ግእዝ ከእስያ ልሳናት ጋር ሲነጻጸር

በዓለም የሥነ ልሳን ጥናት መሠረት የአካድ /የአሦር – አካዳውያን/ ቋንቋ ጥንታዊ ማንነቱ የተረጋገጠው በአንዳንድ የሥነ ጽሑፎች ቅሪት ሲሆን ይህ ቋንቋ በሥነ ልሳን ተማራማሪዎች ዘንድ የምሥራቅ ሴማዊ ልሳን ተብሎ በቅርብ ጊዜ ከተገኘው ከኤብላዊ ቋንቋ ጋር የሚመደብ ነው፡፡ አካድ እና አሦር በመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በኦሪት ዘፍጥረት የተገለጹ እና ከኖኅ ዘመን በኋላ የታወቁ መካናተ ሥልጣኔ ናቸው፡፡ በሥነ ጽሑፍ መረጃ የአከድ ልሳን 2500 ቅ.ል.ክ. እንደነበረ ይናገራል፡፡ በኋላ በአራም የአራማውያን የተባለው ቋንቋው ራሱን የገለጸበት ጊዜ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በሥነ ቅሬተ ምድርም ሆነ በሥነ ልሳን ተመራማሪዎች ዘንድ አካድ የኢኮኖሚ፣ የሕግ የአስተዳደር፣ የታሪክና የሥነ ጽሑፍ መረጃዎች እንደነበረው የተረዳ ነው፡፡


    
የካምም ልጆች ኩሽ፣ ምጽ/ስ/ ራይም፣ ፋጥ፣ ከነዓን ናቸው፡፡ የኩሽም ልጆች ሳባ፣ ኤውላጥ፣ ሰብታ፣ ሬጌም፣ ሰበቅታ ናቸው፡፡ የሬጌም ልጆችም ሳባ፣ ድዳን ናቸው፡፡ ኩሽም ናምሩድን ወለደ፣ እርሱም በምድር ላይ ኃያል መሆን ጀመረ እርሱም በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ ነበረ፤ ስለዚህም በእግዚአብሔር ፊት ኃያል አዳኝ እንደናምሩድ ተባለ፡፡ የግዛቱም መጀመሪያ በሰናኦር አገር በባቢሎን አሬክን አርካድ ሌድን ናቸው፡፡ አሦርም ከዚያች አገር ወጣ፡፡ ነነዌን የረሆቦት የተባለችውን ከተማ ካለህን በነነዌና በካለህ መካከልም ሬሴንን ሠራ፡፡ እርስዋም ታላቂቱ ከተማ ናት ምጽራይምም ሉዲምን ኢኒሜቲምን ላህቢምን ነፍታሌምን ጳጥሮሰኒምን ከእነርሱ የፍልስጥኤም ሰዎች የወጡባቸውን ከሳሎሂምን ቀፍቶሪምንም ወለደ፡፡ ዘፍ. 10፡6-14

 

አፍሪካዊያንም በየዘመናቱ የሥልጣኔ ማእከሉን በወንዞች ጤግሮሰ እና ኤፍራጥስ ዳር እንደ መሠረቱ ፤ አካዳውያን ፈለገ ግዮንን የራሱን ለአፍሪካውያን ሕዝቦች የሥልጣኔ መሠረት አድርጎ መቆየቱ የሚታወስ ታሪክ ነው፡፡ አፍሪካውያን በራሳቸው ፊደል ቢጠቀሙም በተለያዩ የዓለም ዐቀፍ ተጽዕኖዎች ሥር በመውደቃቸው መሠረታዊውን ፊደል ጽሕፈታቸውንና ቋንቋቸውን ሊያጡ ችለዋል፡፡ ይህንን ፊደል ጠብቃ የተገኘችው ኢትዮጵያ ናት፡፡ የኢትዮጵያ ፊደልና ቋንቋም በሥነ ጽሑፍ መረጃነት ለዓለም ከቀረቡት ልሳናት የሚታወቅባቸው ባሕርያት ሲኖሩት ከጠፋው ከአካድ ቋንቋ ይብልጥ በሥነ ጽሑፍ መረጃነቱ ራሱን ያሳደገ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ይህንም በቋንቋው ጠባያት ከአካድ ጋር ቢመሳሰል በራሱ ደግሞ ከአፍሮ እስያ ከቋንቋ መለየት ይህ ሴማዊና ካማዊ ብሎ ለመጠቅለል የሚያስቸግር ቢሆንም በቋንቋ ጥናት ዋና የመለያ ፍጥረት በማጥናት መመደብ የሚቻል ይሆናል፡፡ ከዚህ አንጻር ግእዝን ሴማዊ፣ ደቡብ ሴማዊ፣ ሰሜን ሴማዊ /በኢትዮጵያ/ አድርገው የሚከፋፍሉበት፡-

 

