በመንግሥትህ አስበኝ!

በሚያስፈራ ግርማህ በምጽዓት ቀን ስትገለጥ

በፊትህ የሚቆም ጠፍቶ ዓለም ሁሉ ሲንቀጠቀጥ

መልካሙን ዘር ከክፉው አበጥረህ ስትለያቸው

በፍርሃት ያርዳል የጽድቅ ፍሬ ለሌላቸው

ለእኔም ጨንቆኛል ዳግም የምትመጣበት

በደሌ ተቆጥሮ በሥራዬ የምመዘንበት

ዝክረ ግማደ መስቀሉ!

በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን (በ፫፻፳፯ ዓ.ም) የንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እናት ቅድት እሌኒ መስቀሉን ለማግኘት ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች፡፡ ቅድት ዕሌኒ መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን በታሪክ አዋቂው አረጋዊው ኪራኮስ አማካኝነት ዕጣን እንዲጤስ አድረጋ በዕጣኑም ጢስ አመልካችነት መስቀሉን ከተቀበረበት ቦታ ለማውጣት በመስከረም ፲፯ ቀን ቍፋሮ አስጀምራለች፡፡ ንግሥት እሌኒ ከመስከረም ፲፯ ቀን አስጀምራ እስከ መጋቢት ፲ ቀን ሌሊትና ቀን ለሰባት ወራት ያህል የጉድፍን ኮረብታ ቆፍረው ቆሻሻውንም ካስወገዱ በኋላ ሦስት መስቀሎች ተገኙ፡፡ የጌታም መስቀል ሙት በማስነሣቱ ተለይቶ ታውቋል፡፡ መስቀሉ የተገኘው መጋቢት ፲ ቀን ፫፻፳፮ ዓ.ም. ነበር፡፡ በተመሳሳይ መልኩ መስቀሉ ከተቀበረበት ተራራ ተቈፍሮ የወጣበት መጋቢት ፲ ቀንም በቤተ ክርስቲያን በደማቅ ሥርዓት ይከበራል፡፡ በተጨማሪም መስከረም ፲፯ ቀን ንግሥት ዕሌኒ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረችበትን የመታሰቢያ በዓል ታቦት አውጥተው ዑደት በማድረግ በቤተ ክርስቲያን ያከብሩታል፡፡ ከሦስቱ መስቀሎች መካከል ጌታችን የተሰቀለበት መስቀል የተለየው ተአምራት በማድረጉና ብዙ ድውያንን በመፈወሱ ነው፡፡

የበረሓው ኮከብ

በሕግ በሥርዓቱ ተጉዘው፣ ተጋድሏቸውን ፈጽመው፣ ዓለምን ንቀው፣ ከኃጢአት ሥራ ርቀው፣ በጽቅ ሥራ ደምቀው፣ የባሕሪው ቅድስናውን በጸጋ ተቀብለው፣ በቤቱና በቅጽሩ መታሰቢያ ከሰጣቸው አባቶቻችንን መካከል አንዱ ርእሰ ባሕታዊ ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንዱ ናቸው፡፡

“ልትድን ትወዳለህ?” (ዮሐ.፭፥፭)

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የዐቢይ ጾም ሳምንታትን በቅዱስ ያሬድ ስያሜ መሠረት አራተኛውን ሳምንት መጻጉዕ ብላ ታከብራለች። “መፃጉዕ” ማለት “ድውይ፥ በሕመም የሚሰቃይ፥ የአልጋ ቁራኛ” ማለት ነው። ይህንንም ስያሜ እንዴት እንደመጣ ለማየት በዕለቱ የሚነበበውን የወንጌል ክፍል ብንመለከት እንዲህ ይላል። “ከታመመ ሠላሳ ስምንት ዓመት የሆነው አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ ‘ልትድን ትወዳለህ’ አለው። ድውዩም ጌታ ሆይ አዎን! ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም እንጂ፤ ነገር ግን እኔ በመጣሁ ጊዜ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል አለ። ጌታ ኢየሱስም ‘ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ’ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ፤ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ፤ ያም ቀን ሰንበት ነበረ” ይላል። (ዮሐ.፭፥፭-፲)

ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት ሰነበታችሁ? ትምህርት እንዴት ነው? መቼም ከመጀመሪያው የዓመቱ አጋማሽ ትምህርት ውጤታችሁ በመነሣት የበለጠ ጎበዝ ለመሆን እየተማራችሁ እንደሆነ ተስፋ እናደርጋለን! “ብልህ ልጅ ከስሕተቱ ይማራል” እንዲሉ አበው ከትናንት ድክመታችሁ በመማር የበለጠ ውጤታማ ተማሪ ለመሆን መሥራት ይገባል፡፡ ወላጆቻችን እኛን ለማስተማር ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍሉ አስተውሉ! ልጆች የእነርሱ ድካም እኛ መልካምና ጎበዝ እንድንሆን ነውና በርቱ! ለዛሬ የምንማማረው ስለ ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ነው፤ መልካም ቆይታ!

