የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከበረ።

ዜና ዕረፍት

ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በአብነት መምህርነታቸው አያሌ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን በማፍራታቸውና ባበረከቱት የረዥም ዘመን አገልግሎት የመቀሌ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራልና የከሣቴ ብርሃን ሰላማ መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ሆነው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ተሹመው በተመደቡበት ኃላፊነት ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ የካቲት ፳፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።

የብፁዕነታቸው በረከት ይደርብን!

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት፣ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከጥር ፳፱ እስከ የካቲት ፩ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ለ ፫ ተከታታይ ቀናት በመላው ዓለም የታወጀው የነነዌ ፆም እና ምሕላ መጠናቀቅን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ፡፡

“መንፍስ ቅዱስ እናንተን ጳጰስ አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ …ተጠንቀቁ” (ሐዋ.፳፥፳፰)

ከዚህ ኃይለ ቃል ሦስት ነገሮችን እንማራለን፤ አንደኛ ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር አምላክ በደሙ ዋጅቶ የመሠረታት መሆኑን፣ ሁለተኛ ጳጰስ አድርጎ የሚሾም መንፈስ ቅዱስ መሆኑን፣ ለመንጋውና ለራሳችን መጠንቀቅ አስፈላጊ መሆኑን ቅዱስ ጳውሎስ ለኤፌሶን መሰነባባቻ ባደረገው ንግግር ይህን ኃይለ ቃል ተናግሯል፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሦስት ሺህ ዘመናት ውስጥ የቆየው ቀኖና፣ሥርዓተ ሢመት፣ ትውፊት ቅብብሎሽ በአሁኑ ዘመን ለመሻር መንጋውን እየበተነ አባቶችን እየሸረሸረ ያለውን ክስተት ሁሉ በየደረጃው ያለው የድርሻውን ለመወጣት ከማንኛውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት የምንነሣበት ጊዜ መሆኑን ነው፡፡

“ለሦስት ቀናት በጾምና በጸሎት በአንድ ልብ ሆነን ወደ ፈጣሪያችንን እንድንጮህ አደራ እንላለን” ቅዱስ ሲኖዶስ