የሆሳዕና ቡሻና በዐታ ለማርያም ገዳም ተቃጠለ

 ጥር 13 ቀን 2006 ዓም.                            

በእንዳለ ደምስስ

በሐድያና ስልጢ ሀገረ ስብከት ጎረጎራ ወረዳ ውቅሮ ፋለታ ቀበሌ የደብረ ምጥማቅ ቡሻና በዓታ ለማርያም ገዳም ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም. የከተራ ዕለት መነሻው ባልተወቀ ምክንያት ሙሉ ለሙሉ መቃጠሉን የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ መልአከ ገነት ቆሞስ አባ ቢኒያም መንቻሮ ገለጹ፡፡bushana

 

ሥራ አስኪያጁ በሰጡን መረጃም የከተራ ዕለት የበዐታ ለማርያም ታቦት ወደ ጥምቀተ ባሕር ከወረደ በኋላ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ መቃጠሉን ገልጸው ቤተ ክርስቲያኑ ንዋያተ ቅዱሳቱን ጨምሮ ሙሉ ለሙሉ ወድሟል ብለዋል፡፡

 

በካዝና ውሰጥ የነበረው የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጽላት ካዝናው በእሳቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመለብለቡ ምክንያት መክፈት እንዳልተቻለና መቃጠልና አለመቃጠሉን እንዳልተረጋገጠ ያስታወቁት ሥራ አስኪያጁ፤ ጉዳዩን ለፖሊስ በማሳወቅ የቃጠሎውን መንስኤ ለማጥራት ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

 

የቡሻና በዐታ ለማርያም ገዳም ከዚህ በፊት ሥዕለ አድኅኖ በዛፎች ላይ ታይቶበት በነበረ ቦታ መቃኞ ተሰርቶለት ሐምሌ 2001 ዓ.ም. ቅዳሴ ቤቱ እንደተከበረ ይታወቃል፡፡

 

ትልቁ በገና

ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም.                                                                                                                                                        

እንዳለ ደምስስ

የማኅበረ ቅዱሳን የመዝሙር ክፍል አባላትና የአቡነ ጎርጎርዮስ የትምህርትና ሥልጠና ማእከል በበገና ድርደራ የሠለጠኑ 250 ወጣቶችን የከተራ በዓልን ለማክበር የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳምን በዝማሬ አጅበው ወደ ጃንሜዳ 06Begenaሰልፋቸውን ይዘው በገናቸውን እየደረደሩ ይጓዛሉ፡፡ አሰላለፋቸውና ብዛታቸው እንዲሁም ጸዓዳ አለባበሳቸው ለዓይን ይማርካሉ፤ እንደ ምንጭ ውኃ ኮለል እያለ የሚፈሰው ዝማሬ ነፍስን ያለመልማል፡፡ ምእመናን በትኩትና በተመስጦ፤ ጎብኚዎች ባዩት ነገር በመገረም የፎቶ ግራፍና የቪዲዮ ካሜራቸውን አነጣጥረው የቻሉትን ያህል ያነሳሉ፡፡

 

በመካከላቸው አንድ በገና ከሁሉም ቁመት በላይ ረዝሞ ይታያል፡፡ ሰልፉ ቆም ሲል ጠጋ ብዬ ተመለከትኩት፡፡ ከዚህ በፊት እንዲህ አይነት ትልቅ በገና አይቼ እንደማላውቅ እርግጠኛ ነኝ፡፡ በገናውን የያዙት ልጆች መገረሜን አስተውለው “ይህ በገና በዓለማችን ከሚገኙ በገናዎች ትልቁ ነው፡፡ በገና እግዚአብሔርን ለማመስገን የምትጠቀመው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሰቲያን ብቻ ናት፡፡ እስከ ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥም ይህንን በገና በትልቅነቱ የሚስተካከለው የለም” አሉኝ፡፡ በገናውን እንደ ሕፃን ልጅ በፍቅር እንደሚያሻሽ አባት ዳሰስኩት፡፡

 

በገናው ሁለት ሜትር ከሃያ ሳንቲ ሜትር ይረዝማል፡፡ አሥር አውታሮች ሲኖሩት እያንዳንዱ አውታር በስምንት በጎች አንጀት የተሠራ ነው፡፡ አሥሩ አውታሮች በአጠቃላይ በ80 በጎች አንጀት ተዘጋጅተዋል፡፡ ከላይ ያለው ብርኩማ ስልሳ ሳንቲ ሜትር ይረዝማል፡፡ በተጨማሪም በገናውን ለማዘጋጀት የአንድ ትልቅ በሬ ቆዳ ፈጅቷል፡፡

 

ማኅበረ ቅዱሳን በየዓመቱ በጥምቀት በዓል ላይ ለታቦታት ክብር ሲባል፤ እንዲሁም ሊጠፋ ተቀርቦ የነበረውን የቤተ ክርስቲያናችን ቅርስ ቀድሞ ወደነበረበት ለመመለስና ለትውልድ ለማስተላለፍ በአቡነ ጎርጎርዮስ ሥልጠና ማእከል ወጣቶችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል፡፡

