Entries by Mahibere Kidusan

የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ በርባናስ አረፉ

በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
ግንቦት 21/2003 ዓ.ም.
Abune Bernabas.jpgከሃያ ዓመታት በላይ ቤተ ክርስቲያንን በጵጵስና በቅንነት ያገለገሉት የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ በርናባስ አረፉ፡፡

ርክበ ካህናትን ተከትሎ የሚደረገውን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ለመካፈል ወደ አዲስ አበባ መጥተው በነበሩበት ወቅት ታመው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚህም ሳቢያ የምልዐተ ጉባኤውን የመጨረሻውን ቀን ማለትም የማክሰኞ ዕለት ስብስባ አልተካፈሉም፡፡ በዚህም ሁኔታ አርብ ግንቦት 19 ቀን 2003 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ተነስተው የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከሆኑት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ጋር ደብረ ማርቆስ ገብተው ያደሩ ሲሆን ወደ ሀገረ ስብከታቸው መቀመጫ ባሕር ዳር  ቅዳሜ 8፡00 ሰዓት ገብተው በመዋል ማታ 1፡30 ላይ እንዳረፉ ታውቋል፡፡

አባታችን ሆይ(የመጨረሻው ክፍል)

 ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
አቤቱ ወደፈተና አታግባን÷ ከክፉ አድነን እንጂ÷ መንግሥት ያንተ ናትና÷ ኃይል ክብር ምስጋና ለዘለዓለሙ አሜን።
ግንቦት 19/2003 ዓ.ም.

ጌታችን በዚህ ቃል የእኛን ደካማነት በማሳወቅና መታበያችንን በማጥፋት ፣ ፈተናዎች በእኛ ላይ ከመሠልጠናቸው በፊት  በትሕትና በመገኘት ልናርቃቸው እንደምንችል በግልጽ አስተማረን ፡፡ በዚህ ምክንያት ድላችን እጅግ ታላቅ ይሆናል ፡፡ ሰይጣን ከፊት ይልቅ በታላቅ ፍርሃት ውስጥ ይወድቃል ፡፡ እንዲህ ስል ለጸሎት በእግዚአብሔር ፊት ስንቀርብ በማስተዋል ልንሆን ይገባናል ሲል ነው  ፡፡ ልቡናችንን ሰብስበን መጸለይ ከተሣነን ግን ዝም ማለትን በመምረጥ የፈተናው ጊዜ እስኪያልፍ ድረስ በትዕግሥት ልንጠባበቀው ይገባናል ፡፡  እንዲህ ካደረግን ከከንቱ ውዳሴና ከትዕቢት ነጻ እንደወጣን ማስተዋል ይቻለናል ፡፡

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም (ክፍል አራት)

በዲ/ን ዮሐንስ ልሳነወርቅ

ከክፍል ሦስት የቀጠለ

  7. የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉም (The interpretation of Scripture)

(ግንቦት 19/2003 ዓ.ም)

ለቅዱስ ኤፍሬም ስለ እግዚአብሔር የሰው ልጅ እውቀት ቀዳሚ ምንጩ በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱ  ስለ ራሱ እንዲባል  የፈቀደውን ነው። የእግዚአብሔር ስሞችና በቅዱስ መጽሐፍ ያሉ የተለያዩ ዓይነቶችና ምሳሌዎች በእግዚአብሔርና በሰውነት መካከል መገናኛ ነጥብን ይፈጥራሉ፤እግዚአብሔር በፈጣሪ ትሕትናው የሰው ልጅ ሊረዳው ወደ ሚችለው ደረጃ ራሱን ዝቅ አደረገ። በሰው ልጅ በኩል በእግዚአብሔር የተሰጠውን ራሱን ወደማወቅ ወደሚወስደው መንገድ የመቅረብ ዕድል ለመጠቀም ከተፈለገ ሁለት ነገሮች አስፈላጊ ናቸው፤በመጀመሪያ ደረጃ ቀድመን እንደተማርነው በመጽሐፍ ቅዱስ ፈጽሞ ለእግዚአብሔር የተጠቀመባቸው ስሞችንና ስእላዊ አገላለጾችን ጥሬ ትርጉም በመውሰድ ያልተገባን ስህተት  ልንፈጽም አይገባም፤በሁለተኛ ደረጃም የአንባቢው ዝንባሌ የመቀበልና ቀናነት መሆን አለበት። ቅዱስ መጽሐፍን በተሳሳተ ዝንባሌ ወይም በራሱ ግንዛቤ የሚቀርብ ከሆነ ከመጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ምንም ዓይነት እውቀት ለማግኘት ይሳነዋል ብቻ ሳይሆን ወደ ኃጢአትም ሊገባ ይችላል።

የተዛባ አመለካከት አገልግሎታችንን አያደናቅፈውም

ግንቦት 16፣2003ዓ.ም

 
በእግዚአብሔር ፈቃድ በቅዱስ ሲኖዶስ ይሁንታ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለመደገፍና ለማጠናከር የተመሠረተው ማኅበረ ቅዱሳን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ አያሌ ፈተናዎችን እያሳለፈ 19 ዓመታት ተጉዟል፡፡

ወርቅ ሠሪው ጴጥሮስ(ለሕፃናት)

በእመቤት ፈለገ

ልጆች እንደምን ሰነበታችሁ? ዛሬ ይዘንላችሁ የቀረብነው የአንድ ጌጣጌጥ የሚሠራ ሰው ታሪክ ነው ተከታተሉ፡፡

ከብዙ ዓመታት በፊት ስሙ ጴጥሮስ የተባለ በጣም ጥሩ ክርስቲያን ነበር፡፡ የተለያዩ ጌጣጌጦች ማለትም ቀለበት፣ የአንገት ሃብል ይሠራ ነበር፡፡

“በእንተ ጦማረ ሐሰት”

ግንቦት 13፣ 2003 ዓ.ም

በሐሰት የተሠራጨውን ሰነድ በተመለከተ ከማኅበረ ቅዱሳን የተሰጠ መግለጫ

እምነትና ሥርዓቷ ጸንቶ የቆየውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሕልውናዋን ለማሳጣት እና ሐዋርያዊ ተልእኮዋን ለማደናቀፍ ቀን ከሌሊት የሚተጉ አካላት የጥፋት ሤራቸውን ከመጎንጎን እና የተቻላቸውን ሁሉ ከመፈጸም ወደ ኋላ ብለው አያውቁም፡፡ ቅድስት ቤተክርቲያን ሕግና ደንብ አውጥታ በመዋቅሯ አቅፋ እንዲያገለግል አደራና ሓላፊነት የሰጠችው ማኅበረ ቅዱሳንም የጥቃታቸው አንዱ አላማ ነው፡፡ የማኅበሩን ቀና አገልግሎት ለማስቆም ብዙ ጥረዋል፡፡