ሥርዓተ ጸሎት

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች!  እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? የአዲሱ ዓመት የትምህርት ዘመን ከተጀመረ ሁለተኛውን ወር እያጋመስን ነው አይደል? ለመሆኑ ከተማርነው ትምህርት ምን ያህል እውቀት አገኘን? ይህን ለራሳችሁ መጠየቅና መበርታት አለባችሁ!
ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ባለፈው ጊዜ ስለ አጽዋማት መማራችን ይታወሳል! አሁን ደግሞ ስለ ሥርዓተ ጸሎት እንማማራለን፤

የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን

ጸሎት ሰው ከልዑል እግዚአብሔር ጋር የሚነጋገራት ናት፤ የተበደለ ደኃ ከንጉሥ እንዲጮኽ ሰው ወደ ልዑል እግዚአብሔር የሚጮሃት ጩኸት ነች። ባለፈው እያመሰገነ፣ ለሚመጣው እየለመነ፣ የእግዚአብሔርን ጌትነቱን እየመሰከረ፣ በደሉን እያመነ እግዚአብሔርንም እራሱንም ደስ የሚያሰኝባት ጩኸት ናት። “ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ነው” እንዳሉ ፫፻ ምዕት በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የበደለውን ይቅር በለኝ እያለ ለሚጸልይ ሰው ብዙ ሥርዓት አለው።

‹‹ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ›› (መዝ.፹፰፥፫)

ነቢዩ ዳዊት ‹‹ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ፤ ከመረጥኋቸው ጋር ቃል ኪዳን አደረግሁ›› ብሎ እንደነገረን እግዚአብሔር ባዘጋጀላቸው ማረፊያ ሊያኖራቸው ቃል ኪዳን የሰጣቸው ንዑዳን አሉ።(መዝ.፹፰፥፫) የአምላካችን ቃል ኪዳን ፍጻሜው በመንግሥቱ ማኖር ነው። እያንዳንዱ እንደተጠራበት ጊዜና ሁኔታ በተለያየ አኳኋን ጌታውን ቢያገኝም የአምላካችን ስጦታ ግን ለመረጣቸው ሁሉ አንዷ መንግሥተ ሰማያት ናት፡፡ (ማቴ.፳፥፱)

ሥርዓተ ጾም

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? በአዲሱ ዓመት ከአሁኑ ጀምራችሁ መምህራን የሚነግሯችሁን በንቃት ሁናችሁ በመከታተል፣ ያልገባችሁን በመጠየቅ ትናንት ከነበራችሁ ዕውቀት ተጨማሪ ዕውቀትን ጥበብን ልትቀስሙ ያስፈልጋል! ቤተ ክርስቲያን በመሄድም መንፈሳዊውን ትምህርት በመማር በሥነ ምግባር ልትታነጹ ያስፈልጋል፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! አሁን ያለንበት ወቅት ወርኃ ጽጌ ይሰኛል፤ (የአበባ ወቅት ነው)…

‹‹ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሺ፥ ተመለሺ›› (መሓልየ መሓልይ ዘሰሎሞን ፯፥፩)

በብሥራተ መልአክ በድንግልና ፀንሳ በድንግልና የወለደችውን አንድያ ልጇን ሄሮድስ ሊገድልባት በፈለገው ጊዜ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከሀገር ወደ ሀገር መሰደዷን የሚያመለክተውን፣  ከስደትም እንድትመለስ ጠቢቡ በትንቢት ቀድሞ የተናገረው ይህን ቃል ነው፡፡ ወቅቱ አብዝተን ስለ ስደቷና ተያያዥ ታሪኮች የምንማርበት፣ የምንጸልይበት፣ የምናስተምርበትና የምንዘምርበት ወቅት በመሆኑ በዚህ ርእስ ተከታታይ ጽሑፎችን ለማቅረብ እንሞክራለን፤ ተከታተሉን!

የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን

በክርስቶስ ክርስቲያን ተሰኝቶ ክርስቶሳዊ የሆነ ሁሉ የድርሻውን የሚወጣና ሥርዓቱን የሚጠብቅ ከሆነ በዚህ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ክብሯ ልዕልናዋ ተጠብቆ ትኖራለች፣ ረድኤተ እግዚአብሔርና በረከቱ ዘወትር አይለየንም፤ ሀገር ጽኑ ሰላም ትሆናለች፣ በወዲያኛው ዓለምም የዘለዓለምን ርስት መንግሥተ ሰማያትን እንወርሳለን፤ የድርሻችንን የማንወጣና ቸልተኞች የምንሆን ከሆነ ግን የቤተ ክርስቲያንንም የሀገርንም ክብርም ልዕልናም ማስጠበቅ አንችልም፤

‹‹በደስታ በዓልን አድርጉ›› (መዝ.፻፲፯፥፳፯)

ቀናትን ሁሉ ባርኮ የሰጠን አምላካችን እግዚአብሔር ጊዜ የእርሱ ስጦታ በመሆኑ የከበረ ድንቅ ሥራውን ፈጽሞበታል፡፡ በእያንዳንዱ ዕለት ፍጥረታትን ከመፍጠሩ ባሻገር ለምስጋና፣ ለውዳሴ እና ለድኅነት ያከበራቸው በዓላትም አሉት፤ በእነዚህ ዕለታት ቃል ኪዳን አድርጓል፡፡

ቅዱስ መስቀል

ቅዱስ መስቀል ቀስት ከተባለ ጠላታችን ዲያብሎስ እንድናመልጥና ድል እንድናደርገው የተሰጠን ነው፤ ቅዱስ መስቀል መድኅን ዓለም ክርስቶስ ተሰቅሎ በክቡር ደሙ ቀድሶ የሰጠን፣  ሰላማችን የታወጀበት ኃይላችን፣ የሰላም አርማችን ነው!

የቤተ ክርስቲያን በዓላት አከባባር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ አሸጋግሮ በሰላም ለዚህ ዕለት አደረሳችሁ! ዕንቁጣጣሽ እንዴት አለፈ? መቼም ደስ ብሏችሁ እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው!ልጆች! በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን በዓላት እንዴት እንደሚከበሩ እኛም ደግሞ በምን ዓይነት መልኩ በበዓላት ላይ መሳተፍ አንዳለብን ልንነግራችሁ ወደድን፤ መልካም ቆይታ!

የምእመናን ድርሻ በቤተ ክርስቲያን ከምን ይጀምራል?

ቤተ ክርስቲያን የሁላችንም ቤት ናት፡፡ በቤታችን ሁላችንም የሥራ ድርሻ እንዳለን ሁሉ በመንፈሳዊት ቤታችን በቤተ ክርቲያንም እንዲሁ ሁላችንም ድርሻ ሊኖረን ይገባል፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሊቀ ጳጳሳት፣ የካህናት እና በቤተ ክርስቲያን በአስተዳደር ሥራ ላይ የተሠማሩ ሰዎች ቤት ብቻ ሳትሆን የሁላችንም ቤት ናት፡፡