 

ለጥምቀት በዓል በክብር የወጡት ታቦታት በክብር ተመልሰዋል

 ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

ለጥምቀት በዓል ከመንበራቸው በክብር የወጡት ታቦታት ወደመጡበት አብያተ ክርስቲያናት በእልልታና በዝማሬ ታጅበው ተመልሰዋል፡፡ከሌሊቱ 12፡30 ሰዓት ጀምሮ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፤ ወእጨጌ ዘመንበረ 06Epiphany17ተክለ ሃይማኖት ፤ ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ ከሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዩልዮስ፤ ከተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና የመንግሥት ተወካዮች ጋር በመሆን በጃንሜዳ ጥምቀተ ባሕር ተገኝተዋል፡፡

 06Epiphany21

በቅዱስነታቸው መሪነት የጸሎተ ወንጌል ሥርዓት በማድረስ በዐራቱም ማእዘናት፤ ከዐራቱም የወንጌል ክፍሎች ዕለቱን በማስመልከት ምንባባት ተነበዋል፡፡ ቀጥሎም ቅዱስነታቸው ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር ሆነው ጸበሉን ባርከው  ለምእመናን ረጭተዋል፡፡

 

የጥምቀት ሥነሥርዓቱ ቀጥሎም የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና የሰንበት ትምህርት ቤቱ መዘምራን ዕለቱን በማስመልከት ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡06Epiphany22የሕንድ ኦርቶዶክስ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዩልዮስ ባስላለፉት መልእክት “የሕንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እኅትማማቾችና የቀረበ ግንኙነት ያላቸው ናቸው፡፡  በተለይም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታላቅ ታሪክና ትውፊት ያላት በመሆኗ የጥምቀት በዓልን በደመቀና ማራኪ በሆነ ሃይማኖታዊ ሥነሥርዓት የምታከብር ብቸኛ ቤተ ክርስቲያን ናት” ብለዋል፡፡

 

 

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በመጨረሻ በሰጡት ቃለ ምዕዳን “ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ይቀድስ፤ ያጣነውን ልጅነት ይመልስልን ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ፡፡ ሰላሙንም አደለን፡፡ ይህንንም ጠብቀን መኖር ይገባናል” ብለዋል፡፡

 

በመጨረሻም በትናንትናው ዕለት በክብር ከየአብያተ ክርስቲያናቱ ወጥተው ወደ ጥምቀተ ባሕር የወረዱት ታቦታት በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ በሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራንና ምአመናን ታጅበው ወደየመጡበት በክብር ተመልሰዋል፡፡ የቅዱስ ሚካኤል ታቦታት ግን በነገው እለት የሚመለሱ በመሆኑ በዚያው ይገኛሉ፡፡

 

የጥምቀት በዓል አከባበር በጃን ሜዳ

 ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም

የከተራ በዓል ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም. በጃሜዳ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ የዋለ ሲሆን፤ ምሽቱን ደግሞ በስብከተ ወንጌልና በዝማሬ ቀጥሎ በሥርዓተ ቅዳሴ ተፈጽሟል፡፡ በመላው ኢትዮጵያ በሚገኙ የጥምቀተ ባሕር ቦታዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ የከተራ በዓል በድምቀት ተከብሯል፡፡

ጥር 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ከሌሊቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች እየተካሔዱ ሲሆን፤ ጃን ሜዳ የሚካሔደው ሥነሥርዓት ቅዱስነታቸውና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በጸሎተ ወንጌል ተጀምሮ የጥምቀት መርሐ ግብሩ ይቀጥላል፡፡ የእለቱ ተረኛ የሆነው የወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ዝማሬ የበዓሉ አካል እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡

 

የከተራ በዓል በደብረ ታቦር ከተማ በድምቀት ተከበረ

 

 

ጥር10 ቀን 2006                                                                                                                      ዳንኤል  አለሙ  ደብረ ታቦር ማእከል

በደብረ ታቦር ከተማ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሰት፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና ማኅበራት እንዲሁም ሕዝበ ክርስቲያኑ ከሰባት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት የመጡ ታቦታትን አጅበው በአጅባር ባሕረ ጥምቀት በድምቀት ተከበረ፡፡

የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንቱ ታባታቱን በቃለ እግዚአብሔርና በቅዱስ ያሬድ ዜማ፤ ከሰ/ትቤት መዘምራንና ምእመናን ጋር በምስጋናና በእልልታ በማጀብ በዓሉን አድምቀውታል፡፡

የከተራ በዓል መንፈሳዊ ይዘት በተሞላበት ሁኔታ በነጫጭ አልባሳት በደመቁ ምእመናን እና ምእመናት ተከብሮ ሲውል፤ ለከተማው ህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባጃጆች በባንዲራ እና ምስጢረ ጥምቀቱን በሚገልፁ ጥቅሶች ተውበው የተለየ ድምቀት ሰጥተውታል፡፡ በተጨማሪ ታሪካዊ እና ለታላቁ ደብር ለደብረ ታቦር ኢየሱስ በወጣቶች የተሰራ ሰረገላ በዓሉን ካደመቁት ትእይንቶች መካከል አንዱ ነበር፡፡

