ሁለቱ ዓሣ ደግሞ የፍቅረ እግዚአብሔርና የፍቅረ ቢጽ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ፍቅረ እግዚአብሔር ማለት እግዚአብሔር አምላክን በፍጹም ነፍስና በፍጹም ሐሳብ መውደድ ነው፡፡ ፍቅረ ቢጽ ደግሞ ባልንጀራን እንደራስ አድርጐ መውደድ ነው ዘዳ.6፡5፣ ማቴ.22፡37 በተጨማሪም እንጀራውና ዓሣው የሥጋውና የደሙ ምሳሌ ነው፡፡

3.በባሕር ላይ እንደተራመደ
ጌታችን በተአምራት ሕዝቡን መግቦ ካሰናበተ በኋላ ይጸልይ ዘንድ ብቻውን ወደ ተራራ ወጣ፡፡ እንዲህም ማድረጉ “ተአምራት ተደረገልን ብላችሁ ጸሎታችሁን አትተዉ” ለማለት ለአብነት ነው፡፡ ከሌሊቱም በአራተኛው ክፍል ዘባነ ባሕርን /የባሕርን ጀርባ/ እየተረገጠ በማዕበል ስትጨነቅ ወደ ነበረችው ወደ ደቀመዛሙርቱ ታንኳ መጣ፡፡ ደቀመዛሙርቱ ግን ምትሃት መስሏቸው ፈርተው ጮኹ ወዲያውም “አይዟችሁ እኔ ነኝ አትፍሩ፤” አላቸው፡፡

 

ስምዖን ጴጥሮስም “አንተ ከሆንክስ እዘዘኝና ወደ አንተ ልምጣ፤” አለው፡፡ ጌታም “ባሕሩን እየተረገጥክ ና” ብሎ አዘዘው፡፡ ስምዖን ጴጥሮስ ግን መጓዝ ከጀመረ በኋላ ነፋሱን አይቶ ፈራ፡፡ ሊሰጥምም በጀመረ ጊዜ “ጌታ ሆይ አድነኝ” ብሎ ጮኸ፤ ጌታም እጁን ዘርግቶ ያዘውና “አንተ እምነት የጎደለህ ለምን ተጠራጠርህ” አለው፡፡ “ከርሱ ጋር ሳለሁ ጥፋት አያገኘኝም ፣ አትልም ነበር” ሲለው ነው፡፡ በመርከብ ያሉትም “በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነው፤” ብለው ሰገዱለት፤ ተሻግሮም በጌንሴሬጥ ብዙ ሕሙማንን ፈወሰ፡፡ ሕሙማኑም የተፈወሱት የልብሱን ጫፍ በእምነት በመዳሰሳቸው ነበር፡፡

በዚህ ታሪክ ከሌሊቱ በአራተኛው ክፍል መባሉ እሥራኤላውያንን ሰዓተ ሌሊቱን በአራት ክፍል ስለሚከፍሉት ነው፡፡ ይህም፡-
1ኛ. ከምሽቱ እስከ ሦስት ሰዓት
2ኛ ከሦስት ሰዓት እስከ ስድስት ሰዓት
3ኛ. ከስድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት
4ኛ. ከዘጠኝ ሰዓት እስከ ንጋት ነው፡፡ /በዚህ ክፍል ሌሉቱ እያለፈ ነው፣ እየነጋ ነው ይባላል፡፡/ ይህ ሰዓት ማዕበል ፈጽሞ የማይነሣበት ሰዓት ነው፡፡ ነገር ግን ተአምራቱን ለመግለጽ የፈለገ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ሰዓቱ ማዕበል እንዲነሣ አድርጓል፡፡ እንዲህ ባይሆን ኖሮ “ድሮም ማዕበል ይነሣል፣ ደግሞም ጸጥ ይላል፤ ምን አዲስ ነገር አለ” ባሉ ነበር፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በአራተኛው ሰዓተ ሌሊት ወደ ባሕር መምጣቱ በአራተኛው ክፍለ ዘመን ወደ ዓለም የመምጣቱ ምሳሌ ነው፡፡

በአራት የተከፈሉት ዘመናትም፡-
1ኛ. ዘመነ አበው
2ኛ. ዘመነ መሣፍንት
3ኛ. ዘመነ ነገሥት
4ኛ. ዘመነ ካህናት ናቸው፡፡

የነፋሱ ኃይልም የጽኑ መከራ ምሳሌ ነው፡፡ ከዚህም ሌላ ባሕር የዓለም ምሳሌ ስትሆን ታንኳይቱ ደግሞ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ናት፡፡ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን በየጊዜው የሚነሣባትን የመከራ ማዕበል ፀጥ የሚያደርግላት አምላክ አላት፡፡ ለዚህም ሳይታክቱ “እግዚኦ፣ እግዚኦ፣ እግዚኦ ማለት ያስፈልጋል፡፡

ምንጭ፡- ስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ 5ኛ ዓመት ቁጥር 3 ታኅሣሥ 1990 ዓ.ም.

 

ሱባዔና ሥርዓቱ

መጋቢት 17 ቀን 2008 ዓ.ም

መ/ር ሳሙኤል ተስፋዬ

ሱባዔ ምንድን ነው?