መሠዊያው

በእስራኤል ምድር በሰማርያ ላይ አክዓብ ነገሠ

ጣዖትን አቆመ …መለከትን ነፋ …ለበኣል ደገሠ

የቤተ መቅደሱ መሠዊያው ፈረሰ

የእግዚአብሔር ካህናት ደማቸው ፈሰሰ

ምኵራብ

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የዐቢይን ጾም ሦስተኛ ሳምንት ምኩራብ ብላ ትጠራዋለች። ዓመት እስከ ዓመት ያለውን ይትበሃል በያዘው ድጓ ዐቢይ ጾም በገባ በሦስተኛው ሳምንት መጀመሪያው ቀን ቅድስት በሆነች በሰንበት በሚዘመረው በጾመ ድጓው ክፍል “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሀረ ቃለ ሃይማኖት፤ ጌታችን ኢየሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ፤ የሃይማኖት ቃልን አስተማረ” ሲል እናገኘዋለን።

“ሰውን በአርአያችንና በአምሳላችን እንፍጠር” (ዘፍ.፩፥፳፮)

በዕለተ ዐርብ እግዚአብሔር አራት ፍጥረታትን ፈጠረ፡፡ እነርሱም በእግር የሚሽከረከሩ፣ በክንፍ የሚበሩና በልብ የሚሳቡ፣ በየብስ፣ የሚኖሩ በደመ ነፍስ ሕያዋን የሆኑ ፍጥረታትን ነው፡፡ በመጨረሻም እግዚአ ዓለም ሥላሴ “ሰውን በአርአያችንና በአምሳላችን እንፍጠር” ብለው በነግህ አራቱን ባሕርያተ ሥጋ አምስተኛ ባሕርየ ነፍስን አዋሕደው የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ አድርገው በማዕከለ ምድር በቀራንዮ ፈጠሩት፡፡ (ዘፍ.፩፥፳፮)

ጌታችን ጾመ፤ በዲያብሎስም ተፈተነ (ማቴ.፬)

ጌታችን በገዳመ ቆሮንቶስ ሲጾም “ወቀርበ ዘያሜክሮ፤ ሰይጣን ሊፈትነው ቀረበ” ይላል፡፡ በመጀመያም እንዲህ አለው፤ “እመሰ ወልደ እግዚአብሔር አንተ በል ከመ እላ አዕባን ኅብስተ ይኩና፤ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ በል አለው።” (ማቴ. ፬፥፫) ሰይጣን የመጀመርያውን ሰው አዳም በመብል ድል ነሥቶት ስለነበር በለመደበት ክርስቶስን ድል ሊነሣ መጣ። ይኸውም አብ በደመና “የምወደው ልጄ እርሱ ነው” ሲል ሰምቶ ነበርና ይህን ተናግሯል። (ማቴ.፫፥፲፯) ሰይጣን እንዲህ ያለው በትርጓሜ ወንጌል እንደምናገኘው በአንድ እጁ ደንጋይ ይዞ በሌላ እጁ ደግሞ ዳቦ ይዞ በመቅረብ ነበር። ምን ነው ከያዝከው አንበላም ቢለኝ አዳምን ድል እንደነሣሁት እርሱንም ድል እነሣዋለሁ። ቢያደርገው ደንጋዩን ወደ ዳቦ ቢቀይረው ለሰይጣን ታዛዥ ብየ እዳ እልበታለሁ ብሎ ቀረበ። (የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፫ አንድንምታ ትርጓሜ)

ኪዳነ ምሕረት!

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! እንዴት አላችሁ? የዕረፍት ጊዜ እንዴት ነበር? መቼም ቁም ነገር ሠርታችሁበት እንዳሳለፋችሁ ተስፋችን ነው፡፡ ልጆች! ዛሬ የምንማማረው ስለ እመቤታችን ኪዳነ ምሕረትና ከአምላካችን ስለተሰጣት ቃል ኪዳን ነው፡፡

ውድ የእግዚአብሔር ልጆች! ወር በገባ በ፲፮ኛው (ዐሥራ ስድስት) ቀን “ኪዳነ ምሕረት” ብለን የምናከብረውና የምንዘክረው ታላቅ በዓል አለ፡፡ ይህ በዓል ለምን የሚከበር ይመስላችኋል?