– ልዩ ልዩ አስማተ መካናት መመሳሰል ምሳሌ- ሳባ
– የቋንቋዎቹ የራሳቸው መመሳሰል
– የሥነ ቅርጽ መመሳሰል ወዘተ ሲሆን ግእዝ ከነዚህ ቋንቋዎች መደብ የሚለዩት ጠባያት አልነበሩትም፡፡ ወይም ደግሞ በእነዚህ ቋንቋዎች የተዘነጉ ጽሑፎች በግዕዝ ግን አልነበሩም ማለት አይቻልም፡፡ ለአብነትም ያህል «ተስዐቱ» የሚለው የጥንት ሥርው ምን ይመስላል የሚለው ሲጠና ከአረማይክ ይልቅ የግእዝ «ታስዕ» የሚለው ቃል ቀዳሚነት ጥንታዊነት ይኖረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት አረማይክ ያጣውን ግእዙ በመጠበቅ እንዴት አረማይኩ ለግእዝ በዘመኑ ያጣን ቃል ሊያቀብለው ቻለ የሚል ጥያቄ አስነሥቷል፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ግእዝ በድምጸ ንባቡ የለሌሎች የአፍሪካ ልሳናት እና የሩቅ ምሥራቅ ልሳናት የሚታወቁበትን የድምፀት ንበት በመያዝ ከአፍሪካ ልሳናት ጋር ሊያመሳስለው ይችላል፡፡


 
ምሳሌ፡

                ቀዳማይ     –     ካልአይ

አካድያን  –     ያቅቱል       –     ያቀትል
ዐረበኛ    –     ቀተለ         –     ያቀቱል
ግእዝ     –     ቀተለ         –     ይቀትል
   

ማስታወሻ- አካድያን ያቅትል ሲል በ «ይ»እና በ «ቅ» መካከል አናባቢ«አ»ኔ ሲጨምር ግእዙ ግን አይጨምርም፡፡ በተጨማሪም በግእዝ ቋንቋ በቀዳማይ አንቀጽ ዝርዝር ጊዜ የአገናዛቢ ቅጥያዎችን የምንጨምር ሲሆን አካድያን ግን የሰማዊነት ባሕርይን የሚያሳይ ነው፡፡

 
ቀዳማይ፡-
ግእዝ – አካድያን
አነ – ቀተልኩ – አቅቱል
አንተ – ቀተልከ – ተቅቱል
አንቲ – ቀተልኪ – ተቀቱሊ
አንትሙ – ቀተልክሙ – ተቅቱላ
አንትን – ቀተልክን – ተቅቱላ
ንሕነ – ቀተልነ – ኒቀቱላ
ውእቱ – ቀተለ – ተቅቱል
ይእቲ – ቀተለት – ኢቅቱል
ውእቶሙ – ቀተሉ – ኢቅቱሉ
ውእቶን – ቀተላ – ኢቅቱላ
ለካልአይ – ግእዝ – አካድያን
አነ – እቀትል – አቀትል
አንተ – ትቀትል – ተቀተል
አንትሙ – ትቀትሉ – ተቀተላ
አንትን ትቀትላ – ተቀተላ
ንሕነ – ንቀትል – ኒቀተላ
ውእቱ – ይቀትል – ኢቀተላ
ይእቲ – ትቀትል – ተቀተላ
ውእቶሙ – ይቀትሉ – ኢቀተሉ
ውእቶን – ይቀትላ – አቀተላ
አንቲ – ትቀትሊ – ተቀተሊ
 

ጥንታዊ ቃላትን እየወሰዱ ቋንቋን በአንድ መመደብ የሚቻል ነው፡፡ ጥንታዊ አናባቢ /ኧ/ ከአካድያን ይልቅ በግእዝ መጠበቁ ግእዝን ልዩ ያደርገዋል፡፡ አካድያን እና ግእዝ በካልአይ የመጥበቅ ድምጽ ሲኖራቸው ጥንታዊ የደቡብ ዐረብ ልሳን ግን የሌለው በመሆኑ ግእዝን እንዴት ከሌላው ቋንቋ ከሳባ መጣ እንላለን? በተጨማሪ የግእዝን ከሌሎች ከሚመስላቸው ከማዕከላዊው ምሥራቅ ሀገራት ቋንቋዎች ስናገናኘው የጥንታዊ የቋንቋ ባሕርይ ቅርጽና ድምጽ መያዙን የምናገኝባቸው ቃላት እንጠቀማለን፡፡

 
ጥንታዊ ቃል – የአካድ – ዐረበኛ – ዕብራይስጥ – የሦርያ – ግእዝ
አብ «-»    አብ –         አብ –     አብ –         አባ –   አብ
ልበ – ልብ – ሉብ /ጥ/ – ሌይብ /ጥ/ – ሌባ – ልብ
ቤት /በይት – ቢቱ – በይት – ባይ /ቤት – በይት /ታ – ቤት
ደም- – – ደም – ዳም – ድማ – ደም
ዐይን – ዓን – ዐይን – ዐዪን – ዐይ-ና – ዐይን
ወይን – – – ወይን – ያዪን – – – ወይን
ወዘተ. . .
ይ – – – /ይ/ አልቦ ዪ – ይ