Entries by Mahibere Kidusan

በደማቸው እንዳንጠየቅ ሥጋት አለን

በስብከተ ወንጌል ሐዋርያዊ ጉዞ ወቅት የምናስተውለው ችግር በሕዝቦች መካከል ያለው የቋንቋ ልዩነትና በነዚህ ቋንቋዎች ሠልጥነው የተዘጋጁ ልኡካን ማነስ ነበር፡፡ ይህ ችግር ብዙ ማኅበረሰቦችን ከስብከተ ወንጌል ተለይተው እንዲኖሩ ምክንያት ሆኗል፡፡ ከዚህም ሌላ ሕዝቡ በተለያዩ የእምነት ድርጅቶች እንዲወሰድና ከበረት እንዲወጣም ሆኗል፡፡

የዝማሬ መዋሥዕት አድራሾች ተመረቁ

በደረጀ ትዕዛዙ
 
Zimare_Mewasit.JPG
 
በዙር አባ አቡነ አረጋዊ ገዳም የዝማሬ መዋሥዕት ትምህርታቸውን ተከታትለው ተመረቁት ደቀ መዛሙርት ከአቡነ እንድርያስ ጋር

በደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት በላይ ጋይንት ወረዳ ሳሊ በተባለው ቀበሌ የሚገኘው የጽርሐ አርያም ዙር አባ አቡነ አረጋዊ ገዳም ዝማሬ መዋሥዕት ትምህርት ቤት ዐሥራ ሰባት የዝማሬ መዋሥዕት አድራሾችን አስመረቀ፡፡

በአፋር ሰመራ ከተማ የመጥምቁ ዮሐንስ ገዳም ቅዳሴ ቤት ተከበረ

ሎጊያ ወረዳ ማዕከል
    Semera_Kidus_Yohanes_Church.jpg
 
 
 
 
 
 
 
በሰመራ ከተማ የተሰራዉ የቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን

በአፋር ሀገረ ስብከት ሰመራ ከተማ በሀገረ ስብከቱና በአካባቢው ማኅበረሰብ ከፍተኛ ጥረት የተሠራው የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ገዳም መቃኞ ተጠናቆ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ፡፡

ሰንበት ትምህርት ቤቶቹ የልምድ ልውውጥ አደረጉ

በይብረሁ ይጥና

ከሲዳማ ሀገረ ስብከት ሀዋሳ ከተማና አካባቢዋ የተውጣጡ የስድስት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ተወካዮች በአዲስ አበባ የአምስት ሰንበት ትምህርት ቤቶችን እንቅስቃሴ በመጎብኘት የልምድ ልውውጥ አደረጉ፡፡

ዐቢይ ጾም፤ ወደ ትንሣኤ የሚደረግ ጉዞ

ዲ/ን ዘላለም ቻላቸው

አንድ ሰው ለጉዞ ሲነሣ ወዴት እንደሚሄድ ማወቅ አለበት፡፡ በዐቢይ ጾምም እንዲሁ፡፡ ከሁሉም በላይ ዐቢይ ጾም መንፈሳዊ ጉዞ ነው፤ መድረሻውም ትንሣኤ ነው፡፡ ለእውነተኛው መገለጥ ለፋሲካ መሟላት የሚደረግ ዝግጅት ነው፡፡ ስለዚህ በጣም አስፈላጊ የሆነና ስለ ክርስትና እምነታችንና ሕይወታችን በጣም ወሳኝ የሆነ ነገር ስለሚገልጥልን ይህን በዐቢይ ጾም እና በትንሣኤ መካከል ያለውን ግንኙነት ለመረዳት በመሞከር መጀመር አለብን፡፡

የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (አራተኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ   የሕይወት ብርሃን የሚያጠፋው ሞት የተባለው ጠላታችን በመጨረሻው ዘመን በእግዚአብሔር ኃይል አንዲጠፋና ሰውም የማይጠፋና ሰውም የማይጠፋውን የዘላለም ሕይወት እንደሚያገኝ ፣ ተድላ ደስታ ያለበትን መንግሥተ ሰማያትንም እንደሚወርስ በቅዱሳት መጻሕፍት ተገልጿል ፤ በወንጌሉ የምሥራች ቃል ተረጋግጧል፡፡ ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ

የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (ሦስተኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ   ‹‹ ጌታ ማኅየዊ ›› የተባሉት ቃላት ለአምላክ ብቻ የሚሰጡ ናቸው፡፡ ስለዚህም መንፈስ ቅዱስ ‹‹ ጌታ ማኅየዊ ›› መሆኑንና አምላክነቱንም በቅዱሳት መጻሕፍት ቃል በማረጋገጥ ፣ የመንፈስ ቅዱስ ተቃዋሚዎችን የረቱት የጥንቶቹ የቤተ ክርስቲያን አባቶች በአንቀጸ ሃይማኖታቸው ደንግገውልናል፡፡ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ጋር እኩል ስለሆነ ከእነርሱ ጋር ልንሰግድለትና ልናመሰግነው እነደሚገባን አስተምረውናል፡፡ ሙሉውን […]

የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (ሁለተኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ   ሰው ባጠፋው ጥፋት ከደስታ ሕይወት ወጥቶ፣ ከክብሩ ተዋርዶና ወድቆ በችግርና በመከራ ኖሮ በመጨረሻ ሥጋው በመቃብር በስብሶ ሲቀር፣ ነፍሱ ደግሞ በሲዖል ስትሠቃይ በማየቱ ወልደ እግዚአብሔር ሰውን ከዚህ ክፉ ነገር ለማዳን ሰው ሆኖ ሕማምና ሞትን ተቀብሎ እንዳዳነው እናምናለን፡፡ ሙሉውን እዚህ በመጫን ያንብቡ

የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (አንደኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ እግዚአብሔር አምላክ የሁሉም አባት ነው መባሉ እርሱ ለፍጥረታት ሁሉ ማለት ለዓለም ሁሉ ሠራኢና መጋቢ ፣ ለሕዝብና ለአሕዛብ ሁሉ መሪና ጠባቂ በመሆኑ ነው፡፡ ‹‹እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና በጻድቃንና በኃጢያተኞችም ላይ ዝናቡና ያዘንባልና››(ማቴ.5፣45)፡፡ እርሱ የሰማይ ወፎችን ይመጋባቸዋል ፤ የሜዳ አበቦችንና የሜዳውን ሣር ሁሉ በልዩ ልዩ ኅብረ ቀለም ያስጌጣቸዋል ፣ ያለብሳቸዋልም […]