የቱን ታስታውሳላችሁ?
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ በሰላም አሸጋገራችሁ! አዲሱን ዓመት ከተቀበልን ሳምንታትን አስቆጥረን ወር ሊሞላን ጥቂት ቀናት ብቻ ቀሩን! አዲሱ የትምህርት ዘመን እንዴት ነው? ትምህርት ጀመራችሁ አይደል? በርቱ!
ታዲያ ልጆች! ቤተ ክርስቲያን በመሄድ መማርንም እንዳንዘነጋ! በሰንበት ሄደን በመማር በሥነ ምግባር ያጌጠ፣ በሃይማኖቱ የጸና ጎበዝ ሆነን ማደግ አለብን፤ መልካም! ለዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው “የቱን ታስታውሳላችሁ” በሚል ርእስ እስከ ዛሬ ትማሩት ከነበረው የተወሰነ ጥያቄዎችን አዘጋጅተን ነው፤ ምላሽችሁን ደግሞ በድረ ገጽ አድራሻችን “website.amharic@eotcmk.org” እና “https://t.me/Hiwot122716” ትልኩልናላችሁ!