የ2004 የከተራ በዓል አከባበር ከዓድባራቱ እሰከ ጃንሜዳ፡፡
ጥር 11/2004ዓ.ም.
በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ዐበይት በዓላት ተብለው ከሚጠቀሱት መካከል የጥምቀት በዓል አንዱ ነው፡፡ይህንም በዓል ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ፤ በማእከለ ዮርዳኖስ የተጠመቀበትን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ ከዋዜማው ከጥር 10 ጀምሮ በደመቀ ሁኔታ በማክበር ላይ ትገኛለች፡፡ ለእኛ አብነት ይሆነን ዘንድ፤ የእዳ ደብዳቤያችንን እንደ ገል ቀጥቅጦ እንደ ሰም አቅልጦ በደላችንን ይደመስስ ዘንድ ጌታ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይህንን መሠረት በማረድግ በየአብያተ ክርስቲያናቱ የሚገኙ ታቦታት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ በካህናትና ዲያቆናት፤ እንዲሁም በሰንበት ት/ቤቶች መዘምራንና ምእመናን በዝማሬ በመታጀብ በአቅራቢያቸው ወደሚገኘው ታቦት ማደሪያ በማምራት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ በመሔድ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ማምራቱን ያበሥራሉ፡፡ ‹‹ያን ጊዜም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ናዝሬት መጣ ዮሐንስም በዮርዳኖሰ ወንዝ አጠመቀው›› እንዲል፡፡/ማቴ.3፡1/

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መሥራቿን መድኀኔዓለም ክርስቶስን ለዓለም የምትሰብክበት፣ ከእርሱም ያገኘችውን፣ ይህም ዓለም እንደሚሰጠው ያልሆነውን፣ የእግዚአብሔር ልጅነት፣ ሰላም፣ ፍቅርና ትሕትና ለዓለሙ ትሰብክበታለች፡፡ እንዲሁም ለአገራችን በጎ ገጽታን በመፍጠር ረገድ ከተለያዩ አገራት የሚመጡ ጎብኚዎች ተደንቀው የሚያዩትና አንዳንዶች ልባችውን ለእውነት ክፍት ያደረጉ የሚያምኑበት በመስተንግዶው የሚደመሙበት በመሆኑ ሃይማኖታዊ በዓሉን በልዩ ትኩረት ታከብራለች፡፡
ለዚህ በዓል አከባበር ቤተ ክርስቲያን ቅድመ ዝግጅቶችን በማድረግ ታቦታት በሰላም ወጥተው
በሰላም እንዲመለሱ ጉልህ ሚናዋን ትወጣለች፡፡ በዚህ መሠረት በየአጥቢያው የሚገኙ ወጣቶች ከክብረ በዓሉ ቀደም ብሎ ለሓላፊነት በመሰብሰብ ቅዱሳት ሥዕላትን በታቦታት ማረፊያዎች በማዘጋጀት፣ በተለያዩ ኅብረ ቀለማት ያሸበረቁ ጨርቆችን /ባነሮችን/፤ የኢትዮጵያ ባንዲራን በየአብያተ ክርስቲያናቱ አደባባዮች በመስቀል፣ የቤተ ክርስቲያናትን ቅጥርና አስፋልት በማጽዳት፤ለታቦት ክብርን በመስጠት ምንጣፎችን በማንጠፍ በዓሉን ያደምቁታል፡፡
‹‹ያሰባሰበንና ያነሳሳን እግዚአብሔር ነው፡፡ በራሳችን ያደረግነው አንዳችም ነገር የለም፡፡ ይህንን ክብረ በዓል ከዐራት ዓመታት ወዲህ ነው በዚህ ሁኔታ በማክበር ላይ የምንገኘው፡፡ በየወሩ ከእያንዳንዱ አባል ዐሥር ዐሥር ብር በማዋጣት፤ ከምእመናን በመጠየቅ፤ እንዲሁም በጎ አድራጊ ምእመናንን በማነጋገር የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እናሰባስባለን፡፡ ባገኘነው ገንዘብ የኢትዮጵያ ባንዲራን፤ የተለያዩ ኅብረቀለማት ያላቸው ጨርቆችን በ