ሱባዔ በሰዋስው ትርጉሙ ሰባት ማለት ነው፡፡ ሱባዔ በመንፈሳዊ አተረጓጎም አንድ ሰው ከዚህ ቀን እስከዚህ ቀን በጸሎት ከፈጣሪዬ እገናኛለሁ ብሎ የሚያቅደው መንፈሳዊ ዕቅድ ነው፡፡ ሰባት ቁጥር በእስራኤላውያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ለምሳሌ፡- ፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፍጥረትን ከመፍጠር ማረፉ፣ ለጸሎት የሚተጉ ምእመናን በቀን ለሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥርን ፍጹምነት ያመለክታል፡፡ ዘፍ.2፥2፤ መዝ.118፥64፡፡ ከዚህ አንጻር አንድ ሰው ለሰባት ቀናት ቢጾም አንድ ሱባዔ ጾመ ይባላል፡፡ ለዐሥራ አራት ቀን ቢጾም ሁለት ሱባዔ ጾመ እያለ እየጨመረ ይሄዳል፡፡

መቼ ተጀመረ?

ሱባዔ የተጀመረው ከውድቀት በኋላ በመጀመሪያው ሰው በአዳም ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት መጸለይን እንዳስተማሩት የመጽሐፍ ቅዱስ ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡ መላእክት ለአዳም ጊዜያትን አስተምረውት ነበር፡፡ ቅዳሴ ማርያም ትርጓሜ፡፡ አዳም ጥፋቱን አምኖ ከባሕር ውስጥ ሱባዔ በመግባቱና በመጸለዩ እግዚአብሔር በማይታበል ቃሉ ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንኀለሁ ሲል ቃል ኪዳን ገብቶለታል /መጽሐፈ ቀሌምጦስ አንቀጽ አራት/፡፡

ሱባዔ ለምን?

የሰው ልጅ ኃጢአት በሚስማማው የሥጋ ሰውነቱ ዘወትር ፈጣሪውን ይበድላል፡፡ በፈጸመው በደል ኅሊናው ይወቅሰዋል፡፡ ይጸጸታል፡፡ በመጀመሪያ ደፍሮ በሠራው ኃጢአት በኋላ ይደነግጣል፡፡ ይህ በማንኛውም ሰብአዊ ፍጥረት ኅሊና ውስጥ የሚፈራረቅ ክስተት ነው፡፡ በዚህ ጊዜ የፈጣሪውን ይቅርታ ለማግኘት ያስባል፤ ይተክዛል፡፡ በውስጡ ሰውነቴ በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለኛል. ነገር ግን በብልቶቼ ባለ በኃጢአት ሕግ የሚማርከኝ ሌላ ሕግ አያለሁ፡፡ እኔ ምንኛ ጐስቋላ ሰው ነኝ ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል? እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ፡፡ ሮሜ.7.22-25፡፡

ሰው በደፋርነቱ የኃያሉን አምላክ ትእዛዝ ተላልፎ ትካዜ ሽክም ሲያስጨንቀው ሸክሙን የሚያቃልልበትና የሚያስወግድበት መንፈሳዊ ጥበብ ከቸሩ ፈጣሪ ተሰጥቶታል፡፡ ይኸውም በጥቂት ድካመ ሥጋ ያልተወሰነ ጸጋ እግዚአብሔር የሚያገኝበት ሥርዓት ሱባዔ ነው፡፡ ከጥንት እስከ ዛሬ አንድ ሰው በትካዜ ሽክም መንፈሱ ሲታወክ የነፍስና የሥጋ ጸጥታውን ለመመለስና ለማስከበር መጾምና መጸለይ ግድ ይሆንበታል፡፡ በዚህ ጊዜ አመክሮ /ሱባዔ/ ይገባል፡፡

እግዚአብሔርን ለመማፀን

ሰው ሱባዔ ከሚገባባቸው መሠረታዊ ጉዳዮች አንዱ እግዚአብሔርን ለመማፀን ነው፡፡ ማንኛውም ሰው ሱባዔ ሲገባ በቁርጥ ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማኅፅኖ ሊኖረው ይገባል፡፡ ምንም የምንጠይቀው /የምንማፀነው/ ነገር ሳይኖር ሱባዔ ብንገባ የምናገኘው መልስ አይኖርም፡፡ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታና ዝግጅት ሱባዔ የሚገቡ ሰዎች ከሱባዔ በኋላ ምን እንደ ተመለሰላቸው የሚያውቁት ነገር ስለማይኖር ሱባዔ በመግባታቸው የሚያገኙት ነገር የለም፡፡ 

ስለዚህ ሱባዔ ከመግባታችን በፊት፡- ሱባዔ የምገባው ለምንድን ነው? በማለት ራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ ለምሳሌ አንድ ክርስቲያን በግል ሕይወቱ ዙሪያ ስለ ሀገር ሰላም፣ ስለ ጓደኛው ጤና ወዘተ ጉዳዮች ላይ ፈጣሪውን ይማፀናል፡፡ በዚህ ጊዜ በግል ሕይወቱም ሆነ በሀገር ጉዳይ ለገባው ሱባዔ ወዲያውኑ መልስ ሊያገኝ ይችላል፤ እንዲሁም መልሱ ሊዘገይ ይችላል፡፡ በዚህ ጊዜ ከተሐራሚው ትዕግሥት /መታገሥ/ ይጠበቅበታል፤ ለምን ላቀረብኩት ጥያቄ ቶሎ መልስ አልተሰጠኝ? በማለት ማማረርና እግዚአብሔርን መፈታተን ተገቢ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ሥራውን የሚሠራበትና ለሚማፀነውም መልስ የሚሰጥበት የራሱ ጊዜ አለው፡፡ ለምሳሌ በጓደኛው ውድቀት ምክንያት ሱባዔ ገብቶ በአንድ ሳምንት ውስጥ መልስ ያገኘ የአንድ ገዳም አገልጋይ ታሪክ መመልከት ተገቢ ነው፡፡

