Entries by Mahibere Kidusan

የመነኮሳት አባቶች የጋራ መኖሪያ ቤት ተመረቀ

በደረጀ ትዕዛዙ
 
debre_Tsege.jpgበ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ሀገረ ስብከት በደብር ቅዱስ ደብረ ጽጌ ቅድስት ማርያም ገዳም የተሠራው የአረጋውያን አባቶች መነኮሳት የጋራ መኖሪያ ቤትና መጦሪያ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡መንፈሳዊ ዕውቀት ሀብታቸውን ሲያካፍሉ የኖሩ አባቶችን ለመንከባከብ የተደረገው ጥረት የሚያስመሰግን መሆኑን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ተናገሩ፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በገዳሙ ተገኝተው የመነኮሳቱን መኖሪያ ሕንፃ መርቀዋል፡፡

 

«በአዳም ምክንያት ሁላችን እንደምንሞት፣ እንዲሁም በክርስቶስ በኲርነት ሁላችን እንነሣለን፡፡» 1ኛ ቆሮ. 15፥22

                            ክፍል አራት

በጸጋ እግዚአብሔር አምላኩ የከበረ ይህ ሐዋርያው ጳውሎስ ትምህርቱን የበለጠ ተቀባይነት ያለው ለማድረግ  ብርሃነ እግዚአብሔር ኦሪትን ለሐዲሱ ምስክር እያደረገ ያስተማምናል፡፡ስለሆነም «ነሥአ መሬተ ወገብሮ ለእጓለ እመሕያው ወነፍሐ ላዕሌሁ መንፈሰ ሕይወት፤እግዚአብሔር አዳምን ከምድር ዐፈርን ወስዶ ፈጠረው፡፡ የሕይወትንም እስትንፋስ አሳደረበት፡፡»ብሎ መጽሐፍ እንደተናገረ በዚች ነፍስ ሕይወትነት የሚኖር ሥጋ አስቀድሞ መፈጠሩን ይገልጽና፤ከትንሳኤ ዘጉባኤ በኋላ ግን መንፈስ ቅዱስ ሕይወት ሆኖት የሚኖር ሥጋ እንደሚገኝ /እንደሚነሳ/ ለአጽንዖተ ነገር ደጋግሞ ይናገራል፡፡ ዘፍ 2÷7

የኅዳር ጽዮን በዓል አከባበር ዛሬም ቀጥሎ በድምቀት ተከብሯል።

ዲ/ን አሉላ መብራቱና በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ

ኅዳር 20 ቀን ከዋዜማው ጀምሮ መከበር የጀመረው የኅዳር ጽዮን በዓል ዛሬም ቀጥሎ በድምቀት ተከብሮ ውሏል።

ከትናንትና ማታ 2፡00 ደወል ከተደወለበት ጀምሮ፥ ሊቃውንት ካህናትና ዲያቆናት  ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በስብሐተ ማኅሌት በማድረስ ሌሊቱን አሳልፈዋል።

አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል

በሰሙነ ሕማማት ጠቅለል ባለ መልኩ የምናስባቸው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሕማማት አሥራ ሦስት ናቸው፡፡ እነርሱም አሥራ ሦስቱ ሕማማተ መስቀል ይባላሉ፡፡ ለክርስቲያኖች እነዚህን ሕማማተ መስቀል ማወቅና ዘወትር ማሰብ ተገቢ በመሆኑ እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡

የቤተክርስቲያን ፈተና እና ምዕመናን

በዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ

መግቢያ

የቤተክርስቲያን ታሪክ የሚጀምረው ከዓለመ መላእክት ነው፡፡ ታዲያ ፈተና ሁሌ አብሯት የሚኖር ቤተክርስቲያን መፈተን የጀመረችው በዚሁ በዓለመ መላእክት ነበር፡፡ ዲያብሎስ ትዕቢትንና ሐሰት ከራሱ አንቅቶ መላእክትን «እኔ ፈጠርኋችሁ» በማለት ባሰማው የሐሰት አዋጅ ከሰው ልጅ ወደዚህ ምድር መምጣት ጀምሮ በብሉይ ኪዳንም በርካታ ፈተናዎች ተፈራርቀዋል፡፡