ማዘጋጀት፤ ምንጣፎችን በመግዛት በቤተ ክርስቲያን ልጅነታችን የበኩላችን እንድንወጣ ከበረከቱ ተሳታፊ እንድንሆን እያገለገልን እንገኛለን›› በማለት ስሜቱን ያካፈለን ከመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስና የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያናት አጥቢያ፤ የስድስት ኪሎ አካባቢ ወጣቶች መካከል አንዱ ወንድም ነው፡፡ በየአጥቢያው ተዘዋውረን የበዓሉን ቅድመ ዝግጅት ለመቃኘት በሞከርንበት ወቅት ያገኘናቸው ወጣቶች የመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ገዳም አጥቢያ ወጣቶች፤ የቅድስት ማርያም ቤዛዊት ዓለም ማኅበር አባላት፤የዐራት ኪሎ አካባቢ ወጣቶች ቤተ ክርስቲያኒቱንና አደባባዮችን በማስጌጥ ሥራ ላይ ተጠምደዋል፡፡ ስለ ዝግጅቱም የተሰማቸውን ሲገልጹ ነበር፡፡ በተጨማሪም ‹‹ከፖሊስ አባላት ጋር በመቀናጀት ቅድመ ዝግጅቶችን በማድረግና በመወያየት አስፈላጊውን ጥበቃ ለማድረግ ተዘጋጅተናል፡፡›› በማለት የገለጹ ሲሆን ባስተላለፉት መልእክትም ወጣቶች የእነሱን አርአያነት በመከተል ቤተ ክርስቲያን ከእነሱ የምትጠብቀውን አገልግሎት እንዲሰጡ እንዲሁም እምነታቸውን አጥብቀው እንዲይዙ ግዴታቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
‹‹ኀዲጎ ተስዐ ወተስዐተ ነገደ››
ምእመናን ከየቤታቸው ለበዓሉ በሚገባው ልብስ አሸብረቀው ወጥተዋል፡፡ እናቶቻችን ከየአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናቱ የሚሰሙትን የሊቃውንት አባቶቻችን ወረብ ተከትልው፣ የታቦታቱን መውጣት በመጠባበቅ እልልታቸውን ያሰማሉ፡፡ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችም ዝግጅቶቻቸውን አጠናቅዋል፣ የዝማሬ ልብሳቸውን ለብሰዋል፡፡ የሻይ የእረፍት ሰዓታቸውን በመጠቀም ከየመሥሪያ ቤታቸው በር ላይ የታቦታትን ማለፍ በእነርሱም መባረክን ዐይናቸው ተስፋ እያደረገች ታቦታቱ የሚመጡበትን አቅጣጫ ያማትራሉ፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን መዘምራንም ለወትሮው በሚታወቁበት፤ እኅቶች በሙሉ ነጭ ልብስ ወንድሞችም በነጭ ልብስና በቀይ ጃኖ ደምቀው የመንግሥተ ሰማያት ሙሽራ መስለዋል፡፡ ዘንድሮ ግን ሁሉንም ያስደመመ ነገር ይዘው ቀርበዋል፡፡ በርካታ ምእምናንን ዐይናቸውን ማመን እንዳልቻሉ ያስታውቃሉ፡፡ ‹‹በውኑ ይሄን ያህል በገና ደርዳሪ አለን?›› የሚሉ ይመስላል፡፡ አንዳንዶቹም በደስታ ፊታቸው እያበራ በተመሰጦ ‹‹እመቤቴ በምልጃሽ መድኀኒቴ ነሽ›› በሚለው መዝሙር ከበገና ደርዳሪዎቹ ጋር ወላዲተ አምላክን ያመሰግናል፤ ይማጸናል፡፡ ቁጥራቸው ወደ 150 የሚጠጋ የቅዱስ ዳዊት የበገና ቤተሰብ አባላት በገናችውን ወድረው ለዝማሬ ማየት በእውነት ልብን በሐሴት ይሞላል፡፡ ዐይንን ሳይነቅሉ ዐሳብን ሣይከፍሉ ለመከታተል ለመዘመርም ያስገድዳል፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርትና ሥልጠና ማእከልን በርቱ ቀጥሉበት ያስብላል፡፡
