“ስለ ምን ጾምን?” (ኢሳ.፶፰፥፫)
የነነዌ ከተማ ሰዎች ኃጢአት በትንቢተ ዮናስ ውስጥ አንድ ሁለት ተብሎ አልተገለጸም፤ በጥቅሉ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፥ ክፉታቸውም ወደ ፊቴ ወጥቶአልና በእርስዋ ላይ ስበክ” ተብሎ በእግዚአብሔር ከመገለጹ በቀር አልተዘረዘረም። (ዮናስ ፩፥፪) ሆኖም ክፉታቸው ወደ ፊቴ ወጥቶአልና የሚለው የልዑል አምላክ ቃል የኃጢአታቸውን ታላቅነት ያመለክታል። ኃጢአታቸው በዮናስ መጽሐፍ ውስጥ አልተዘረዘረም አልን እንጂ በሌሎቹ መጻሕፍት ውስጥ ግን ተዘርዝሯል። ለምሳሌ ነቢዩ ናሆም የነነዌ ኃጢአት ምን ምን እንደነበረ ገልጿል። እነዚህም፡-