«አኃው ለተልእኮ በወጡበት አንዱን ድቀት አግኝቶት አድሯል፡፡ በነጋው ወንድሜ እኔ ድቀት አግኝቶኛልና እንግዲህ ወዲህ ተመልሼ ከዚያ ገዳም አልሔድም፤  አለው፡፡ እኔም እንጂ አግኝቶኛል፤ ይልቁንስ ሔደን ኃጢአታችንን ለመምህረ ንስሐችን ነግረን፤ ቀኖናችንን ተቀብለን እንደ ቀደመው ኾነን እንኖራለን ብሎ አጽናንቶ ይዞት ሔደ፡፡ ሔደው ለመምህረ ንስሐቸው ነግረው ቀኖናቸውን ተቀብለው 1 /አንድ/ ሱባዔ፣ ቀኖና እንዳደረሱ ሰረይኩ ለከ በእንተ ዘኢገብረ እኁከል፤ ኃጢአት ስላላደረገው ወንድምህ ይቅር ብዬሃለሁ የሚል ድምፅ አሰምቶታል፡፡ /ዜና አበው/፡፡

ከላይ ታሪካቸው የሰፈረው የገዳም አገልጋዮች ለአገልግሎት በተላኩበት አገር አንዱ ድቀት አግኝቶት በዝሙት ሲወድቅ ጓደኛው እንደ እርሱ ድቀት እንዳገኘው አድርጐ ጓደኛውን በማጽናናት ወደ ገዳም በመመለስ አንድነት ኾነው ሱባዔ ይገባሉ፡፡ አንድ ሱባዔ /ሰባት ቀን/ እንደ ጨረሱ ከእግዚአብሔር ዘንድ ኃጢአት ሳይሠራ ለአንተ ብሎ ሱባዔ ስለገባው ወንድምህ ስል ይቅር ብዬሃለሁ የሚል ፈጣን መልስ አግኝቷል፡፡ ስለዚህ ሱባዔ በግል ሕይወትም ሆነ በጓደኛችን ሕይወት ዙሪያ ስንገባ ፈጣን ወይም የዘገየ መልስ ሊሰጠን ስለሚችል በትዕግሥት መጠባበቅ ይኖርብናል፡፡

የቅዱሳንን በረከት ለመሳተፍ

ቅዱሳን አባቶችና ቅዱሳት እናቶች የተጋደሉትን ተጋድሎ በማዘከር ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ገዳማትና አድባራት የሚገባ ሱባዔ የቅዱሳኑን በረከት ተካፋይ ያደርጋል፡፡ ቅዱሳን በሚጋደሉበት ቦታ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋ የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ /ኢሳ.56.6/ በማለት እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ስለ ገባላቸው ሱባዔ በመግባት በረከታቸውን መሳተፍ ይቻላል፡፡ በጾመ ነቢያት የነቢያትን በረከት ለመሳተፍ፣ በጾመ ሐዋርያት የሐዋርያትን በረከት ለመሳተፍ፣ በጾመ ፍልሰታ የእመቤታችንን በረከት ለመሳተፍ ሱባዔ መግባት የነበረና ወደ ፊትም የሚኖር የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ነው፡፡ ዛሬ ይህን ሥርዓት በመከተል የተለያዩ ቅዱሳንን በረከት ለመቀበል /ለመሳተፍ/ የቅዱሳን አፅም ካረፈበት ገዳም በጾም፣ በጸሎት፣ በጉልበትም ገዳማትን በማገልገል የቅዱሳንን በረከት ደጅ የሚጠኑ ምእመናንና መናንያን በየገዳማቱ እጅግ በርካታ ናቸው፡፡

ይኸውም በመጽሐፈ ነገሥት ካልዕ በምዕራፍ 2.9 እንደ ተመለከተው ነቢዩ ኤልሳዕ መምህሩን ኤልያስን በማገልገል የኤልያስ በረከት በእጥፉ በኤልሳዕ ላይ አድሮበታል፡፡ ይህን አብነት በማድረግ በየገዳማቱ በትሕርምት የሚኖር መናንያንን ያገለገሉበትን ገዳም አባት በረከት በእጥፍ እየተቀበሉ ለሌሎችም የሚያቀብሉ አባቶች በየገዳማቱ አሉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሆኖ በስመ ገዳማዊ የምእመናንን ገንዘብ የሚዘርፉና የእውነተኛ መነኮሳትንና መናንያንን የተቀደሰ ሕይወት የሚያጐድፉ መኖራቸውን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

የተሰወረ ምሥጢር እንዲገለጥልን

በዘመነ ብሉይ እግዚአብሔር ለአንዳንድ ነገሥታት ራእይ በማሳየት ምሥጢርን ይሰውርባቸው ነበር፡፡ ለምሳሌ የግብፁን ፈርዖን፣ የባቢሎኑን ናቡከደነፆርንና ብልጣሶርን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ዘፍ.41.14-36፡፡ ዳን.4.9፤ ዳን.5.4፡፡ እነዚህ ነገሥታት በግል ሕይወታቸውም ሆነ በመላው ሽክም ወደ ፊት ሊፈጸም የሚችል ራእይ ቢያዩም ቅሉ ራእዩን በትክክል ተረድተው እንዲህ ይሆናል የማለት ብቃት አልነበራቸውም፡፡ ስለዚህ በዘመናቸው ይኖር የነበሩትን ነቢያት ሱባዔ ገብተው የሕልማቸውን ትርጉም እንዲነግሩአቸው ይማፀኑ ነበር፡፡ ነቢያትም ሱባዔ በመግባት ነገሥታቱ ያዩትን የምሥጢረ ሥጋዌ ነገርና የመንግሥታቸውን አወዳዳቅ ገልጸው ይናገሩ ነበር፡፡ ዳን.5.28፡፡