ከሰዓት በኋላ በነበረው መርሐ ግብር በተለይም በጃንሜዳ ከየአድባራቱ ዐሥራ ሦስት ታቦታት በአንድነት የሚገኙበት በመሆኑ ሕዝቡን ለመባረክ የተገኙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ፕሬዚዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዚዳንት ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ልብሰ ተክህኖ ለብሰው፤ በመዘምራንና ምእመናን በመታጀብ ጉዞ የተጀመረ ሲሆን አመሻሽ ላይ ጃን ሜዳ ሊደርሱ ችለዋል፡፡ የየሰንበት ት/ቤቶቹ መዘምራን፤ የማኅበረ ቅዱሳን መዝሙር ክፍል አባላት ያሬዳዊ ዜማ እየዘመሩ፤ ምእመናን በእልልታና በሸብሸባ ታቦታቱን በማጀብ በዓሉን አድምቀውታል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ከጋዜጠኞች ለቀረበ ጥያቄ ዕለቱን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ ‹‹የዛሬው በዓላችን በሃይማኖታችን ውስጥ የእግዚአብሔርን ጸጋና በረከት የምናገኝበት፤ ሁላችንም በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የምንወለድበት፤ ልጅነት የምናገኝበት በዓል ነው፡፡›› በማለት ገልጸዋል፡፡
በዓሉን በተመለከተ ያነጋገርናቸውና ከፈረንሳይ ሀገር የመጡት ቱሪስት በዓሉን በመገረም እየተከታተሉ ‹‹ወደ ኢትዮጵያ የመጣሁት ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ የራሺያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተከታይ ነኝ፡፡ ኢትዮጵያውያን በጣም የተለያችሁ ናችሁ ማለት ይቻላል ፡፡ እንደዚህ ዓይነት የበዓል አከባበር ዐይቼ አላውቅም፡፡ በጣም አስደሳችና ታላቅ በዓል ነው፡፡ ሕዝቡ በእልልታና በዝማሬ፣ በሽብሸባና በጭብጨባ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ፍጹም አስደሳች ነው፡፡›› በማለት ገልጸዋል፡፡
በሰሜን አሜሪካ የኦሃዮ ስቴት ኮሎምበስ ከተማ የደብረ ሰላም ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት ቀሲስ ያሬድ ገ/መድኅን
ከበዓሉ ተሳታፊዎች መካከል አንዱ የነበሩ ሲሆን ከረጅም ጊዜ በኋላ በሀገራቸው ማክበር በመቻላቸው መደሰታቸውን፤ ወጣቶች ለታቦታቱ ምንጣፍ በማንጠፍ የሚያደርጉት ጥረት እንዳስደነቃቸው የገለጹ ሲሆን፤ በውጭ ሀገር የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን የሚያደርጉት ጥረት በተመለከተ ‹‹እኛ እምነታችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት ጊዜ እየደረሰ ነው፡፡ በውጭው ዓለም አብያተ ክርስቲያናት መተከላቸው፣ በዓላትን በጋራ ማክበራችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ለዓለም ሕዝብ ማስተዋወቅ የጀመርንበት ወቅት እንደሆነ ያሳያል፡፡ እግዚአብሔር ከፈቀደ እነሱም ተጠምቀው የማይመለሱበት፤ የቤተ ክርስቲያን ልጆች የማይሆኑበት ምክንያት አይኖርም ›› በማለት ወደፊት ብዙ መሠራት እንዳለበት ገልጸዋል፡፡
