አሥሩ ትእዛዛት

  እመቤት ፈለገ
እግዚአብሔር አምላካችን እጅግ በጣም የሚወደን እና የሚያስብልን አባታችን ነው፡፡ እርሱ ደግሞ ሁሉንም የሚያውቅ ስለሆነ ለእኛ ምን እንደሚጠቅመን፤ምን እንደሚያስፈልገን፤ምን እንደሚጎዳን ሰለሚያውቅ አሥሩን ትእዛዛት ሰጠን፡፡

 እነዚህም፡-
          1.ከኔ በቀር ሌሎችን አማልክት አታምልክ
          2.የእግዚአብሔር አምላክህን ስም በከንቱ አትጥራ
          3.የሰንበትን ቀን አክብር
          4.አባትና እናትህን አክብር
          5.አትግደል
          6.አታመንዝር
          7.አትስረቅ
          8.በሐሰት አትመስክር
          9.የባልንጀራህን ቤት አትመኝ
         10.ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ የሚሉት ናቸው፡፡

 

እነዚህ ትዕዛዞች ሁሉም ሰው እንዲያደርጋቸው ርህሩህ አባታችን እግዚአብሔር አዞናል፡፡ እነዚህ ትዕዛዞችን ከፈጸምን እግዚአብሔር ይወደናል፤በረከትም ይሰጠናል፡፡
ልጆች እግዚአብሄርን እንወደዋለን አይደል? እግዚአብሄርን መውደዳችን የሚታወቀው ደግሞ አድርጉ ያለንን ስናደርግ፤ አታድርጉ ያለንን ደግሞ የማናደርግ ከሆነ ነው፡፡ይህን ካደረግን እግዚአብሔር በእኛ ደስ ይለዋል፤ ይባርከናል፤የሚያስፈልገንን ሁሉ ይሰጠናል፡፡ እነዚህ ትዕዛዛት ካልፈጸምን  ግን እግዚአብሔር ያዝንብናል፤ ከደጉ አምላካችንም እንለያያለን፡፡ ከአምላካችን ከተለየን ደግሞ ጥሩ ነገር አይኖረንም፡፡ ስለዚህ ልጆች እነዚህን ትእዛዛት ልንፈጽማቸው ስለሚገባ እያንዳዳቸውን በዝርዝር በሌላ ቀን እናያቸዋለን፡፡

በሌላ ቀን አሥሩን ትዛዛት በዝርዝር እስከምናያቸው ድረስ እናንተ በቃላችሁ ይዛችሁ ለእማማ፤ ለአባባ እና ለጓደኞቻችሁ ንገሯቸው፡፡