የክርስትና መሠረተ እምነት በጸሎተ ሃይማኖት (ሁለተኛ መጽሐፍ)

በሊቀ ጉባኤ አባ አበራ በቀለ
 
ሰው ባጠፋው ጥፋት ከደስታ ሕይወት ወጥቶ፣ ከክብሩ ተዋርዶና ወድቆ በችግርና በመከራ ኖሮ በመጨረሻ ሥጋው በመቃብር በስብሶ ሲቀር፣ ነፍሱ ደግሞ በሲዖል ስትሠቃይ በማየቱ ወልደ እግዚአብሔር ሰውን ከዚህ ክፉ ነገር ለማዳን ሰው ሆኖ ሕማምና ሞትን ተቀብሎ እንዳዳነው እናምናለን፡፡