መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!

‹‹ሕፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ ተውአቸው፤ አትከልክሉአቸውም›› (ሉቃ.፲፰፥፲፮)

አእምሯቸው ብሩህ ልቡናቸው ንጹሕ የሆኑት ሕፃናት ተንኮል፣ ቂም፣ በቀል የሌለባቸው የዋሃን ናቸው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕፃናትን ወደ እርሱ እንዲያመጡ አድርጎ መንግሥተ ሰማያትን ለመውረስ እንደ እነርሱ (ሕፃናት) ተንኮል፣ ቂም፣ በቀልን በልቡና መያዝ እንደማያስፈልግ ከክፋት መራቅ እንዳለብን አስተማረባቸው፡፡

ወላጆች እንደ ልማዳቸው ለማስባረክ ሕፃናትን ወደ ጌታችን ሲያመጧቸው ደቀ መዛሙርቱ ‹‹ለምን አመጣችሁ!›› ብለው ወላጆችን በተናገሩ ጊዜ ጌታን ‹‹ተዋቸው›› አለ፤ ደቀ መዛሙርቱ መከልከላቸው ትምህርት ያስፈቱናል (ሕፃናት ናቸውና ይረብሻሉ) በማለት ነው፡፡ ጌታችን ግን እንዲመጡ አደረጋቸው፤ ባረካቸው፤ እነዚህ ሕፃናት ቁጥራቸው ከ፪፻ መቶ በላይ እንደሆነ መተርጉማነ አበው ያብራራሉ፤ በዚያን ጊዜ ከጌታችን የተባረኩት ሕፃናት አድገው ጳጳስ፣ ኤጲስ ቆጶስ ሆነዋል፤ ከፍጹምነት ማዕረግ ደርሰዋል፡፡ (የማቴዎስ ወንጌል አንድምታ ፲፱፥፲፭)

ምሥጢረ ጥምቀት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የትንሣኤ በዓል እንዴት ነበር? ቤተ ክርስቲያን በመሄድ በማስቀደስ አከበራችሁተ አይደል! የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ በዓል የደስታ በዓላችን ነው! በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባቶቻችን በሠሩልን ሥርዓት መሠረት እስከ በዓለ ሃምሣ (ጰራቅሊጦስ) ይታሰባል፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! በሰንበት ትምህርት ቤት በመግባትም ተማሩ አገልግሉ፤ በቤተ እግዚአብሔር ማደግ መታደል ነውና! ሌላው ደግሞ በዘመናዊ ትምህርታችሁም በርቱ! ሁለተኛው የመንፈቀ ዓመት ትምህርት እየተገባደደ ስለሆነ በተማራችሁት መሠረትም ስለምትፈተኑ በርትታችሁ ማጥናት አለባችሁ፡፡ መልካም! አሁን ለዛሬ ወዳዘጋጀንላችሁ ትምህርት እናምራ፤ ባለፈው ምሥጢረ ሥጋዌን ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ  ምሥጢረ ጥምቀትን እንማራለን፤ ተከታተሉን!

‹‹ሰዎች እንዲያደርጉላችሁ የምትፈልጉትን ነገር ሁሉ እናንተም አድርጉላቸው›› (ማቴ.፯፥፲፪)

በሕይወታችን ውስጥ ለአምላካችን እንዲሁም ለሌሎች ፍቅራችንን የምንገልጽበት መንገድ ለራሳችን እንደምናደርገውን ሁሉ ከልብ ከመነጨ ፍቃድ ለባልንጀሮቻችን ማድረግ ነው፡፡ መሠረታዊ ነገሮች እንዲሟሉልን ብቻ ሳይሆን ለምድራዊ ኑሮአችን የሚያስፈልጉንን ሁሉ ስናደረግ እንዲሁ ለቤተ ሰቦቻችን፣ ለወዳጆቻችን፣ ለዘመዶቻችን እና ለጎረቤቶቻችን ማድረግን መርሳት የለብንም፡፡ ይህም ማዕድ ከመጋራት ጀምሮ አብሮ እስከ መቸገር፣ መራቆትና ኅዝንንም ሆነ ደስታን እስከ መካፈል ይደርሳል፡፡