እንዲሁም ቅዱሳን በየራሳቸው ያዩት ራእይ ምሥጢር ሲከደንባቸው የራእዩ ምሥጢርና ትርጉም እንዲገለጥላቸው ሱባዔ ይገባሉ፡፡ እግዚአብሔርም በንጽሕና ሆነው የገቡትን ሱባዔ ተመልክቶ ምሥጢር ይገልጥላቸዋል፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ዕዝራ የመጻሕፍትን ምሥጢር እንዲገልጥለት ሱባዔ ቢገባ የጠፉትን የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ዳግም መልሶ ለመጻፍ ችሏል፡፡ መዝ.8.1፡፡

በዘመነ ሐዲስ በሰፊው የሚወሳው ቅዱሳን ሐዋርያት ከነሐሴ 1-14 የገቡት ሱባዔ ነው፡፡ ይህ ሱባዔ ተሰውሮ የነበረውን የቅድስት ድንግል ማርያምን ትንሣኤ ተረድተው በረከቷን ለመሳተፍ አብቅቷቸዋል፡፡

እመቤታችን ያረፈችው ጥር 21 ቀን 50 ዓመተ ምሕረት ነው፡፡ ሐዋርያት ሊቀብሯት ወደ ጌቴ ሰማኔ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ በታተኗቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት የእመቤታችንን ሥጋዋን ወስደው በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር አኑረውታል፡፡/ተኣምረ ማርያም፤ ስንክሳር ነሐሴ 16 ቀን/፡፡ በዚህ ጊዜ እነርሱ ተደናግጠው ስለተበታተኑ የእመቤታችን የዕረፍቷ ያስጨንቃቸው ነበር፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ በተመስጦ እየሄደ ሥጋዋን ያጥን ነበር፡፡ ለሐዋርያት ይህን ይነግራቸዋል፡፡ ለዮሐንስ ተገልጣ ለእኛ ሳትገለጥ ብለው በነሐሴ ሱባዔ ገቡ፡፡ ሁለተኛው ሱባዔ ሲፈጸም በ14ኛው ቀን መልአክ ሥጋዋን አምጥቶ ሰጥቶአቸዋል፤ ቀብረዋታል፡፡ በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16 ቀን ተነሥታ ዐርጋለች፡፡ /ተኣምረ ማርያም፤ ስንክሳር ነሐሴ 16 ቀን/፡፡

እንግዲህ ለቅዱሳን ሐዋርያት የእመቤታችን የዕረፍትና የዕርገት ምሥጢር የተገለጠላቸው በሱባዔ ነው፡፡ ይህን መሠረት በማድረግ ሐዋርያዊት ቤተ ክርስቲያን የእመቤታችንን የዕርገቷን በረከት ለማግኘት ትጾማለች፡፡ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ይህን የሱባዔ ወቅት ሕፃናትም ሳይቀሩ ይሳተፉታል፡፡

ሱባዔ ነቢያት

እግዚአብሔር ለአዳም የገባውን ቃል ኪዳን መሠረት በማድረግ ቀደምት ነቢያት በተነሡበት ዘመን ቅደም ተከተል ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆንና ዳግም መምጣት ትንቢት ተናግረዋል፡፡ ሱባዔም ቆጥረዋል፡፡ ኢሳ.7.14፡፡ መዝ.49.3፡፡ ዘካ.13.6፤ ዘካ.14.1፡፡ የአንዱ ነቢይ ትንቢታዊ ንግግርና ሱባኤ በአነጋገርና በአቆጣጠር ከሌላኛው ነቢይ ጋር ይለያያል፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር ትንቢቱን ሲያናግር ምሳሌውን ሲያስመስል ጐዳናው ለየቅል በመሆኑ ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ እግዚአብሔር በብዙ ዓይነትና በብዙ ጐዳና ለአባቶቻችን በነቢያት ተናገረ፡፡ እንዲል፡፡ ዕብ.1.1፡፡ የአቆጣጠር ስልታ ቸውና የሱባዔ መንገዳቸው ቢለያይም ዓላማና ግባቸው ግን አንድ ነው፡፡

ሱባዔ አዳም

አዳም ትንቢት በመናገርና ሱባዔ በመቁጠር የመጀመሪያውን ሥፍራ ይይዛል፡፡ ምክንያቱም በገነት ሰባት ዓመት ከአንድ ወር ከዐሥራ ሰባት ቀን በተድላና በደስታ ከኖረ በኋላ ሕግ በማፍረሱና የፈጣሪውን ቃል በመጣሱ ያለምንም ትካዜና ጉስቁልና ከሚኖርበት ዔደን ገነት ተባርሯል፡፡ ዘፍ.3.24፡፡ እርሱም ፈጣሪው እንዲታረቀው፣ በዐይነ ምሕረት እንዲጐበኘው፣ ቅዝቃዜው ሰውነት ከሚቆራርጥ ባሕር ውስጥ በመቆም ለሠላሳ አምስት ቀን /አምስት ሱባዔ/ ሱባዔ ገብቷል፡፡ በባሕርዩ የሰውን ልጅ እንግልት የማይወድ ቸሩ ፈጣሪ የአዳምን ፈጽሞ መጸጸት ተመልክቶ በኀሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ ወእድኅክ ውስተ መርህብከ ወእቤዝወከ በመስቀልየ ወበሞትየኸ በአምስት ቀን ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ ብሎ ተስፋውን ሰጠው፡፡ አዳም የተሰጠውን ተስፋ ይዞ በዓለመ ሥጋ ለዘጠኝ መቶ ሠላሳ አመት ከኖረ በኋላ መከራና ችግር ከበዛበት ዓለም በሞት ተለይቷል፡ 

