?
በዲ/ን እሸቱ
ሚያዝያ 26፣2003ዓ.ም
ሰው ማነው? ብሎ ለጠየቀ “ሰው ንግግሩን ይመስላል” እንዳትለኝ ንግግሩ እምነቱን የሚያመለክት ዕውቀት አይሆነውምና ነው፡፡ ለሰው ባሕርያዊ ተፈጥሮና ዕውቀት ምስክሩ ውስጣዊ የአዕምሮ አቋምና የሕሊና ሕግ ነው ብለንም አንደመድምም፡፡ ሰው እንዲያውቅ የተመደበለት የሕግ ተፈጥሮ ዕውቀት መጀመሪያ ክፍል መልካምን ማወቅ፡፡ ሁለተኛ ክፋትን ንቆ መልካምን ገንዘብ ማድረግ፡፡ ሦስተኛ መልካምን በግብር መግለጽ ናቸው፡፡ የቤተ ክርስቱያን ሊቃውንት ይሁዳን ሲገልጹ “በአፍ አምኖ በልቡ የካደ” ይሉታል፡፡ ባህላችን “አፈ ቅቤ፤ ሆደ ጩቤ” እንዲል፡፡
የክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር መሠረት ያለ ትምህረት በተፈጥሮ የሚሰጥ ሲሆን ይህም ሕገ ልቦና፤ ሕገ ህሊና፤ ሕገ ተፈጥሮ ወይንም ሕገ ጠብዓያዊ በመባል ይታወቃል፡፡ ሕገ ኦሪትና ሕገ ወንጌል፤ ሕገ ሕሊናን ይተረጉማሉ፡፡ ለአብነት ብንጠቅስ አዳምና ሔዋን ቅዱስ ዳዊትና ይሁዳን፤ ከመጸጸት ክፉዎችን ከማዘን የምታደርሳቸው የሕሊና ኮሽታ ነች፡፡ በኑሮ ሂደት ሀዘን፣ ጸጸት ርትዕ በምናደርግበት ጊዜ ልዩ መንፈሳዊ ጥበብ አልያም ዕውቀት በመታደል ሳይሆን ሰው በመሆናችን በሕሊና ውስጥ የተቀረጸ በህሊና ሚዛን የሚሰጥ ፍርድ በመኖሩ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሕገ ሕሊና በጽሑፍ ከተሰጡን ሕግጋት /ሕገ ኦሪት፣ ሕገ ወንጌል፣ ማሕበራዊ ሕግ/ በላይ ሰማያዊና ምስጢርን ለመጠበቅ ሲያገለግል እናገኘዋለን፡፡ የቤተ ክርስቲያን የሀገር የግል ምስጢር ይጠበቅ ዘንድ መንፈሳዊ ሕግና ማህበረሰባዊ ሕግ ይደነግጋል፡፡ የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ያለ ምድራዊ ሕግ አስገዳጅነት በሕገ ልቦና ዳኝነት ለሰማያዊ ምስጢር የታመነች ነበረች “እናቱ ማርያም በልቧ ትጠብቀው ነበር” እንዲል፡፡ /ሉቃ.2÷19/፡፡
“ሰው ራሱ መጽሐፍ ነው” የሚለው የአነጋገር ስልት የሚያስተላልፈው ሰው ይነበባል፤ ይጠናል፤ ይተነተናል ይጸድቃል፤ ይሻራል ለማለት ነው፡፡ እነዚህን ተግባራት ለሌሎችም ሆነ ለራሳችን ለድርጊታችን ብያኔ ፍርድ ለመስጠት ረቂቅ የሕሊና ልጓም እንደ መሠረት ሆኖ ያገለግላል፡፡ ሰው በውስጡ የሚያረጋግጣት እውነት በክበበ አዕምሮ በሚጨበጥ ሕገ ባሕርይ ከመገለፅ እምቢ አትልም፡፡ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት እምነት በቅድሚያ እንዲገኝ ግድ ቢሆንም በተግባር ወይንም በድርጊት ካልተዋሃደ ክርስቲያናዊ ሕይወታችን ፍሬ ቢስ፤ ረብ የሌለው ከንቱ ድካም ይሆናል፡፡ ለመሆኑ እምነታችን ከድርጊታችን ለምን ተዛነፈ? በጽናት የምናምነውን እምነት አጥቦ የመውሰድ ብቃት ያለው ሃይል ይኖር ይሆን? በዕለት ተዕለት ማኅበራዊ መስተጋብር የምንወስናቸው መጠነ ሰፊ ጥቃቅን ውሳኔዎች ውህደ ሃይማኖት ምግባር የታሹ ወይስ የስሜት ውጤቶች ናቸው? እርግጥ ነው ስሜት አልባ ሰብአዊ ፍጡር ሊሆን አይችልም፡፡ ነገር ግን ነፍስን ደስ የሚያሰኝ ሰማያዊ እውነት ከስሜት በላይ ነው፡፡ በገሃዱ ዓለም በብዙዎቻችን ሕይወት የሚታየው ውሳኔዎቻችን በድካም ባካበትነው ዕውቀት፤ መንፈሳዊ አስተምህሮ፤ ዓለማዊ ጥበብ፤ የቅዱሳን ሕይወት ሳይሆን ለስሜት ያጋደለ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ለሁለት ጌታ መገዛት አይቻልም የሚለውን ኃይለ ቃል ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተማረው ይሁዳ ለ30 ብር ሸጦታል ለምን ትለኝ እንደሆን ሰው ክፉን ነገር እስኪሰራ ሰው ልበ ሙሉ ይሆናልና ነው፡፡ ሁለተኛው የህሊና ዓይን ከነፍስ ባይለይም በኃጢአት ምክንያት ይጨልማል ይደክማልና ነው፡፡ በአጭር አገላለጽ ድርጊታችንን የሚቆጣጠረው በዕለቱ ስሜታችንን ያቀጣጠለው ኃይል እንጂ በጥረት ያካበትነው ትምህርት ወይም ዕውቀት ሆኖ አይታይም፡፡ ሰው ሆይ ለምን ይሆን…



