Entries by Mahibere Kidusan

ግእዝ ከእስያ ልሳናት ጋር ሲነጻጸር

በዓለም የሥነ ልሳን ጥናት መሠረት የአካድ /የአሦር – አካዳውያን/ ቋንቋ ጥንታዊ ማንነቱ የተረጋገጠው በአንዳንድ የሥነ ጽሑፎች ቅሪት ሲሆን ይህ ቋንቋ በሥነ ልሳን ተማራማሪዎች ዘንድ የምሥራቅ ሴማዊ ልሳን ተብሎ በቅርብ ጊዜ ከተገኘው ከኤብላዊ ቋንቋ ጋር የሚመደብ ነው፡፡ አካድ እና አሦር በመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል በኦሪት ዘፍጥረት የተገለጹ እና ከኖኅ ዘመን በኋላ የታወቁ መካናተ ሥልጣኔ ናቸው፡፡ በሥነ ጽሑፍ መረጃ የአከድ ልሳን 2500 ቅ.ል.ክ. እንደነበረ ይናገራል፡፡ በኋላ በአራም የአራማውያን የተባለው ቋንቋው ራሱን የገለጸበት ጊዜ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በሥነ ቅሬተ ምድርም ሆነ በሥነ ልሳን ተመራማሪዎች ዘንድ አካድ የኢኮኖሚ፣ የሕግ የአስተዳደር፣ የታሪክና የሥነ ጽሑፍ መረጃዎች እንደነበረው የተረዳ ነው፡፡


‹ትውልድ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቃል ተመልከቱ› /ኤር 2፥31/

ዲ/ን ብርሃኑ አድማ
‹አንድ ምድራዊ ንጉሥ ወይም ጠቅላይ ሚኒስቴር ወይም ሌላ ታላቅ ባለሥልጣን ደብዳቤ ቢጽፍልን በደስታ አናነበውምን? በእርግጠኝነት በታላቅ ደስታ የማያነበውና በልዩ ትኩረት የማይመለከተው አይኖርም፡፡ ይሁን እንጂ ከምድራዊ ባለሥልጣን እንዲህ ያለ ደብዳቤ የተጻፈለት ሰው የለም፤/ለሥራ፣ ለሹመት፣…ካልሆነ በቀር/ ከሰማያዊው ንጉሥ ግን ያልተጻፈለት የለም፣ በምድራዊ ዋጋ የማይታመን ለሕይወት መድኃኒት የሆነ ደብዳቤ ተጽፎልን ነበር። ይሁን እንጂ ለአንድ ምድራዊ ንጉሥ ደብዳቤ የምንሰጠውን ያህል ክብርና ትኩረት እንኳን አልሰጠነውም፡፡

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም(ክፍል ሁለት)

ዲ/ን ዮሐንስ ልሳነወርቅ

ከክፍል አንድ የቀጠለ

በቅዱስ ኤፍሬም ሥራዎች ላይ በሚያጠነጥነውና የሚያበራ ዐይን በሚል ርእስ ሰባስቲያን ብሩክ ካዘጋጀው  መጽሐፍ የተገኘው እንዲህ ተተርጉሞ ቀርቦአል። መልካም ንባብ

በዚህ ክፍል ውስጥ የምናየው ፈጣሪና ፍጡር፣/የተሰወረውና የተገለጠው/ሁለቱ ጊዜያትና ነጻ ፈቃድ በሚሉት ርእሶች ስር ቅዱስ ኤፍሬም በግጥም ያቀረበውን ትምህርት ነው።የቅዱስ ኤፍሬም መዝሙራት ከሚያጠነጥኑባቸው ርእሰ ጉዳዮች አንጻር ስያሜ ተሰጥቶአቸዋል። ለምሳሌ በእምነት ዙሪያ የጻፈውን -Faith ፣በቤተ ክርስቲያን ዙሪያ የጻፈውን -Church የሚል ሲሆን ፤በዚህ ጽሑፍም እነዚህ  በእያንዳንዱ መዝሙር ስር ተጠቅሰዋል።

አሥሩ ትእዛዛት

  እመቤት ፈለገ
እግዚአብሔር አምላካችን እጅግ በጣም የሚወደን እና የሚያስብልን አባታችን ነው፡፡ እርሱ ደግሞ ሁሉንም የሚያውቅ ስለሆነ ለእኛ ምን እንደሚጠቅመን፤ምን እንደሚያስፈልገን፤ምን እንደሚጎዳን ሰለሚያውቅ አሥሩን ትእዛዛት ሰጠን፡፡

