‹‹ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሽ፥ ተመለሽ›› (መሓ.፯፥፩)

ውድ አንባብያን! እንደምን ሰነበታችሁ? ከዚህ በፊት የእመቤታችንን የስደቷን ነገር አንሥተን ‹‹ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሽ፥ ተመለሽ›› በሚል ርእስ ከክፍል አንድ እስከ ሦስት አድርሰናችሁ ነበር፡፡ ጥሩ ትምህርት እንዳገኛችሁበት ተስፋ እናደርጋለን፡፡

የዛሬው ትኩረታችን ያን ሁሉ መከራ የተቀበለችበት የስደቷን ምክንያትና ዓላማ መዳሰስ ነው፡፡

‹‹ሱላማጢስ ሆይ ተመለሽ ተመለሽ›› (መሓ.፯፥፩)

ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕፃንዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ፡፡ አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር ይገዛቸውም ዘንድ ያለውን ወንድ ልጅ ወለደች፡፡……..ሴቲቱም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቧት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ስፍራ ወደ በረሃ ሸሸች፡፡ (ራእ.፲፪፥፬-፮

‹‹ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሺ፥ ተመለሺ›› (መሓልየ መሓልይ ዘሰሎሞን ፯፥፩)

 እሾህ በተባለ ጥንተ አብሶ አዳማዊና ሔዋናዊ ኃጢአት መካከል ያበበች የፍሬ ሕይወት ክርስቶስ መገኛ አማናዊት የሃይማኖት አበባ እመቤታችን በዚህ በአበባው ወቅት (በጽጌ ወራት) መራራው የጣፈጠበት፥ ፍሬ ሕይወት ልጇን እንዳይገሉባት መራራውን የስደት ሕይወት የተጋፈጠችበት መታሰቢያ ወቅት ነው፡፡

‹‹ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሺ፥ ተመለሺ›› (መሓልየ መሓልይ ዘሰሎሞን ፯፥፩)

በብሥራተ መልአክ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደችውን አንድያ ልጇን ሄሮድስ ሊገድልባት በፈለገው ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሀገር ወደ ሀገር መሰደዷን የሚያመለክተውን፣  ከስደትም እንድትመለስ ጠቢቡ በትንቢት ቀድሞ የተናገረው ይህን ቃል ነው፡፡ ወቅቱ አብዝተን ስለ ስደቷና ተያያዥ ታሪኮች የምንማርበት፣ የምንጸልይበት፣ የምናስተምርበትና የምንዘምርበት ወቅት በመሆኑ በዚህ ርእስ ተከታታይ ጽሑፎችን ለማቅረብ እንሞክራለን፤ ተከታተሉን!

የሐዋርያት ጾም

ጾሙን በጰራቅሊጦስ ማግሥት ጀምረው የጥያቄያቸውን መልስ እስኪያገኙ እስከ ሐምሌ አምስት ቆይተዋል። የጌታ ፈቃዱ ሆኖም በሐዋርያነት አገልግሎታቸው የሚታወቁት የሰማዕትነት ኅልፈታቸው ጾሙን ፈተው ለአገልግሎት በተሠማሩበት ዕለት ሁኗል (ስንክሳር ዘሐምሌ አምስት)። በረከታቸው ይደርብን!

“በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንን ተሸከመ፤ ስለመተላለፋችን ቆሰለ፤ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን” (ኢሳ.፶፫፥፬‐፮)

ሰባት የጾምና የጸሎት ሳምንታትን አሳልፈን፣ “ሆሣዕና በአርያም” ብለን አምላካችን በመቀበል፣ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማሙን፣ መገረፍ መገፈፉን፣ መሰቀልና መሞቱን እንዲሁም የድኅነታችንን ዕለት ትንሣኤን በተስፋ ለምንጠብቅበት ለሰሙነ ሕማማት ደርሰናልና አምላካችን እንኳን ለዚህ አበቃን!