በወንጀል ተከሶ በወኅኒ የተፈረደበት ሰው ከእስር የሚፈታበትን ዕለት በማውጣት በማውረድ ወራቱንና ዓመታቱን እንደሚቆጥር፣ አዳምም በሞት ቢለይም በሲኦል የነፍስ ቅጣት ካለበት ሥፍራ ይኖር ስለነበር የተሰጠውን ተስፋ በማሰብ ሱባዔውን እየቆጠረ የተናገረውን የማያስቀር የማያደርገውን የማይናገር ጌታየ እነሆ አድንኀለሁ ብሎ የገባልኝ ዘመን ተፈጸመ፤ ሰዓቱ አሁን ነው፤ እያለ ሲያወጣ ሲያወርድ ቸር አምላክ ሰው ኾኖ ሥጋ ለብሶ በአካለ ነፍስ ወደ ሲኦል ወርዶ፡- ተንሥኡ ለጸሎት ለጸሎት ተነሡ፤ ሰላም ለኩልክሙ፤ ሰላም ለእናንተ ይሁን በማለት አዳምን ከነልጅ ልጆቹ ነጻ አውጥቶታል፡፡ አዳምን በመከተል ልጆቹም አበው ቅዱሳን ነቢያት ሱባዔ በመግባት የተስፋን ዘመን በመቁጠር በመልካም ግብር ተከትለውታል፡፡ በዚህም መሠረት በርካታ ነቢያት በተለያየ ስልት ሱባዔ ቆጥረዋል፤ እኛም ሱባዔ ከቆጠሩ ነቢያት የተወሰኑትን በዚህ ጽሑፍ እንደሚከተለው እናቀርባለን፡፡

ሱባዔ ሔኖክ

ጻድቁ ሔኖክ፣ የያሬድ ልጅ ሲሆን፣ በትውልድ ከአዳም ሰባተኛ ነው፡፡ እርሱም በሕይወቱ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት ቤት ንብረቱን በመተው በሱባዔና በትሕርምት እግዚአብሔርን አገልግሏል፡፡ ፍጹም አካሔዱን ከእግዚአብሔር ጋር ያደረገ ሰው በመሆኑ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በሐዲስ ኪዳን መልካም ግብር ተመስክ ሮለታል፡፡ ሔኖክም አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረገ፡፡ ዘፍ.5.22፡፡ ይህም በመሆኑ እግዚአብሔር የሱባዔውን ዋጋ ቅዱስ መንፈሱን በረድኤት ስለ አሳደረበት ትንቢት ተናግሯል፤ ሱባዔ ቆጥሯል፡፡ በሰማይ ተሰውሮ ሳለ ስለ ቅዱሳን መላእክት፣ ስለ መሲሕ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ፀሐይና ጨረቃ አመላለስ /ዑደት/ የሚተርክ በስሙ የተሰየመውን መጽሐፍ ጽፏል፡፡ ዘፍ.5 21-24፡፡ ይሁዳ ቁ.14፡፡ ሔኖክ 1.9፡፡

ሱባዔ ሔኖክ የሚባለው ነቢዩ ሔኖክ በመስፈርት የቆጠረው ሱባዔ ነው፡፡ መስፈርቱ /ማባዣ ቁጥር/ 35 ሲሆን 35’19 ሲበዛ በውጤቱ 685 ዓመት ይሆናል፡፡ 685’12 ስናባዛው 7980 ይሆናል፡፡ ይኸውም ሐሳብ የሚያስረዳው ስለክርስቶስ ምጽአት ነው፡፡

ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አሁን የደረስንበት ዘመን 7497 ይሆናል፡፡ ይህን ለማረጋገጥ በ5500 ዓመት ላይ 1997 ዓመትን መደመር ነው፡፡ በዚህን ጊዜ ከላይ ያስቀመጥነውን 7497 ዓመት ይሰጠናል፡፡ በነቢዩ ሔኖክ አቆጣጠር መሠረት ምጽአተ ክርስቶስ በ7980 ይሆናል፡፡ ከላይ ሔኖክ የቀመረውን ቁጥር ይዘን ከ7980 ዓመት ላይ አሁን ያለንበትን ዘመን /1997/ ስንቀንስ 483 ዓመት እናገኛለን፡፡ ስለዚህ በሔኖክ ሱባዔ መሠረት ምጽአተ ክርስቶስ ሊሆን 483 ዓመት ይቀራል፡፡ 

