‹‹ሐሰትን አትነጋገሩ›› (ሌዋ.፲፱፥፲፩)
ከሁሉም አስቀድሞ ሰዎች ፈጣሪ እግዚአብሔር የእውነት አምላክ እንደሆነ ልንረዳ ይገባናል፡፡ እርሱ እውነተኛና የእውነት መንገድ እንደሆነ ስንናውቅ መንገዳችን በእውነትና ስለ እውነት ይሆናል፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ›› በማለት እንደተናገረው በሕይወታችን ውስጥ እውነትን ማሰብ፣ እውነትን መናገር እንዲሁም በእውነተኛው መንገድ መጓዝ የሚቻለን አምላካችን እውነተኛ መሆኑንና ሐሰትን እንደሚጠላ ስናውቅ ነው፡፡ (ዮሐ.፲፬፥፮)