timket 2007

የከተራ በዓል ቅድመ ዝግጅት

ጥር 11 ቀን 2007 ዓ.ም. 

 

በእንዳለ ደምስስ

timket 2007የከተራ በዓልን በማስመልከት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ዓውደ ምሕረትና ግቢ፤ ታቦታት በሚያልፉባቸው ጎዳናዎችና አደባባዮች ማኅበራትና ወጣቶች ተሰባስበው የተለያዩ ኅብረ ቀለማትን በመጠቀም በማስዋብ ላይ ይገኛሉ፡፡

በተዘዋወርንባቸው ቦታዎች ሁሉ ወጣቶቹ በጥድፊያ ላይ ናቸው፡፡

 

በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ግቢውን በማስዋብ ላይ ከሚገኙት ወጣቶች አንዱ ስለ አገልግሎታቸው ላቀረብንለት ጥያቄ ሲመልስ “የጥምቀት ክብረ በዓል ለእኛ ለኢትዮጵያውያን የእምነታችን መገለጫ ከሆኑት ዓበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡ በረከት እንድናገኝ፤ ታቦታት በሰላም ከመንበራቸው ወጥተው በሰላም እንዲመለሱ ዓውደ ምሕረት፤ ጎዳናዎችና አደባባዮችን ምንጣፍ በማንጠፍ፤ ምእመናንን በማስተናገድ በዓሉን በድምቀት እንድናከብር በየዓመቱ ተሰባስበን እናገለግላለን” ብሏል፡፡

 

በተዘዋወርንባቸው ቦታዎች የያዝናቸውን ፎቶ ግራፎች እነሆ፡-

timket 07 -03timket 07 -06timket 07- 04

timket 07 -02timket 07- 07