ሱባዔ ዳዊት

ነቢዩ ዳዊት ከእስራኤል ነገሥታት ሁሉ ታላቅና ተወዳጅ ንጉሥ ነበር፡፡ ዘመነ መንግሥቱ 1011-971 ከክርስቶስ ልደት በፊት እንደ ነበር ይታመናል፡፡ ነቢዩ ዳዊት ልበ አምላክ እንደ መሆኑ ትንቢት ተናግሯል፡፡ ሱባዔ ቆጥሯል፡፡ ይኽውም ቀመረ ዳዊት በመባል ይታወቃል፡፡ እስመ ዐሠርቱ ምእት ዓመት በቅድሜከ፤ ከመ ዕለት እንተ ትማልም ኃለፈት፤ ሺ ዓመት በፊትህ እንዳለፈች እንደ ትላንት ቀን፡፡ /መዝ.89.4/ የሚለውን መምህራን ሲቆጥሩት 1140 ዓመት ይሆናል፡፡ ይኸውም በጌታ ዘንድ 1140 ዓመት እንደ አንድ ቀን እንደሆነ ነቢዩ ዳዊት ተናግሯል፡፡ ይህም ለዳዊት ሱባዔ መቁጠሪያ /መሥፈሪያ/ ሆኖ አገልግሏል፤ 1140*7= 7980 ዓመት ይሆናል፡፡ ይህም ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ በ7980 ዓመት ክርስቶስ ዳግም እንደ ሚመጣ የሚያመለክት ነው፡፡ 

ሱባዔ ዳንኤል

ነቢዩ ዳንኤል ምድቡ ከዐበይት ነቢያት ነው፡፡ እስራኤል ወደ ባቢሎን ሲማረኩ ተማርኮ ወደ ባቢሎን ወርዷል፡፡ እርሱም ስለ ክርስቶስ መምጣት ትንቢት ተናግሯል፤ ሱባዔም ቆጥሯል፡፡ ሰብአ ሰንበታተ አድሞሙ ለሕዝብከ፤ ሰባ ሰንበት ወገኖችህን ቅጠራቸው፡፡ ይኸውም ክርስቶስ ከ490 ዓመት በኋላ ሰው መሆኑን የሚያመለክት ትንቢት ነው፡፡ እንዲሁም እስከ ክርስቶስ ንጉሥ ትትሐነፅ መቅደስ ወእምዝ ትትመዘበር፤ እስከ ንጉሥ ክርስቶስ ድረስ መቅደስ ትታነፃለች በኋላም ትፈርሳለች ሲል ተናግሯል፡፡ 

የአቆጣጠር ስልቱም በዓመት ሲሆን ይኸውም ሰባቱን ዓመት አንድ እያሉ መቁጠር ነው፡፡ ይኽውም ሱባዔ ሰንበት ይባላል፡፡ ዳንኤል ሱባዔ ከቆጠረበትና ትንቢት ከተናገረበት ጀምሮ ክርስቶስ እስከ ሚወለድ 490 ይሆናል፡፡ መስፈርቱ /ማባዣው/ ሰባት ስለሆነ 7*70 ስናባዛው 490 እናገኛለን፡፡ ይኸውም ነቢዩ ሱባዔ ከቆጠረና ትንቢት ከተናገረ ከ490 ዓመት በኋላ የክርስቶስን መወለድ ያመለክታል፡፡

በአጠቃላይ ከላይ የተመለከትናቸው ቅዱሳን ነቢያት አካሄዳቸውን ከእግዚአብሔር ጋር በማድረግ ሱባዔ ገብተው በትሕርምት በመኖራቸው ድንቅ የሆነውን የክርስቶስን ልደትና ዳግም ምጽአት ለመተንበይ ችለዋል፡፡ ሱባዔ መግባት የራቀን ለማቅረብ የረቀቀን ለማጉላት ብቃትን ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያስገኝ መንፈሳዊ ጥበብ መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡

የሱባዔ ዓይነቶች

የግል ሱባዔ/ዝግ ሱባዔ/

የግል ሱባዔ አንድ ሰው ብቻውን ሆኖ በቤትና በአመቺ ቦታ የሚይዘው ማንም ሰው ሳያየው በግሉ የጸሎት በኣቱን ዘግቶ በሰቂለ ኅሊና ሆኖ ፈጣሪው ብቻ እንዲያየው እንዲሰማው በኅቡዕ የሚፈጽመው ሱባዔ ነው፡፡ ማቴ.6፡5-13፡፡ በዚህ ዓይነት መልክ አንድ ሰው ሱባዔ ሲገባ ዘጋ ይባላል፡፡ ዝግ ሱባዔ የያዘ ሰው የሚያስፈልገውን ነገር ይዞ ወደ በኣቱ ከተከተተ በኋላ ሱባዔው እስኪፈጸም ድረስ ከሰው አይገናኝም፡፡ መዝ. 101-6-7፡፡

የማኅበር ሱባዔ

የማኅበር ሱባዔ የሚባለው ካህናት፣ ምእመናን ወንዶችና ሴቶች፣ ሽማግሌዎችና ወጣቶች በአንድ ሆነው በቤተ ክርስቲያንና አመቺ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ ተሰብስበው የሚገቡት ሱባዔ ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን የነበሩ ምእመናን ወደ እግዚአብሔር በመሄድ ይጸልዩ ነበር፡፡ 1ኛ ሳሙ.1፡9፤ መዝ.121፡1፤ ሉቃ.18፡10-14፡፡

በሐዲስ ኪዳንም የሐዋርያት ተከታዮች የኾኑ መነኮሳት፣ ካህናትና ምእመናን በገዳማት፣ በአድባራት፣ የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች፣ የጽዋ ማኅበርተኞች ስለ ማኅበራቸው ጥንካሬና ከማኅበርተኞቹ መካከል አንዱ ችግር ሲገጥመው የማኅበር ሱባኤ ይያዛል፡፡.

