Entries by Mahibere Kidusan

ቅድስት ድንግል ማርያም እና ታቦተ ጽዮን – የመጀመሪያ ክፍል

ታቦተ ጽዮን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ስትኾን፣ በውስጧ የያዘችው የሕጉ ጽላትም የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቷ ከማይነቅዝ እንጨት መሠራቷ የእመቤታችንን ንጽሕና የሚያመለክት ሲኾን፣ በውጪም በውስጥም በጥሩ ወርቅ መለበጧ ደግሞ ቅድስናዋንና በሁለት ወገን ድንግል መኾኗን የሚያስረዳ ነው፡፡

ጽላተ ሕጉ ወደ ቤተ ክርስቲያን ተመለሰ

እንደ መጋቤ ሰላም ቀሲስ ሰሎሞን ማብራሪያ ለጽላቱ መገኘትና ወደ መንበሩ መመለስ መነሻ የኾነው አቶ በለጠ ዘነበ የተባሉ የ፹ ዓመት አረጋዊ የተመለከቱት ራእይና ያደረጉት ጥረት ነው፡፡

ጾመ ነቢያት (የገና ጾም)

የነቢያት፣ የሐዋርያት፣ የጻድቃንና የሰማዕታት አምላክ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፣ ከቅዱሳን ነቢያትና ሐዋርያት በረከት እንዲያሳትፈን፤ መንግሥቱንም እንዲያወርሰን ዅላችንም በዚህ በጾመ ነቢያት ወቅት በጾም በጸሎት ተወስነን እግዚአብሔርን ልንማጸነው ይገባል፡፡

ዘመነ አስተምሕሮ

ጌታችን በዚህ ጸሎት ይቅርታ እንድንጠይቀው በማስተማር ይቅር ሊለን እንደሚወድ ቢነግረንም ይቅር ለመባል ግን እኛ የበደሉንን ይቅር ማለታችን የግድ እንደኾነ በግልጽ አስቀምጦልናል፤ «በደላችንን ይቅር በለን» ከማለታችን በፊት «እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል» እንድንል ያዘዘን እኛ ይቅርታ የምናገኘው ሌሎችን ይቅር ስንል ብቻ መኾኑን ለማመልከት ነው፡፡

ንስሐን በአስተርጓሚ

‹‹በጠረፋማው የአገራችን ክፍል የሚኖሩ ወገኖች የሚጠይቃቸው አጥተዋልና ልንደርስላቸው ይገባል›› የሚሉት ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ አብያተ ክርስቲያናትን፣ ማሠልጠኛ ተቋማትንና የአብነት ትምህርት ቤቶችን በየቦታው በማስፋፋት በልዩ ልዩ ቋንቋ ማስተማር የሚችሉ ሰባክያነ ወንጌልንና ካህናትን ማሠልጠን ለዚህ ኹሉ ችግር መፍትሔ እንደሚኾን ጠቁመዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን በዜማ መሣሪያዎችና በልሳነ ግእዝ ያሠለጠናቸውን ፭፻፶ ተማሪዎች አስመረቀ

አቶ ሰይፈ ዓለማየሁ የማኅበሩ ተቀዳሚ ዓላማ የቤተ ክርስቲያንን ትውፊት ሳይበረዝና ሳይከለስ ጠብቆ በማቆየት ለተተኪው ትውልድ ማስተላለፍ መኾኑን ጠቅሰው ‹‹እናንተ ተመራቂዎችም የዚሁ ዓላማ አካል በመኾናችሁ የተማራችሁትን ትምህርት ለሌሎችም ማስተላለፍ አለባችሁ›› ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌላዊ

አርያኖስ በሚባል ንጉሥ ትእዛዝ ጥቅምት ፲፪ ቀን አንገቱን በሰይፍ ተቈርጦ በሰማዕትነት ዐርፏል፤ ምእመናንም ሥጋውን በክብር ቀብረውታል፡፡