በበዓሉ ላይ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ከውጭ ሀገር በዓሉን ለመከታተል የመጡ እንግዶችና ቱሪስቶች የተገኙ ሲሆን የዓመቱ ተረኛ የሆነው የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን መዘምራን ዕለቱን በማስመልከት ያሬዳዊ ዝማሬ ‹‹ተሰአልከ እግዚኦ ምደረከ ሃሌ ሉያ ወረደ ወልድ እም ሰማያት ውስተ ምጥማቃት በፍስሐ ወበሰላም›› በማለት አቅርበዋል፡፡ በብፁዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገሪማ ሰፋ ያለ ቃለ እግዚአብሔር ተሰጥቷል፡፡ በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ጳውሎስ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ተሰጥቶ ታቦታቱ ወደ ተዘጋጀላቸው ማረፊያ ቦታ ገብተዋል፡፡





ቱሪስቶች ከዓመት ወደ ዓመት ፍሰታቸው እየጨመረ መጥቷል፡፡ ይህም ዝማሜው፣ አልባሳቱ፣ የበዓሉ ድምቀት ፣ የቦታው ሥርዓት ለየት ያለ እንዲሁም በእግዚአብሔር ድንቅ ጥበብ በቅዱስ ላሊበላ የታነጸው ህንጻ ከሊቃውንቱ፣ ሊቃውንቱ ከህንጻው ጋር አብረው የሚታዩና የማይጠገቡ በመሆናቸው እንደሆነ ሊቀ ሥዩማን ገልጸውልናል፡፡


ደብረ ሃይማኖት መካነ ኢየሱስ የሃይማኖት አባቶችን ለሀገሪቱ ከማበርከቱም በላይ በኢትዮጵያ ካቶሊኮች ገብተዉ ከወጡበት የጥንቱ ጊዜ በኋላ መልኩን ቀይሮ የቤተ ክርስቲያን ሊቃዉንትን ሲያበጣብጥ የቆየዉ የቅባትና የጸጋ ሰርጎ ገብ ፈጽሞ ካልረገጣቸዉ የሰሜን ኢትዮጵያ የትርጓሜ ትምህርት ቤቶች አንዱ መሆኑ በሊቃዉንቱ በተደጋጋሚ ተመስክሮለታል፡፡የደብሩ አስተዳዳሪና የድጓ መምህር መልአከ ሃይማኖት ሲሳይ አሰፋ በታሪክ የሚታወሱትን ሊቃዉንት ሲያወሱ የታች ቤት ትርጓሜ መሥራች የሚባሉት መምህር ኤስድሮስ የዚህ ቦታ መምህር እንደ ነበሩና ጣና ገብተዉ መጻሕፍትን መርምረዉ የታች ቤቱን ትርጓሜ ጎንደር ልደታ ላይ ከማስተማራቸዉ በፊት መካነ ኢየሱስ ላይ ተምረዉ ከዚያም ወንበሩን ተረክበዉ ማስተማራቸዉንና በኋላም መጥተዉ በቦታዉ ጥቂት ጊዜያትን ከቆዩ በኋላ እዚያዉ አርፈዉ መቀበራቸዉን አስረድተዋል፡፡ የቦታዉን ታላቅነት አስመልክቶ በሊቃዉንቱ ዘንድ ብዙ የሚነገርለት መሆኑን ያወሱት መልአከ ታቦር ተሾመ ዘሪሁንም በታላቁ ሊቅ የኔታ ገብረ ጊዮርጊስ ከተቀኙት መወድስ ዉስጥ ፤
ነበር፡፡ በዚህም ከአምላኩ ዘንድ ዋጋ አግኝቶበታል፡፡ አንድ ወቅት ያዕቆብ ለላባ “ሃያ ዓመት ሙሉ ከአንተ ጋር ነበርሁ በጎችህና ፍየሎችህ አልጨነገፉም የመንጎችህንም ጠቦቶች አልበላሁም አውሬ የሰበረውን አላመጣሁልህም ነበር፤ እኔ ስለ እርሱ እከፍልህ ነበርሁ፤ በቀንም በሌሊትም የተሰረቀውን ከእጄ ትሻው ነበር፡፡ የቀን ሀሩር የሌሊት ቁር ይበላኝ ነበር ፤ እንቅልፍ ከዐይኔ ጠፋ”(ዘፍ.፴፩፥፴፰-፴፱)ብሎት ነበር፡፡ እናንተ እረኞች ይህን እረኛ ለመንጎቹ ምን ያህል እንዲጠነቀቅ አስተዋላችሁን? በሌሊት እንኳ እነርሱን ለመጠበቅ በትጋት ያለእንቅልፍ የሚተጋ እነርሱንም ለመመገብ በቀን የሚደክም እውነተኛ እረኛ ነበር፡፡