ንጉሡ የያዘውን በረከት ወደኢትዮጵያ ሳያደርስ ስናር በተባለው ቦታ ዐረፈ፡፡ ከጊዜ በኋላ የዐፄ ዳዊት ልጅ ዳግማዊ ቆስጠንጢኖስ የተባለው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ተቀብሎ በደብረ ብርሃን፣ በየረር፣ በመናገሻ እና በልዩ ልዩ ተራራማ ቦታዎች ሲዘዋወር ቆይቶ “ መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ አኑር ” የሚል ራእይ ተገልጦለት ቅዱስ መስቀሉን በወሎ ክፍለ ሀገር በአምባሰል አውራጃ በግሸን ደብረ ከርቤ አስቀምጦታል ፡፡ መጋቢት ዐሥር ቀን ደብረ ብርሃን ሲገባ ብርሃን ስለወረደና ዐፄ ዳዊት ከግብፃውያን ጳጳሳት እና ንጉሥ እጅ መስቀሉን የተረከቡበትን ቀን በማዘከር የአድባራት እና የገዳማት ሊቃውንት ልብሰ ተክህኖአቸውን ለብሰው የብር መቋሚያ እና ጸናጽል ይዘው ወደ ነገሥታቱ ሔደው ተቀጸል ጽጌ እያሉ እያሸበሸቡ ጸሎተ ወንጌል ያደርሱ ስለነበር መስከረም ዐሥር ቀን የዓፄ መስቀል በዓል ተብሎ ይከበራል፡፡
ተራራ ያመለከተበት ዕለት መስከረም ዐሥራ ስድስት ቀን በመሆኑ የመስቀል ደመራ በዓል በዚሁ ዕለት ይከበራል፡፡
እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ያለውን እውነተኛ ፍቅር በተለያየ መንገድ አሳይቷል፡፡ ሰማይና ምድር የእርሱ የሆነ አምላክ በከብቶች ግርግም ተወለደ፡፡ የተነገረው ትንቢት የተቆጠረው ሱባዔ ሲያልቅ በመስቀሉ ተፈጸመ ብሎ ሕይወትን በመስጠት ሞታችንን በመውሰድ ፍቅሩን ገለጠ መስቀል ፍቅረ እግዚአብሔርን የሚያሳስበን የስብከታችን ርእስ የኑሮአችን መርሕ ስለሆነ በዓመት አንድ ጊዜ ወይም ሁለት ጊዜ ብቻ ሳይሆን ዘወትር እናስበዋለን፡፡
ቋንቋ ዝማሬና ትርዒት አሳይተዋል፡፡ የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ሰንበት ተማሪዎች ቅድስት እሌኒን በገጸ ባሕርይ ወክለው የመስቀሉን መገኘት አብሥረዋል፡፡ ከዚያም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስና በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ደመራው ተባርኮ ተቀጣጥሏል፡፡ ምእመናን ከመስቀሉ በረከት ለመሳተፍ የደመራውን ዓመድ እንደ እምነት አድርገው በግምባራቸው እየተቀቡ ወደ ቤታቸው ተመልሰዋል፡፡
“ውእቱ ዝንቱ መስቀል ወቦቱ ንትመካህ ከመ ንሰብሖ … እንሰግድለት ዘንድ የምናከብረው፣ እናከብረው ዘንድ የምንመካበት ይህ መስቀል ነው፡፡” /ጸሎተ ኪዳን/ እንደተባለው ሕይወትና ድኅነትን ያገኘንበት የሲኦልን እሳት ተሻግረን ወደ ገነት የገባንበት የአምልካችን ፍቅር የተገለጠበት ዐውድ በመሆኑ መስቀሉን እያሰብን በዓሉን እናከብራለን፡፡


የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል ያዘጋጀው 3ኛው ዓመታዊ የጥናትና ምርምር ጉባኤ ከነሐሴ 28 እስከ 29 ቀን 2003 ዓ.ም በብሔራዊ ሙዚየም አዳራሽ ይከናወናል።