የዐዋጅ ሱባዔ

የዐዋጅ ሱባዔ በአገር ላይ ድንገተኛ አደጋ፣ አባር ቸነፈርና ጦርነት ሲነደ እንዲሁም ለማኅበረ ምእመናን አስጊ የሆነ መቅሰፍት ሲከሰት፣ እግዚአብሔር መሽቱን በምሕረት ቁጣውን በትዕግሥት እንዲመልስ የሚያዝ የሱባዔ ዓይነት ነው፡፡ ለዚህ ዓይነቱ ሱባዔ የነነዌ ሰዎችና በፋርስ በስደት ይኖር የነበረ እስራኤላውያን ተጠቃሾች ናቸው፡፡ የነነዌ ሰዎች የዮናስን ስብከት ሰምተው ከሊቅ እስከ ደቂቅ ለሦስት ቀን ከመብል ከመጠጥ ተከልክለው በመጾም በመጸለይ እግዚአብሔር መዓቱን በምሕረት ቁጣውን በትዕግሥት እንዲመልስ አድርገዋል፡፡ ሌላው በፋርስ በስደት ይኖር የነበረ አይሁድ በአስቴር ትእዛዝ የያዙት ሱባዔ ተጠቃሽ ነው፡፡ በዚያን ዘመን አርጤክስስ አይሁድ በያሉበት እንዲገደሉ በማዘዙ ከዚህ የጅምላ ጭፍጨፋ ለመዳን አይሁድ በዐዋጅ ሱባዔ ገብተዋል፡፡ አስቴር ገብታ ንጉሡን ስታናግረው ሌላው ሕዝብ በውጭ ዐዋጅ ዐውጀው ሱባዔ ገብተው ፈጣሪያቸውን ተማፅነዋል፡፡ አስቴር 4፡16 – 28፡፡

በአገራችንም ይህን የመሰለ የዐዋጅ ሱባዔ በዐፄ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት ተደርጓል፡፡ ፋሽስት ጣልያን አገራችንን በመውረር ኢትዮጵያን ቅኝ ተገዥ ለማድረግ ድንበሯን አልፎ በመጣበት ወቅት ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ፡-ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ ርዳኝ በማለት የዐዋጅ ሱባዔ መያዛቸው ይነገራል፡፡ በዚህም መሠረት በየገዳማቱ ምሕላ ተይዟል፤ ንጉሡም ታቦተ ጊዮርጊስን ይዘው ዓለምን እጅግ ያስደነቀ ጥቁሮችን ለነጻነታቸው እንዲነሣሱ የሚያስችል ፋና ወጊ የሆነ ድል አግኝተው አገራችንን ለቅኝ ግዛት ያሰበውን ፋሽስት ጣልያንን ማሸነፋቸው በከፍተኛ ስሜት የምናስታውሰው ነው፡፡

ቅድመ ዝግጅት

ሱባዔ መግባት የሚፈልግ ምእመን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይኖርበታል፡፡ ያለምንም ዝግጅት ሱባዔ መግባት ለፈተና ያጋልጣል፡፡ ስለዚህ ቅድመ ሱባዔ /ሱባዔ ከመግባት አስቀድሞ/፣ ጊዜ ሱባዔ/ በሱባዔ ጊዜና ድኅረ ሱባዔ /ከሱባዔ በኋላ/ ዝግጅት አስፈላጊ ነው፡፡

ቅድመ ሱባዔ /ሱባዔ ከመግባት አስቀድሞ/

በመጀመሪያ ሱባዔ የምንገባበትን ምክንያት ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ አንድ ሰው ሱባዔ የሚገባበትን ዓላማ ለይቶ ካስቀመጠ ከሱባዔ በኋላ የሚጠበቀውን ነገር ማግኘት አለማግኘቱን ይረዳል፡፡ ይህ ሳይሆን ሱባኤ ቢገባ ከሱባኤው በኋላ የጠየቀው ነገር ስለሌለ ትርጉም ያጣል፡፡ ስለዚህ ሱባዔ ከመግባታችን በፊት ለምን ሱባኤ ለመግባት እንዳሰብን ለይተን ማወቅ ይኖርብናል፡፡

ሱባዔ ለመግባት የወሰንበትን ምክንያት ከለየን በኋላ ምክንያታችንን ይዘን የንስሐ አባታችንን ማማከር ያስፈልጋል፡፡ ምክንያቱም በምክረ ካህን መጓዝ መጀመር ክርስቲያናዊ ግዴታ ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር በአባትነታቸውና በሕይወት ልምዳቸው ምን ማድረግ እንደሚገባን ምክር ለማግኘት እገዛ ያደርግልናል፡፡ ቅድመ ሱባኤ ከንስሐ አባት ጋር መመካከር ተገቢ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው በሱባዔ ወቅት የተለያዩ ፈተናዎች ቢያጋጥሙት የተሰጠውን ምክር በመጠቀም ፈተናውን ለመቋቋም ይችላል፡፡ እንዲሁም የንስሐ አባቱ በሱባዔ ወቅት በጸሎት እንዲያስቡት መማከር የራሱ የሆነ ድርሻ አለው፡፡

ሱባዔ ለመግባት ስናስብ ለምን ያህል ቀናት መቆየት እንዳለብን መወሰን ያስፈልጋል፡፡ ሱባዔ ከዚህ እስከዚህ እቆያለሁ ብለን ዕቅድ የምንይዝበት ነው፡፡ እንደ አቅማችንና እንደ ችሎታችን ከዚህ ቀን እስከዚህ ብለን በመወሰን ሱባዔ መግባት ተገቢ ይሆናል፡፡ ለምሳሌ፡- ምንም ዓይነት ልምድ ሳይኖረው አንድ ሰው በዋሻ እዘጋለሁ ቢል ከጥቅሙ ጉዳቱ ሊያመዝን ይችላል፡፡ ምክንያቱም በሱባዔ ወቅት ፈተና ስለሚበዛ የሚመጣበትን ፈተና መቋቋም ባለመቻል ሱባዔው ሊቋረጥ ይችላል፡፡ ስለዚህ ቅድመ ሱባዔ ዐቅምንና ችሎታን አገናዝቦ መወሰን ተገቢ ነው፡፡