ደብረ ታቦር ለሀገሪቱ ሊቃውንት መፍለቂያ በመሆን በምሳሌነት የሚጠሩ ካህናት እንደተለመደው ሁሉ የሚማርክ ጣዕመ ዝማሬአቸውና በአባቶችሽ ፈንታ ልጆችሽ ተተኩልሽ እንዳለ ነብዩ ከሊቃውንቱ እግር ሥር ቁጭ ብለው የተማሩ የሰንበት ት/ቤቶች ወጣቶች ዝማሬ አቅርበዋል፡፡ የደብረ ታቦር ከተማ ባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤትም ለበዓሉ አከባበር የሚሆን የድምጽ ማጉያ በመስጠት እንዲሁም ከደብረ ታቦር ወረዳ ቤተ ክህነትና ማኅበረ ቅዱሳን ጋር በመተባበር የሀገሪቱን ባሕልና እሴት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላቸውን አድርገዋል፡፡

የከተራ መርሐ ግብሩ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የ4ቱ ጉባኤ መምህር የሆኑት የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንድርያስ ትምህርት፤ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል፡፡ እርሳቸውም በዓለ ጥምቀት ቤተ ክርስቲያናችን ከምታከብራቸው አበይት በዓላት መካከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው ፤ ታቦቱ ወደ ጥምቀተ ባሕር ወርደው የሚያድሩበት ምክንያት እግዚአብሔር ወልድ በፈለገ ዮርዳኖስ መጠመቁ ምሳሌ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በጥምቀቱም የሰው ልጅ ኃጢዓት የተደመሰሰበት፤ ከኃጢዓት ባርነት የወጣበት መሆኑን ገልጸው ምእመናን ዳግመኛ ወደ ኃጢዓት ባርነት እንዳይመለሱ መትጋ እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡ የጥምቀትን በዓልን ስናከብር ድኅንነት ነፍስን የምናገኝበት ከኃጢዓት ጸድተን የዘላለም ሕይወት የምንወርስበት በመሆኑ በሰላምና በፍቅር እንድናከብረው አበክረው አሳስበዋል፡፡

በዓለ ጥምቀቱ የሚከበርበት አጅባር ሜዳ አራት የታቦታት መግቢያ በሮች ያሉት ሲሆን ለብዙ ዘመናት ቅድስት ቤተክርስቲያን እየተገለገለችበት ቆይታለች፡፡ ይሁን እንጂ በሀገረ ስብከቱና በወረዳ ቤተ ክህነቱ ፈቃድና እውቅና የተቋቋመ ኮሚቴ ቢኖርም የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ አለመኖሩ፤ በህዝቡ ዘንድ ስጋት የፈጠረ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ስለሆነም የሀገር እና ቤተክርስቲያን ሀብት በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት ትኩረት ተሰጥቶት የይዞታ ማረጋገጫ ሊኖረው እንደሚገባ አባቶች እና የአካባቢው ምእመናን ገልጸዋል፡፡

 

የከተራ በዓል በጃንሜዳ በድምቀት ተከበረ

  ጥር 10/2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ 

የከተራ በዓል በጃን ሜዳ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቀነ ጳጳሳት፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች መዘምራንና ምእመናን እንዲሁም የተለያዩ የውጭ ሀገራት አምባሳደሮችችና ሀገር ጎብኚዎች በተገኙበት በድምቀት ተከበረ፡፡06Epiphany19

06Epiphany20ከአሥራ አንድ ታቦታት በላይ ከየአብያተ

ክርስቲያናት በክብር በመውጣት በዝማሬና በእልልታ እንደታጀቡ ወደ ጃንሜዳ አምርተዋል፡፡ የእለቱ ተረኛ አዘጋጅ የሆነው የደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን “ወረደ ወልድ እምሰማያት ውስተ ምጥማቃት፤ በፍስሐ ወበሰላም” በማለት እለቱን06Epiphany18 በማስመልከት ያሬዳዊ ወረብ አቅርበዋል፡፡ የደብሩ ፍቁረ እግዚእ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላትም “በሰላም አስተርዐየ፡ አስተርዐየ ወልደ አምላክ፤ ወተወልደ በሀገረ ዳዊት ተወልደ፤ በዮርዳኖስ ተጠምቀ ከመይቤ ዘወነ” እያሉ ዝማሬ በማቅረብ በዓሉን አድምቀውታል፡፡

06Epiphany15

ስለበዓሉ አከባበር ከሰሜን አሜሪካ የመጣችው ሀገር ጎብኚ በዓሉን አስመልከተን ላቀረብንላት ጥያቄ ስትመልስ “ከዚህ በፊት ለአንድ ጊዜ የመስቀልን በዓል አከባበር ተመልክቼ ነበር፡፡ እሰከዛሬም ከምደነቅባቸው ሃይማኖታዊ በዓላት አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ የጥምቀት በዓላችሁ ደግሞ የተለየ ነው፡፡ ልታከብሩትና ልትኮሩበት ይገባችኋል” ስትል አስተያየቷን ሰጥታለች፡፡