ኒቆዲሞስ

ቅዱስ ያሬድ ንብ የማትቀስመው አበባ እንደሌላት ሁሉን ቀስማ ያማረ የጣፈጠ ማር እንድትሠራ እርሱም ሐዲሳትን ከብሉያት እያስማማ ለጀሮ የሚስማማ ኅሊናን የሚመስጥ ድንቅ ዜማ ባዘጋጀልን መሠረት የዐቢይ ጾም ሰባተኛው ሳምንት ኒቆዲሞስ ተብሎ ይጠራል፡፡ ሊቁ “ኒቆዲሞስ ስሙ ዘሖረ ኀቤሁ ቀዲሙ ሌሊተ ወይቤሎ በጽሚት ረቢ ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጽአከ ሖረ ኀቤሁ ዘስሙ ኒቆዲሞስ ወይቤሎ ለኢየሱስ ረቢ ሊቅ ንሕነ ነአምን ብከ ከመ እምኀበ አብ መጻአከ ከመ ትኩን መምሕረ ወበምጽአትከ አብራህከ ለነ ወሰላመ ጸጎከነ አንሥእ ኃይለከ ወነዓ አድኅነነ፤ አስቀድሞ በሌሊት ወደርሱ ይሔድ የነበረ ስሙ ኒቆድሞስ የሚባል ሰው በቀስታ “ሊቅ ሆይ ከአብ ዘንድ እንደመጣህ እናውቃለን” አለው። ኒቆዲሞስም ወደ እርሱ ሔደ፤ ረቢ ኢየሱስንም ሊቅ (አዋቂ) እንደሆንክ ለማስተማር ከአብ ዘንድም እንደመጣህ እኛ እናውቃለን፤ በምጽአትህም አበራህልን፤ ሰላምንም ሰጠኸን፤ ኃይልህን አንሳ፤ መጥተህም አድነን አለው” ይለናል። (ጾመ ድጓ)

“መኑ ውእቱ ገብር ኄር፤ የታመነ በጎ አገልጋይ ማን ነው?” (ቅዱስ ያሬድ)

ፈልፈለ ማኅሌት ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው እንዲህ እያለ ይዘምራል፤ “ገብር ኄር ወገብር ምእመን ገብር ዘአሥመሮ ለእግዚኡ፣ መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወገብር ምእመን ዘይረክቦ እግዚኡ በምግባረ ሠናይ ወይሠይሞ ዲበ ኵሉ ንዋዩ ወካበ ይቤሎ እግዚአብሔር ገብር ኄር ወምእመን ዘበውኀድ ምእመነ ኮንከ ዲበ ብዙኅ እሠይመከ ባእ ውስተ ፍሥሓሁ ለእግዚእከ፤ጌታው በመልካም ሥራ የሚያገኘው በሐብቱ ሁሉ ላይ የሚሾመው የታመነ በጎ አገልጋይ ማን ነው? ዳግመኛም እግዚአብሔር አንተ የታመንክ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ የታመንህ ስለኾንህ በብዙ እሾምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ይለዋል፡፡” (ጾመ ድጓ) ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዐቢይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት ገብር ኄር ልጆቿን ስለ አገልግሎትና የአገልግሎት ዋጋ በስፋት የምታስተምርበት ሳምንት ነው።

“ልትድን ትወዳለህ?” (ዮሐ.፭፥፭)

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የዐቢይ ጾም ሳምንታትን በቅዱስ ያሬድ ስያሜ መሠረት አራተኛውን ሳምንት መጻጉዕ ብላ ታከብራለች። “መፃጉዕ” ማለት “ድውይ፥ በሕመም የሚሰቃይ፥ የአልጋ ቁራኛ” ማለት ነው። ይህንንም ስያሜ እንዴት እንደመጣ ለማየት በዕለቱ የሚነበበውን የወንጌል ክፍል ብንመለከት እንዲህ ይላል። “ከታመመ ሠላሳ ስምንት ዓመት የሆነው አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ ‘ልትድን ትወዳለህ’ አለው። ድውዩም ጌታ ሆይ አዎን! ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም እንጂ፤ ነገር ግን እኔ በመጣሁ ጊዜ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል አለ። ጌታ ኢየሱስም ‘ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ’ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ፤ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ፤ ያም ቀን ሰንበት ነበረ” ይላል። (ዮሐ.፭፥፭-፲)

ምኵራብ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የዐቢይን ጾም ሦስተኛ ሳምንት ምኩራብ ብላ ትጠራዋለች። ዓመት እስከ ዓመት ያለውን ይትበሃል በያዘው ድጓ ዐቢይ ጾም በገባ በሦስተኛው ሳምንት መጀመሪያው ቀን ቅድስት በሆነች በሰንበት በሚዘመረው በጾመ ድጓው ክፍል “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሀረ ቃለ ሃይማኖት፤ ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ” ሲል እናገኘዋለን።