ዝክረ ልሳነ ሰብእ ቀዳማዊ

1. ግእዝ ምስለ ቤተ ክርስቲያን

ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ዘመናት የፈተና ገፈታ ቀማሽ በመሆን፣ ልጆቿን እያበረታታች ለሀገራዊ ሀብት መጠበቅም እስከ ሰማዕትነት እያበረከተች በየአድባራቱና ገዳማቱ ጠብቃ አሳድጋ ለዚህ ትውልድና ዘመን ካቆየቻቸው ዕሤቶች አንዱ ግእዝ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ቤተ መዘክር፣ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤት፣ ቤተ ክርስቲያን ግምጃ ቤት፣ ቤተክርስቲያን የሥልጣኔ ማዕከል፣ ቤተ ክርስቲያን ከተማ ሀገር በመሆን ስታገለግል ቆይታለች፡፡

በዓለም እያሉ ከዓለም ውጪ መኖር

በዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በበሳል ትምህርቱ በመንፈሳዊ ጥብዐቱና በፍጹም መንፈሳዊ ሕይወቱ በቤተ ክርስቲያናችን የታወቀ አባት ሲሆን ኑሮውም የብህትውና ነበር። ካስተማራቸው በርካታ ትምህርቶቹ መካከል ውስጥ አንድ ክርስቲያን በምድር ሲኖር ሰማያዊውን ሕይወት እንዲኖር ነው። ይህንንም ያስተማረበትን ትምህርት እንዲህ አቅርበነዋል፡፡

ቅዱስ ሲኖዶስ

በዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ
«አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት»
kidusSinodos.jpg
በተነገረው ትንቢት በተቆጠረው ሱባዔ ጌታ በሚያውቃት ዕለት ይህች ዓለም ታልፋለች፡፡ እንደ ቅዱስ መጽሐፍ አስተምህሮ ይህ ዓለም ካለፈ በኋላ የማይጠፋ እና የማይለወጥ የዘለዓለም መኖሪያ የሆነ ሌላ ዓለም ደግሞ አለ፡፡ ያም የእግዚአብሔር መንግሥት ነው፡፡ የሰውን ልጆች ለእግዚአብሔር መንግሥት የምታበቃው እውነተኛዋ ፍኖት ደግሞ ክርስትና ናት፡፡ /ኤር 6.16/ እርሷም አንዲት ናት፡፡ የተሰጠችውም ፈጽማ አንድ ጊዜ ነው፡፡ /ይሁዳ 1-3/

ቤተ ክርስቲያን

በዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ

ቤተ ክርስቲያን ሦስት ትርጉም ያለው በዘርፍና በባለቤትነት የተቀመጠ ስም ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያን ስንል የክርስቲያኖች መገናኛ መሰብሰቢያ በዓት ማለት ነው፡፡ይህም ክርስቲያኖች በአንድነት የሚጸልዩበት፣ የሚሰግዱበት፣ ሥጋ ወደሙን የሚቀበሉበት፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚገናኙበት ቦታና የጸሎት ቤት ማለት ነው፡፡(ኢሳ. 56፥7 ፣ ኤር. 7፥10-11 ማር. 11፥17 ሉቃ.19፥46 ) የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች የራሳቸው የጸሎት ቤት በተወሰነ ቦታ አላደረጉም፣ የተለየ ሕንጻ አላሰሩም ነበር፤ ነገር ግን ወደ አይሁድ ቤተ መቅደስ በመሄድ ይጸልዩ ነበር፡፡እንዲሁም በግል የክርስቲያን ቤቶች በተለያዩ ክፍሎች እየተገናኙ ይጸልዩ ቅዱስ ቁርባንን ያዘጋጁ ነበር፡፡ክርስትና እየተስፋፋና እየታወቀ ከሄደ በኋላ ቤተ ክርስቲያንም በፊልጵስዩስ ለመጀመሪያ ጊዜ በጌታችን ፈቃድ ከተሰራ በኋላ ክርስቲያኖች ሥጋ ወደሙን የሚቀበሉት በቤተ ክርስቲያን ብቻ መሆን ጀመረ፡፡ ከዚያ በፊት የነበሩ ምኩራብና መቅደስም አገልግሎታቸውን ለቤተ ክርስቲያን አስረከቡ፡፡