06Abune Mathias

 

በመጨረሻም ቅዱስነታቸው በሰጡት ቃለ ምእዳን “ጌታን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ መጣ፡፡ ለአምስት ሺሕ አምስት መቶ ዘመናት በላያችን ተጭኖ የነበረውን መርገመ ነፍስ መርገመ ሥጋን አስወግዶ በረከተ ነፍስ በረከተ ሥጋን ለማደል በዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡ ኃጢዓታችንንም አስወገደ፡፡ ከዲያብሎስ ቁራኝነትም አላቀቀን፡፡ ወደ ወገኖቹ መጣ ወገኖቹ ግን አልተቀበሉትም፡፡ ነገር ግን ለተቀበሉት የእግዚአብሔር ልጅ መባልን ሰጣቸው፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን የመንግሥቱ ወራሾች እንድንሆን የተጠራነው በጥምቀት ነው” ብለዋል፡፡ 

 

የከተራ በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው

ጥር 10/2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

የከተራ በዓል በመላው ኢትዮጵያ በድምቀት እየተከበረ ነው፡፡

ከየአብያተ ክርስቲያናቱ ታቦታት በብፁዓን ሊቀነ ጳጳሳት፤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ በሰንበት ትምህርት ቤተ መዘምራንና ምእመናን ታጅበው ወደ ጥምምቀት ባሕር በማምራት ላይ ይገኛሉ፡፡
የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ፤ የቅዱስ በዓለ ወልድ፤ የታዕካ ነገሥት በዐታ ለማርያም፤ የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም፤ የመንበረ መንግሥት ቅዱሰ ገብርኤል ታቦታት በአንድነት በመሆን ወደ ጃን ሜዳ በማምራት ላይ ይገኛሉ የሌሎቹም አድባራትና ገዳማት ታቦታት ወደ ጃን ሜዳ በመቃረብ ላይ ናቸው፡፡

06Epiphany1    06Epiphany2   06Epiphany3

 

 06Epiphany4

ዝግጅት ለጥምቀት በዓል

 

IMG 0062የጥምቀት በዓል በኢትጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ የጥምቀት በዓልን በአደባባይ በማክበር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ብቸኛዋ ቤተክርስቲያን  ስትሆን ከተለያዩ ዓለማት የበዓሉ ታዳሚ ለመሆን የእምነቱ ተከታዮችና ቱሪስቶች ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ወደ ጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታዎች ይሄዳሉ፡፡ ከበዓሉ ቀደም ብሎ ለታቦታቱ ማረፊያና ለበዓሉ ማክበሪያ የተለያዩ ዝግጅቶች ይከናወናሉ፡፡
 ካህናትና ምእመናን  ለበዓሉ የሚስማማ ልብስ በመልበስ ታቦታቱን በማጀብ  ከከተራ ጀምሮ በዝማሬና በእልልታ እስከ ቃና ዘገሊላ ድረስ በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡
ሰሞኑንም በሀገራችን የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታዎችና ታቦታቱ የሚጓዙበት መንገዶች ሲጸዱና ሲያሸበርቁ ሰንብተዋል፡፡ ጥቂት ቦታዎችን ለመጎብኘት ሞክረናል፡፡

አዲስ አበባ
በአዲስ አበባ ከተማ 46 የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታዎች አሉ፡፡ ወደነዚህ ቦታዎች የሚወስዱ መንገዶች ሁሉ እየጸዱ በኢትዮጵያ ባንዲራ፣ በዘንባባና በቄጤማ እያሸበረቁ ይገኛሉ፡፡
በአራዳና በጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቶች ያገኘነው መረጃ እንደሚገልጸው፡-
1.    በጃንሜዳ የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ከአስራ አንድ ባላይ ታቦታት የሚያድሩ ሲሆን እነሱም መንበረ ፓትርያርክ ቅ/ቅ/ማርያም ገዳም፣ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም፣ መ/ፀ/ቅ/ሥላሴ፣ መ/መ/ቅ/ገብርኤል፣ ገነተ ጽጌ ቅ/ጊዮርጊስ፣ ቀጨኔ ደ/ሰ መድኃኔዓለም፣ መንበረ ልዑል ቅ/ማርቆስ፣ ወ/ነጎድጓድ ቅ/ዮሐንስ ፣ገነተ ኢየሱስ፣ መ/ህ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ አንቀጸ ምሕረት ቅ/ሚካኤል ሲሆን የ2006 ዓ.ም በዓል መንፈሳዊ አገልግሎት አቅራቢ ተረኛ የወ/ነጎድጓድ ቅ/ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡

IMG 0034IMG 0045

2.    ወረዳ 13 ቀበሌ 16 ቀበና ሼል አካባቢ ቀበና መድኃኔዓለምና ቀበና ኪዳነምሕረት
3.    በጉለሌ እንጦጦ ተራራ  መ/ፀ ር/አድባራት ቅ/ማርያም እና እንጦጦ ደ/ኃ/ቅ/ራጉኤል
4.    ሽሮ ሜዳ አካባቢ
መንበረ ስብሐት ቅ/ሥላሴ፣ ሐመረ ኖህ ቅ/ኪዳነ ምሕረት
5.    ወረዳ 11 ቀ. 27 ቁስቋም አካባቢ መ/ንግሥት ቁስቋም ማርያም
6.    አዲሱ ገበያ በላይ ዘለቀ መንገድ አካባቢ ደ/ሲና እግዚአብሔር አብ፣ መንበረ ክብር ቅ/ሚካኤል እና አቡነ ተክለሃይማኖት
7.    ጉለሌ አምባ ቅ/ኪዳነ ምሕረትና ድልበር መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን
8.   ወረዳ 11 ቀበሌ 20 ፡-ገርጂ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን፤ የረር ቅዱስ ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን፤ ቦሌ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን
9.   ወረዳ 17 ቀበለሌ 24 /ለምለም ሜዳ/፡-ደብረ ምጽላል እግዚአብሔር አብ ቤተ ክርስቲያን፤
10.  ወረዳ 17 ቀበሌ 2 ወንድራይድ ት/ቤት አካባቢ፡- 7 አብያተ ክርሰቲያናት
11.  ወረዳ 28፡- ሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም፤ አቡነ አረጋዊ፤ ቅዱስ ኡራኤል
12.  ወረዳ 16/17 ቀበሌ 1፡- ደብረ እንቁ ልደታ ለማርያም፤
13.  ሎቄ ገበሬ ማኅበር፡- ሎቄ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
14.  ወረዳ 17 ገበሬ ማኅበር፡- ቦሌ ቡልቡላ ቅዱስ ጊዮርጊስ
15.  ወረዳ 28 ገበሬ ማኅበር ቀበሌ 14/15 ሲኤም ሲ፡- ሰሚት ኪዳነ ምሕረት፤ ቀሬ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤  ወጂ መድኀኔዓለም
16.  ቦሌ 14 /15፡- መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ የረር ቅዱስ ገብርኤል፤ የረር ጽርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ
17.  ወረዳ 28 ገበሬ ማኅበር፡-  ደብረ ኢያሪኮ እግዚአብሔር አብ
18.  ራስ ኃይሉ ሜዳ/ መድኀኔዓለም ትምህርት ቤት አካባቢ፡- ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል፤ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል፤ ጽርሐ አርያም ሩፋኤል፤ ብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጼጥሮስ ወጳውሎስ፤ ጠሮ ሥላሴ
19.  ትንሹ አቃቂ ወንዝ/ ገዳመ ኢየሱስ/፡- ቀራንዮ መድኀኔዓለም፤ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል፤ ቅዱስ ጳውሎስ፤ ገዳመ ኢየሱስ፤ ደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ፊልጶስ፤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም፤ ፊሊዶር አቡነ ተክለ ሃማኖት
20.  አስኮ ጫማ ፋብሪካ / ሳንሱሲ አካባቢ፡- አስኮ ደብረ ገነት ቅዱስ ገብርኤል፤ ኩርፎ ቅዱስ ጊዮርጊስ
21.  ወረዳ 25 ቀበሌ 25 አካባቢ፡- ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ገብረ ክርስቶስ፤ ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ አውጉስታ ቅድስት ማርያም፤ ዳግማዊት ጸድቃኔ ማርያም፤
22.  ወረዳ 24 ቀበሌ 15፡- አየር ጤና ኪዳነ ምሕረት፤ ጀሞ ሥላሴ፤ ደብረ ራማ ቅዱስ ገብርኤል
23.  ቃሌ 15 ቀበሌ፡- ቃሉ ተራራ አቡነ ሃብተ ማርያም፤ ፍኖተ ሎዛ ቅድስት ማርያም
24.  አያት ቤተ ሥራዎች ድርጅት፡- መሪ አቡ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፡- መሪ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት፤ ቅዱስ ሩፋኤል፤ መሪ ቅድስት ሥላሴ
25.  ወረዳ 28 ገበሮ ማኅበር፡- ኢያሪኮ እግዚአብሔር አብ
26.  ቤተል ኳስ ሜዳ፡- ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል፤ አንፎ ቅዱስ ኡራኤል
27.  ወረዳ 18 ቀበሌ 26፡- ቅዱስ እስጢፋኖስ፤ ደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ
28.  ወረዳ 16 ቀበሌ 11 ኳስ ሜዳ፡- ደብረ ጽጌ ቅዱስ ኡራኤል፤ የካ ቅዱስ ሚካኤል
29.  አድዋ ፓርክ፡-ቦሌ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም

IMG 0056

ከአዲስ አበባ ወጪ የሚገኙ አኅጉረ ስብከት በከፊል
  የበዓለ ጥምቀት ዝግጅት በጎንደር – ፋሲለደስ፡-
ቀሃ ኢየሱስ፤ ዮሐንስ መጥምቅ፤ አባ ጃሌ ተክለ ሃማኖት፤ እልፍኝ ቀዱስ ጊዮርጊስ፤ ፊት ሚካኤል፤ አጣጣሚ ሚካኤል፤ መንበረ መንግሥት መድኀኔዓለም
ፋሲለድስ መዋኛ ፡- 8 ታቦታት
ልደታ ለማርያም
በዓታ ለማርያም
   አቡነ ሐራ – ሩፋኤልን ዞሮ ይገባል
በጎንደር ዙሪያ በሚገኙ 13 ቀበሌዎች፤ 13 ክፍለ ከተማዎችና የገጠር ቀበሌዎች

በሐዋሳ  የበዓለ ጥምቀት ዝግጅት
ፒያሳ ሔቁ አካባቢ፡- ደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም
ቅዱስ ገብርኤል
ቅድስት ሥላሴ
ፋኑኤል
በዓለ ወልድ
ዳቶ ኪዳነ ምሕረት
ሐዋሳ መግቢ በይርጋለም ሞኖፖል አካባቢ፡- ደብረ ምጥማቅ መድኃኔዓለም፤ አቡነ ተክለ ሃማኖት፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ

የበዓለ ጥምቀት ዝግጅት በሚዛን ተፈሪ
በሚዛን ተፈሪ ከተማ በሚዛንና አማን ክፍለ ከተማ ለሚከበረው  በዓል ከከተራው  ጀምሮ የከተማዋን ዋና መንገድ በአረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ  የማስዋብ ስራ በከተማው የእምነቱ ተከታይ ወጣቶች ተሰርቷል:: በከተማው የዘንድሮው የበዓሉን ዝግጅት ተረኛ የሆኑት የአቡነ ተክለሀይማኖት የእናቶች አንድነት ገዳምና የቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስትያን ለታቦታት ማደርያና እንዲሁም ለስርኣተ ማኅሌቱና ቅዳሴው የሚከናወንበት ድንኳን በሰበካ ጉባኤያት አስተባባሪነት፣ በወጣት ሰንበት ተማሪዎች ፣ በሚዛን መዕከል አባላት፣ በሚዛን ግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችና በአካባቢው የሚገኙ የእምነቱ ተከታይ ወጣቶች ተባባሪነት የጥምቀተ ባህር ማክበርያ ቦታ ጽዳት ከተደረገ በኋላ ድንኳንና ሌሎች አስፈላጊ ቁሳቁሶችን በማቅረብ በዓሉን ለማድመቅ ተዘጋጅተዋል::
በዓሉ የሚከበረው በሁለት የጥምቀተ ባህር ስፍራዎች ኮሶኮልና አማን ጥምቀተ ባህር ናቸው፡፡  በሚዛን ክፍለ ከተማ ከሾርሹ በዓለ ወልድ አንድ ታቦት፣ ከሚዛን ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ሁለት ታቦታት፣ ከሚዛን ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሁለት ታቦታት፣ ከሚዛን ማረሚያ ቤት ቅዱስ ሚካኤል  አንድ ታቦት በተለምዶ ኮሶኮል ወደሚባለው ጥምቀተ ባህር ጉዟቸውን የሚያደርጉ ሲሆን ፣ በአማን ክፍለ ከተማ ደግሞ ከደብረ መድኀኒት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሁለት ታቦታት፣ ከቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አንድ ታቦት፣ ከደብረ ሰላም ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን ሁለት ታቦታት፣ ከዛሚቃ አባ ሳሙኤል ገዳም አንድ ታቦት፣ ከቅዱስ እስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን አንድ ታቦት ፣ ከመንበረ ንግስት ቅድስት ቁስቋም ቤተ ክርስቲያን አንድ ታቦት ወደ አማን ጥምቀተ ባህር እንደሚዎጡና በአጠቃላይ ቁጥራቸው አስራ አራት የሚሆኑ ታቦታት ወደ ሁለቱ ጥምቀተ ባህር እንደሚያመሩ መረጃዎች ይጠቁማሉ::
ወጣቶች እንደተለመደው ዘንድሮም ሕዝቡ በግፍያ እንዳይጎዳና መጨናነቅ እንዳይፈጠር ታቦታት በሚያልፉበት መንገድ ላይ ምንጣፍ እየተሸከሙ በማንጠፍ ባለፉት ጊዜያት ያሳዩት የነበረው አገልግሎት ዘንድሮም ለቤተ ክርስቲያናቸውና ለእምነታቸው ያላቸውን ፍቅርና ክብር ለማሳየት ተዘጋጅተዋል፡፡ /ከሚዛን ማዕከል ሚድያ ክፍል/