ከራድዮን

ከራድዮን ነጭ ወፍ ሲሆን በሊቃውንቱም ዘንድ የታወቀ ነው። ጠቢባን በድካም ፈልገው አድነው ይይዙታል፤ የታመመ ሰው ቢኖር ያቀርቡታል፤ እርሱም በሽተኛውን ትኩር ብሎ ያየዋል፤ የማይድን ለሞት የቀረበ ከሆነ ፊቱን አዙሮ ይመለሳል፤ ቀኑ ገና ከሆነ ግን አፉን ከፍቶ ከበሽተኛው አፍ እስትንፋሱን ይወስዳል፤ በልዑል እግዚአብሔር ኃይል የሰውየው ደዌ ሙሉ ለሙሉ ወደ ወፉ በእስትንፋሱ ይተላለፋል። ሰውየው ይድናል፤ ወፉ ይታመማል። ፊት ነጭ የነበረው እንደ ከሰል ይጠቁራል፤ ሕመም ሲሰማው ወደ አየር ይነጠቃል፤ ሲብስበት ወደ ባሕር ራሱን ይወረወራል። በባሕር ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ቆይቶ ጠጉሩን መልጦ በዐዲስ ተክቶ፣ ድኖ፣ታድሶ፣ ኃያል ሆኖ ይወጣል። ይህ ፍጥረት በዕለተ ሐሙስ የተፈጠረ ፍጥረታት ነው፡፡ ስለምን ፈጠረው? ቢሉ የወልደ እግዚአብሔር ክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ ለማያምኑ ትምህርት ምሳሌ አብነት ይሆን ዘንድ ይህን ወፍ የማዳን ኃይል ሰጥቶ ፈጥሮታል።

‹‹ታመመ፤ ሞተ፤ ተቀበረ፤ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ›› (የዘወትር ጸሎት)

ጌታ ሰው በመሆኑ የሰውን ልጅ ከኃጢአት፣ ከሞት እና ከሰይጣን ባርነት ነጻ አወጣው። እነዚህ ድል የተነሡትም ፍጹም እስከ መስቀል ሞት በደረሰ መታዘዝ፣ ቅዱስ በሆነ ሕማሙ፣ አዳኝ በሆነ ሞቱና፣ በትንሣኤው ኃይል ነበር።

‹‹እባክህ አሁን አድነን!››

ግሩም አምላክ በትሕትና ከተገለጠባቸው ዕለታት አንዱ የሆነው ድንቅ ቀን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን‹‹ሆሣዕና››በመባል ይታወቃል፡፡ሆሣዕና መተርጉማነ አበው በአንድምታቸው‹‹ሆሣዕና በአርያም በሰማይ ያለ መድኃኒት››ብለው ተርጒመውልናል፤

ምሥጢረ ሥላሴ

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁልን? የዐቢይ ጾምን ከጀመርን እነሆ ሰባተኛው ሳምንት ደረስን! በፍቅር አስጀምሮና አበርትቶ ለዚህ ያደረሰን እግዚአብሔር ይመስገን!… ልጆች!ባለፈው “ሥነ ፍጥረት” በሚል ርእስ ተምረን ነበር፤ ዛሬ ደግሞ ምሥጢረ ሥላሴን ስለምንማር ተከታተሉን!

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን

መጽሔተ ተልእኮ ዘማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን መጽሔቱን ያንብቡ!

መምህር ሆይ!

መሆንህን አውቆ እውነተኛ
ገሰገሰ ወዳንተ በሌሊት ሳይተኛ
ቅዱስ ቃልህንም ሲሰማ ፈወሰው
የታወረ ኅሊናውን አብርቶ አቀናው
ጥያቄውን እንዲያቀርብ አበረታታኸው
ስለ ዳግም ውልደትም አስተማርከው