ሰባቱ ኪዳናት

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰዎችን ከኃጢአት ባርነትና ከጠላት ቁራኝነት ነጻ ለማውጣት ሲል በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ፣ መከራንና ሥቃይን የተቀበለው እንዲሁም በመልዕልተ መስቀል የተሰቀለው ከሰው በነሣው ሥጋ ሲሆን እኛ የሐዲስ ኪዳን ምእመናን አምላካችን ለሰዎች ድኅነት ያደረገልንን ሁሉ እያሳብን ሐሴት ልናደርግ እንዲሁም በመሠረትልን የእውነት መንገድ ልንጓዝ ይገባል፡፡

ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችን!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! አንድ ነገር ለማወቅ በጣም ጓጓን! ምን መሰላችሁ? ስለ ዘመናዊ ትምህርት ውጤታችሁ! በዚህ ጎበዞች እንደ ሆናችሁ ብናምንባችሁም እንደው የግማሽ ዓመት የፈተና ውጤታችሁ ምን እንደሚሆን እንገምታለን፤ ጥሩ ውጤት እንዳመጣችሁ አንጠራጠርም!

ልጆች! ‹‹ልጅነቴ›› በሚል ርእስ የልጅነት ጸጋን እንዴት እንደምናገኝ ተምረን ነበር፤ አሁን ደግሞ የልጅነት ክብርን ካገኘን በኋላ በሃይማኖት እንዴት መጽናት እንዳለብን እንማራለን፡፡

ሰባቱ ኪዳናት

ሰው በጥንተ ተፈጥሮ ለክብርና ለቅድስና ሕይወት ቢፈጠርም አምላኩ እግዚአብሔርን ክዶ ለጠላቱ ተገዢ ሲሆን ኃያሉ ፈጣሪ በረቀቀ ጥበቡ ሥጋን ለብሶ አድኖታል፡፡ ይህን ቃል የፈጸመበት ጥበቡ ሥጋን መልበስና መከራን መቀበል ነበር፡፡ ለዚህም ድንቅ ሥራው ከሰው ልጅ ከትውልድ ሐረግ መወለድ ስለ ሆነ ቃል ኪዳን ገባለት፡፡ ‹‹ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው›› እንዲል፤ (መጽሐፍ ቀሌሜንጦስ ፪፥፳፫)

በዓለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል

ዑራኤል የሚለው ስም “ዑር” እና “ኤል” ከሚሉ ሁለት ቃላት የተመሠረተ ነው። ዑራኤል ማለት ትርጉሙ “የብርሃን ጌታ”፣ ”የአምላክ ብርሃን” ማለት ነው። ቅዱስ ዑራኤል ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ሲሆን ከፍጥረተ ዓለም ጀምሮ በመብረቅና በነጎድጓድ ላይ የተሾመ መልአክ ነው። ይህም የሆነው በከበረች ዕለት ጥር ፳፪ ነው፡፡

አስተርዮ ማርያም

በዘመነ አስተርዮ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ የሆነበትና የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የተገለጠበት ብቻም ሳይሆን በጥር ፳፩ የከበረች እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት ቀን በመሆኑ “አስተርዮ ማርያም” በማለት በዓልን አናደርጋለን፡፡

የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን

በዓል በሚውልባቸው ዕለታት መደበኛ ሥራዎችን አቁመን ለበዓሉ የሚገቡና መንፈሳዊ በሆኑ ክንውኖች ልናሳልፋቸው የሚጠበቅብን ሲሆን በሥርዓቱ መሠረት ልናከብር ይገባናል።

‹‹ልጅነቴ!››

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን! የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀቱን በዓል እንዴት አሳለፋችሁ? ደስ በሚል ሁኔታ አሳልፋችሁታል ብለን እናስባለን፡፡ ልጆች! ዛሬ ልንነግራችሁ የፈለግነው ስለ ‹‹ልጅነት›› ነው፡፡ ልጅነቴ! ብለን ስንናገር ወይም ደግሞ ስናስብ ብዙ ሊታወሱን የሚችሉ ነገሮች አሉ፤

ቃና ዘገሊላ

በቃና ዘገሊላ ወይም በገሊላዋ ቃና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የፈጸመውን ተአምር በማሰብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በዓል ታከብራለች፡፡ ይህም በጥምቀት በዓል ማግስት በጥር ፲፪ ነው፡፡

‹‹ክርስቶስን የምታስመስለን የከበረች ጥምቀት›› ቅዳሴ አትናቴዎስ

በአዳምና በሔዋን በደል ምክንያት ልጅነታችንን በማጣታችን፣ ሰውን ወደ ቀደመ ክብሩ ሊመልሰው እግዚአብሔር ወልድ ከሰማያት ወርዶ፣ ከንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ፣ ድኅነትን ሊፈጽም ከጀመረባቸው አንዱ እና ዋነኛው የክርስትናችን መግቢያ በር ጥምቀት ነው፡፡

በዓለ አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ

አጋእዝተ ዓለም ሥላሴ በኃጢአት የተገነባውን የሰናዖር ግንብ ያፈረሱበት አንድነታቸውንና ሦስትነታቸውን በግልጽ ያሳዩበት ጥር ሰባት ቀን የከበረ በዓል እንደመሆኑ በቤተ ክርስቲያናችን በድምቀት ይከበራል፡፡