የጥምቀት በዓል ዝግጅት በወልድያ
በወልድያ ከተማ የጥምቀት በዓል ከዋዜማው ጥር 10 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በድምቀት እንደሚከበር ተገለፀ፡፡
የሰሜን ወሎ ሃገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ክፍል ኃላፊና የወልድያ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል ስጦታው ሞላ የበዓሉን አከባበር አስመልክተው በሰጡት መረጃ በከተማው ውስጥ ያሉ አድባራትና በዙሪያው የገጠር አብያተ ክርስቲያናት የከተራ በዓሉን በወልድያ ታቦት ማደሪያ በአንድ ላይ ያከብራሉ፡፡
በከተማውና በዙሪያው ያሉ የ10 አብያተ ክርስቲያናት 15 ታቦታት ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ ወደ ታቦት ማደሪያው እንደሚንቀሳቀሱና ምዕመናንም በሰዓቱ ተገኝተው የሚከብሩ ሲሆን፤ ምዕመናን በዓሉን በሰላምና በፍቅር እንዲሁም ጧሪ የሌላችውን አረጋዊያንና አሳዳጊ የሌላቸው ህፃናትን በመርዳት እንድያከብሩ ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
ከባለፉት ሁለትና ሦስት ዓመታት ወዲህ በበዓላት አከባበር ወጣቱ እያሳየው ያለው ተሳትፎና ሥነ-ስርዓት እጅግ የሚያስደስት በመሆኑ በዚህ ዓመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሚጠበቅ ሲሆን፤
ታቦታቱ ጉዞ የሚያደርጉበትን ጎዳናዎች በማፅዳት፣ ሠንደቅ ዓላማዎችን በመስቀል፣ ምንጣፍ በማንጠፍና ቄጤማ በመጎዝጎዝ ለእግዚአብሔር ያላቸውን ፍቅር እየገለፁ ይገኛሉ፡፡ በዓሉን ለማክበር ሰ/ት/ቤቶች፣ ማኅበራትና ወጣቶች ዝግጅት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በዕለቱ መዝሙር፣ ዕለቱን የተመለከተ ስብከተ ወንጌልና ልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች ከተካሄዱ በኋላ 11፡30 ላይ ታቦታቱ ወደ ተዘጋጀላቸው ማረፊያ ይገባሉ፡፡ በዚሁ የዋዜማ በዓሉ ፍፃሜ ይሆናል፡፡ /ወልድያ ማዕከል  ሚድያ ክፍል/

 

 

ቅዱስ ፓትርያርኩ ምእመናን ለመዋቅራዊ ለውጡ ድጋፍ እንዲሰጡ ጠየቁ

 

 

ጥር 9/2006 ዓ.ም.

 

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጥር 7 ቀን 2006 ዓ.ም. የቅድስት ሥላሴን ዓመታዊ የንግሥ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በከበረበት ወቅት ቤተ ክርስቲያኗ በለውጥ ላይ በመሆኗ ምእመናንና አገልጋይ ካህናት ለውጡን ተግባራዊ ለማድረግ እንዲተባበሩ ጥሪ አስተላለፉ፡፡

ቅዱስነታቸው የዕለቱን በዓል አስመልከተው ጥልቅ መንፈሳዊ ትምህርት ካስተማሩ በኋላ በትምህርታቸው ማጠቃለያም ቤተ ክርስቲያን የምእመናንንና የካህናት በመሆኗ የሁለቱ አንድነት አገልግሎቱን የተሟላና የሠመረ እንደሚያደርገው ገልጸው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተንሰራፍቶ ያለው ተገቢ ያልሆነ አሠራር መስተካከል እንደሚኖርበት አሳስበዋል፡፡

 

ቅዱስነታቸው በተደጋጋሚ ተገቢ ያልሆነ አሠራር መኖሩ እየተነገረ ዝም ብሎ ማለፍ ስለማይገባ የችግሩን አሳሳቢነት ግምት ውስጥ በማስገባት የቤተ ክርስቲያኗን አሠራርና መዋቅር በተመለከተ ለውጥ ላይ ስለምትገኝ ምእመናንም የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል፡፡አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጠይቀዋል፡፡

 

 

 

 

 

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅራዊ ለውጡን እንደሚደግፉ አስታወቁ

ጥር 9/2006 ዓ.ም.

በእንዳለ ደምስስ

• “የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ቤተ ክርስቲያኗ የምታምንባችሁ፤ እናንተም የቤተ ክርስቲያኒቱ ታማኝ ልጆች እንደሆናችሁ እናምናለን፡፡” /ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ /
• በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ተንሰራፍቶ ያለውን ሙስና፤ ዘረኝነት፤ ብልሹ አሠራሮች አንገታችንን ደፍተን እንድንሔድ አድርጎን ነበር፡፡/የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች/

የአዲስ አባባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሓላፊዎችና አባላት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተንሠራፋውን ብልሹ አስተዳደር፤ ሙስናና ዘረኝነትን ያስተካክላል ተብሎ የተዘጋጀውን አዲሱን መዋቅራዊ ለውጥ እንደሚደግፉ ጥር 8 ቀን 2006 ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሸ ቅዱስ ፓትርያርኩና ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስታወቁ፡፡