በጎ ያልሆኑ ተጽእኖዎች በክርስትናችን

በማሞ አየነው
 
በተደጋጋሚ ከሚያጋጥሙኝ ክስተቶች አንዱ ይህ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ከምተዋወቀው አንድ ልጅ ጋር ቁጭ ብለን እየተጨዋወትን ነው፡፡ ልጁን የማውቀው ሰ/ት/ቤት ውስጥ ታታሪ አገልጋይ በነበረበት ጊዜ ነበር፡፡ አሁን ከመንፈሳዊ አገልግሎቱ ራሱን አግልሏል፡፡ እንደድሮው ስለመንፈሳዊ ሕይወቱ የሚያወያየው ለአገልግሎት የሚጋብዘው፣ ሲደክም የሚያበረታው፣ ሲሰለች መንፈሱን የሚያድስለት፣ ጓደኛ የለውም፡፡

ሠለስቱ ደቂቅ

በአዜብ ገብሩ
እንደምን ሰነበታችሁ ልጆች?ደህና ናችሁ ልጆች? ዛሬ ስለ ሦስቱ ህጻናት ታሪክ እንነግራችኋለሁን በደንብ ተከታተሉን እሺ፡፡
 

በአንድ ወቅት በባቢሎን ከተማ የሚኖር ናቡከደነፆር የሚባል ንጉሥ ነበር፡፡ይህም ንጉሥ ከወርቅ የተሰራ ትልቅ ጣኦት አሠርቶ አቆመ፡፡ ሕዝቡንም ሁሉ ሰበሰበና ለጣኦቱ እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ ለጣኦት ያልሰገደ ግን በእሳት ውስጥ ይጣላል ብሎ አዋጅ አስነገረ፡፡

Silestu Dekik.jpg
 
ከሕዝቡም መካከል ሚሳቅ፤ሲድራቅ እና አብደናጎም የተባሉት ህፃናት ግን ለጣኦቱ አንሰግድም አሉ፡፡ምክንያቱም እግዚአብሔርን ስለሚወዱ ለእርሱ ስለሚገዙ ነው፡፡ንጉሡ እነዚህን ህጻናት ለጣኦቱ አንሰግድም በማለታቸው በጣም ተቆጣ፡፡ካልሰገዱም ወደ እሳት እንደሚጣሉ ነገራቸው፡፡ህጻናቱም የሚያመልኩት አምላክ በሰማይ እንዳለና እርሱም ከእሳቱ እንደሚያድናቸው ነገሩት፡፡እንዲህም ሲሉ ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ ‹‹አንተ ከእኛ ጋር ነህና ክፉውን አንፈራም››። ንጉሡም በመለሱለት መልስ ይበልጥ ተቆጣ፡፡ እሳቱንም ይነድ ከነበርው ሰባት እጥፍ እንዲያነዱትና ወደ እሳቱ ውስጥ እንዲጥሏቸው አዘዘ፡፡

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም(ክፍል አንድ)

ዲ/ን ቀለመወርቅ ሚደቅሳ

በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የረጅም ዘመን ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ በጎ ተፅዕኖ ካላቸው የአራተኛው መ/ክ/ዘመን አባቶች መካከል አንዱ ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም ነው፡፡ይህ አባት ምንም እንኳን በቋንቋ ውሱንነትና በቦታ ርቀት በርካቶች ሥራዎቹና ጽሑፎቹ የታወቁለት ባይሆንም ሕይወቱን በብሕትውና የመራ የትርጓሜ መጻሕፍትን ፣የቅኔ፣ የግጥምና የወግ ጽሑፍ በማዘጋጀት የኖረ ባለ በጎ ገድል አባት ነው፡፡

ታቦት

ትምህርት ሃይማኖት (የሃይማኖት ትምህርት) በሁለት ይከፈላል፡፡ ይኸውም፦
1ኛ፡- ዶግማ   2ኛ፡- ቀኖና በሚል ነው፡፡
ዶግማ፡- ቃሉ የግሪክ ሲሆን ፍችውም እምነት ማለት ነው፡፡

ቀኖና፡- ደግሞ ቃሉ የግሪክ ሲሆን ሥርዓት ማለት ነው፡፡ ከእነዚህ ከሁለቱ ዶግማ ወይም እምነት አይጨመርበትም፤ አይቀነስበትም፤ አይሻሻልም፤ ችግርና ፈተናም ቢመጣ እስከ ሞት ድረስ አጥብቀን የምንይዘው ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የፈጠረ፤ ቢመረምር እንጂ የማይመረመር ሁሉን ቻይ አምላክ፤ የሚሳነው ነገር የሌለ ፈጣሪ፤ የሰማይና የምድር ባለቤት የሠራዊት ጌታ ሕያው እግዚአብሔር ነው፡፡