ሌላው ቅድመ ሱባዔ ለሱባዔ ተስማሚ የሆነ ወቅትና ቦታ መምረጥ ተገቢ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን በአብዛኛው ሱባዔ የሚገባው አጽዋማትን ተከትሎ ነው፡፡ ስለዚህ ሱባዔ የምንገባበት ወቅት የጾም ወቅት መሆን አለመሆኑን መለየት ያስፈልጋል፡፡ በአጽዋማት ወቅት የሚያዝ ሱባዔ ለተሐራሚ ጠቀሜታው እጅግ የጐላ ነው፡፡ ምክንያቱም በአጽዋማት ወቅት ብዙ አባቶች ሱባዔ ስለሚይዙ ከአባቶች ጸሎት ጋር ልመናችንና ጸሎታችን ሊያርግ ይችላል፡፡ ስለዚህ ወቅትን ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል፡፡

እዚህ ላይ ከወርኃ አጽዋማት ውጭ ሱባዔ አይያዝም የሚል አቋም ለመያዝ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ፈተና ከአጋጠመው በማንኛውም ጊዜ ሱባዔ ሊገባ እንደሚችል እዚህ ላይ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡ ከዚህም ባሻገር ሱባዔ የምንይዝበትን ቦታ መምረጥ አለብን፡፡ ለሱባዔ የምንመርጣቸው ቦታዎች ለፈተና የሚያጋልጡ መሆናቸውን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡ ይኸውም ሱባዔ ከተገባ በኋላ ኅሊናችን እንዳይበተን እገዛ ያደርግ ልናል፡፡ ጫጫታና ግርግር የሚበዛበት ቦታ በሰቂለ ኅሊና ለመጸለይ አያመችም፡፡ ስለዚህ ሱባዔ የምንይዝባቸው ቦታዎች ከከተማ ራቅ ያሉ ገዳማትና አድባራት ተመራጭ ናቸው፡፡

ጊዜ ሱባዔ /በሱባዔ ጊዜ/

በጸሎት ሰዓት ዓምድና ግድግዳ ሳይደገፉ መቋሚያ ሳይዙ በሁለት እግር ቀጥ ብሎ በመቆም መጸለይ ይኖርብናል፡፡ እንዲሁም ፊትን ወደ ምሥራቅ መልሶ መቆም ወዲያና ወዲህ ወደ ግራ ወደ ቀኝ አለመዟዟር በሰፊሐ እድ በሰቂለ ኅሊና ኾኖ መጸለይ ይገባል፡፡ መዝ.5፡3፤ መዝ.133፡2፤ ዮሐ.11፡41፡፡

በሱባዔ ወቅት በቅደም ተከተል መጸለይ አለብን፡፡ መጀመሪያ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አአትብ ገጽየ ወኩለንታየ በትእምርተ መስቀልኸ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አንዱ አምላክ መላ ሰውነቴን በትእምርተ መስቀል አማትባለሁ እያለ ሰጊድን ከሚያነሣው ሲደርስ መስገድ መስቀልን ከሚያነሣ ላይ ስንደርስ ማማተብ ይገባል፡፡

በማስከተል አቡነ ዘበሰማያት፣ መዝሙረ ዳዊት፣ ውዳሴ ማርያምና ሌሎች በመዝገበ ጸሎት የተካተቱትን መጸለይ፤ ቀጥሎ አቡነ ዘበሰማያት፣ ጸሎተ እግዝእትነ ማርያምን፣ ጸሎተ ሃይማኖትን ከጸለይን በኋላ አቡነ ዘበሰማያት መድገም፤ ከዚያ 41 ጊዜ ኪርያላይሶን ይባላል፡፡ ሌላው በሱባዔ ጊዜ ከተሐራሚ የሚጠበቀው ነገር ኃጢአቱን እያሰበ ማዘን ማልቀስ ነው፡፡ ሲያለቅስም ለእያንዳንዱ በደል እንባ ማፍሰስ ያስፈልጋል፡፡

በመጨረሻም ሱባዔ የገባ ሰው ሱባዔውን ሳይጨርስ ወይም ሱባዔውን አቋርጦ ከማንም ሰው ጋር ፈጽሞ መገናኘት የለበትም፡፡

ድኅረ ሱባዔ /ከሱባዔ በኋላ/

ለቀረበ ተማኅፅኖ እግዚአብሔር የሚያደርግልንን ነገር መጠበቅ ይኖርብናል፡፡ እግዚአብሔር ላቀረብንለት ምልጃና ጸሎት እንደ ልባችን መሻት እንደ እርሱ ቸርነት እርሱ በወደደ ጊዜ ያደርግልናል፡፡ ሱባዔ የገባ ሰው ሁሉ ራእይ ላያይ ይችላል፡፡ ምክንያቱም የእግዚአብሔር መልስ አሰጣጥ ለማንም ግልጽ አይደለም፡፡ ከሱባዔ በኋላ መጀመሪያ የምናገኘው የኅሊና ሰላምን ነው፡፡ ይህ ትልቅ የአምላክ ስጦታ ነው፡፡ ከዚህ ባሻገር ሱባዔ ገብተን ያሰብነውን ካላገኘን ዳግመኛ ተዘጋጅተን እስከ መጨረሻው ሰዓት መማፀን መጽናት ይኖርብናል፡፡