ተወካዮቹ በመግለጫቸው “በርካታ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት እስከ እስር ድረስ በመድረስ ሲታገሉለት የነበረውንና አይነኬ የሚመስለውን በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ የተንሰራፋውን ብልሹ አሠራርን እናወግዛለን፡፡ እነዚህን ዘርፈ ብዙ ችግሮችን ለመቅረፍ በሚደረገው ጥረት ውስጥም በግንባር ቀደምትነት እንሰለፋለን፡፡ እስካሁን በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ተንሰራፍቶ ያለውን ሙስና፤ ዘረኝነት፤ ብልሹ አሠራሮች አንገታችንን ደፍተን እንድንሔድ አድርጎን ነበር፡፡ ዛሬ የቤተ ክርስቲያናችን ትንሣኤ ደርሷል፡፡ የጥንቷን ቤተ ክርስቲያናችን ክብር እንደሚመለስልን እናምናለን፡፡ እኛም ከቅዱስነትዎና ከቅዱስ ሲኖዶስ ጎን በመሰለፍ የሚጠበቅብንን ለማበርከት ተዘጋጅተናል” ብለዋል፡፡

የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በሚደረጉ ብልሹና ሥነ ምግባር የጎደላቸው ድርጊቶች ሲፈጸሙ በመጋፈጥ ፊት ለፊት በመናገራቸው አንዳንድ የደብር አለቆችና ጸሐፊዎች በቀጥታ ለፖሊስ በመጻፍ አባላት እየተደበደቡና እየታሰሩ እንደሚገኙ የገለጹት አባላቱ አንዳንድ ፖሊሶችም ጉዳዩን ሳያጣሩ የድርጊቱ ተባባሪ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡ ለዚህም ማሳያነት በአሁኑ ወቅት በደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን ያለውን ችግር በተወካዩ አማካይነት አቅርበዋል፡፡

ከዚህ በፊት በሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አማካይነት ለቅዱስ ሰሲኖዶስ ቀርቦ የነበረውና በእንጥልጥል የቀረው የተሐድሶ መናፍቃንን ጉዳይ በተመለከተ ተጨባጭ መረጃዎችን ማቅረባቸውንና የተወሰኑ ግለሰቦችና ማኅበራት ተወግዘው መለየታቸውን አስታውሰዋል፡፡ ነገር ግን ውሳኔ ሳይሰጣቸው የቀሩ ግለሰቦችና ማኅበራት ስለሚገኙ በቀረበው ማስረጃ መሠረት ጉዳዩ ታይቶ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ እንዲሰጥበትም ጠይቀዋል፡፡

 

መናፍቃኑ በየብሎጎቻቸው ቅዱሳንን እየተሳደቡ እንደሚገኙና በአሁኑ ወቅት የገጠር አብያተ ክርስቲያናትና አብነት ትምህርት ቤቶች ላይ በመዝመት የራሳቸውን መምህራንን በማሰልጠንና በመቅጠር ወረራ እያካሔዱ እንደሚገኙ በመጥቀስ መፍትሔ እንዲፈለግለት አሳስበዋል፡፡

ቅዱስነታቸው በሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ “የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ቤተ ክርስቲያኗ የምታምንባችሁ፤ እናንተም የቤተ ክርስቲያኒቱ ታማኝ ልጆች እንደሆናችሁ እናምናለን፡፡ ምክንያቱም ሰንበት ትምህርት ቤት ዓለማቀፋዊ ነው፡፡ ሁሉም ወጣት በሰንበት ትምህርት ቤት እንዲታቀፍ ነው የምንመኘው፡፡ መበርታት አለባችሁ፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የተደነቀረውን መሠናክል የገንዘብ ብክነት፤ የአስተዳደር ብልሹነትን ለመቅረፍና አማሳኞችን ለመታገል እናንተ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት መዝመት አለባችሁ፡፡ በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ሀብት ባክኗል፤ መልካም አስተዳደር የለም፤ ሸፍጥና ጉቦ ተንሰራፍቷል፡፡ ሃቀኝነት አይታይም፡፡ ይህንን ለመከላከል ትጉ” ብለዋል፡፡
ከቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ውጪ የሚያስተምሩና ችግር የሚፈጥሩ ካሉ በተረጋገጠ መረጃ አስደግፈው ማቅረብ እንደሚገባቸው የገለጹት ቅዱስነታቸው፤ የማኅበራት ደንብን አስመልኮቶ ወጣቱ በአንድ ሕግ፤ በአንድ ሰንበት ትምህርት ቤት መታቀፍ እንዳለበት ጠቅሰው፤ ቤተ ክርስቲያንም ይህንን ጉዳይ ዝም ብላ እንደማትመለከተው አሳስበዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋር በየአጥቢያው የሚፈጠሩ ችግሮች ምን እንደሆኑ መታወቅ እንዳለባቸው በመግለጽ “ለምንድነው የምትታሰሩት? ማነው የሚያሳስራችሁ? ተጽእኖስ ለምን ይደርስባችኋል? ይህ ጉዳይ መጣራት አለበት፡፡ ችግሩ የማነው? ከነማስረጃው አቅርቡ፤ ቤተ ክርስቲያን መፍትሔ ትሰጣለች፡፡ ልጆቿን ዝም ብላ አሳልፋ አትሰጥም” ብለዋል፡፡