አገልግሎት በአርሲ ሀገረ ስብከት ከኅዳር 29/2004 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 10/2004 ዓ.ም ለ11 ተከታታይ ቀናት በተለየዩ ወረዳዎች አካሔደ፡፡ 27 አባላት የተሳተፉበት ሐዋርያዊ አገልግሎት በተመረጡ 6 ወረዳዎች ውስጥ በሚገኙ ቤተ ክርስቲያናት እንዲሁም በአሰላ ከተማ በተሳካ ሁኔታ የተከናወነ ሲሆን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያፈራቻቸው የማኅበረ ቅዱሳን ሰባኪያነ ወንጌል አማካይነት በአውደ ምሕረት ላይ ለምእመናን ሰፋ ያለ የወንጌል ትምህርት ተሰጥቷል፡፡ በማኅበሩ መዝሙር ክፍል አባላት አማካይነት ከአባቶች እግር ስር ቁጭ ብለው የተማሩትን የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዓትና ትውፊት የጠበቀ ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል፡፡
የኑፋቄ ትምህርት ይጠበቁ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን ዶግማና ቀኖና መሠረት ያደረገ ትምህርት በቀጣይነት እንዲሰጥ፤ እንዳይቋረጥባቸው ተማጽነዋል፡፡ “በሕፃንነቴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እሰማቸው የነበሩ መዝሙራትን እንዳስታውስ አደረገኝ፡፡ እባካችሁ እኛንም ልጆቻችንም ከዳንኪራ ባልተናነሰ በስመ መዝሙር ከሚቀርቡና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ካልጠበቁ ጩኸቶች ታደጉን፡፡” ሲሉ በምሬት ገልጸዋል፡፡ በከፍተኛ ውዥንብር ውስጥ ይከታቸው የነበረው የያሬዳዊ ዜማ አቀራረብ የማኅበረ ቅዱሳን የመዝሙር ክፍል ያቀረበውን ከተመለከቱ በኋላ ትክክለኛውን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ትውፊት የጠበቁትን ለመለየት እንደረዳቸውና ማኅበረ ቅዱሳን እየሰጠ ባለው አገልግሎት መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡ “የማኅበረ ቅዱሳን ዘማርያን በሚዘምሩበት ወቅት በተለይ ሴቶች እኅቶቻችን ሲዘመሩ የሙሴ እኅት ማርያም እስራኤላውያን ባህረ ኤርትራን በተሻገሩበት ወቅት ከበሮ ይዛ እግዚአብሔርን ያመሰገኘችበት ዝማሬ አስታወሰኝ፡፡ ሰናይ እገሪሆሙ ለእለ ይእዜኑ ሰናየ ዜና /ኢሳ.52 እንዲል የምሥራች የሚናገሩ ሰዎች እግሮች አመጣጥ መልካም ነው፡፡ መልካም ዜና የሚናገሩ ናቸውና፡፡”በማለት በአገልግሎቱ በመደሰት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡በተጨማሪም ከየማዕከላቱ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ጋር ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል፡፡


በመሰባሰብ የፈጸመው የቅዳሴ ሥርዓታችን አስቀድሞም በቅዱሳን መላእክት ዓለም የነበረና በምድር ባለች መቅደሱም በምእመናን መሰባሰብ የሚፈጸም ነው፡፡ “እኔ በመካከላቸው እሆናለሁ” ብሎ ደስ የሚያሰኝ ዘላለማዊ ቃል ኪዳን የገባልን ጌታችን፣ “ሁለት ወይም ሦስት በስሜ በሚሰበሰቡበት” በማለት መሰባሰባችን ጸጋና ረድኤቱን እንድናገኝ ምክንያት መሆኑን ነግሮናል /ማቴ.18፥20/ በዚህ ርዕስም የጌታን ቃል በታላቅ ትጋት በፈጸመች ሰማያዊ ሥርዓቷን ከቅዱሳን መላእክት ዓለም ያገኘች፣ የምስጋና ሥርዓቷም በትውፊት ደርሶ ለቤተ ክርስቲየን መሠረት በሆነው በጠንታዊት /በሐዋርያት ዘመን/ ቤተ ክርስቲያን ለምእመናን መሰባሰብ ይሰጥ የነበረውን ትኩረትና ምስጢራዊ እይታ እንመለከታለን፡፡
